Telegram Group & Telegram Channel
" ቅድሚያ የምንሰጠው ለአሜሪካ ነው። እሱ ደግሞ ነገ ይጀምራል " - ትራምፕ

ትራምፕ በመጀመሪያ የሥልጣን ቀናቸው በርካታ ትዕዛዞችን ለማስተላለፍ ቃል ገቡ።

የዶናልድ ትራምፕ በዓለ ሲመት ዛሬ የሚከናወን ሲሆን ቃለ መሐላ በፈፀሙ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ " በታሪካዊ ፍጥነት እና ጥንካሬ " እንደሚንቀሳቀሱ ተናግረዋል።

ይህ የተናገሩት በዋሺንግተን ዲሲ በሺዎች ለሚቆጠሩ ደጋፊዎች ንግግር ባደረጉበት ወቅት ነው።

ትራምፕ ያላቸውን ፕሬዝደንታዊ ኃይል ሁሉ ተጠቅመው ስደተኞችን በገፍ ለማባረር፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ላይ የሚያተኩሩ መመሪያዎችን ለመቀነስ እና የስብጥር (ዳይቨርሲቲ) ፕሮግራሞችን ለማስቆም ቃል ገብተዋል።

" ቅድሚያ የምንሰጠው ለአሜሪካ ነው። እሱ ደግሞ ነገ ይጀምራል " ሲሉ ተናግረዋል።

አክለው " ነገ ቴሌቪዥን ስትመለከቱ እንደምትዝናኑ እርግጠኛ ነኝ " ብለዋል።

ትራምፕ ከበዓለ ሲመታቸው በኋላ 200 ገደማ ትዕዛዞች ላይ ፊርማቸውን እንደሚያሰፍሩ ይጠበቃል።

አንዳንዶቹ ትዕዛዞች እንደ ሕግ የሚቆጠሩ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ፕሬዝደንታዊ መመሪያዎች ናቸው።

ትራምፕ " እኔ ሥልጣን በያዝኩ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ የባይደን አስተዳደር ያስተላለፋቸው ትዕዛዞች ይሰረዛሉ " ብለዋል።

የሰው ሰራሽ ክህሎትን (AI) ዕድገት የሚያፋጥን እንዲሁም ኢላን መስክ የሚመራው ዶጅ የተባለ መሥሪያ ቤት እንዲቋቋም የሚወጣ ትዕዛዝ እንደሚፈርሙ አሳውቀዋል።

በተጨማሪ፦

➡️ እኤአ በ1963 ስለተገደሉት ጆን ኤፍ ኬኔዲ መረጃዎችን እንደሚለቁ፤

➡️ ወታደራዊ ኃይሉን 'አይረን ዶም' እንዲሠራ እንደሚያዙ፤

➡️ ብዝሀነት፣ እኩልነት እና አካታችነት የሚባሉ ፖሊሲዎችን ከጦር ሠራዊቱ እንደሚያስወግዱ፤

➡️ ፆታ የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት እንዳይሳተፉ እንደሚያደርጉ፤

➡️ የትምህርትን ሥልጣን ለአሜሪካ ግዛቶች አሳልፈው እንደሚሰጡ ቃል ገብተዋል።

ትራምፕ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕጋዊ ወረቀት የሌላቸውን ስደተኞች ከአሜሪካ እንደሚያባርሩ ገልጸዋል።

" እናንተን በጣም ደስተኛ የሚያደርጉ ብዙ ትዕዛዞች ማየታችሁ አይቀርም " ሲሉ ለደጋፊዎቻቸው ተናግረዋል።

#BBC

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93889
Create:
Last Update:

" ቅድሚያ የምንሰጠው ለአሜሪካ ነው። እሱ ደግሞ ነገ ይጀምራል " - ትራምፕ

ትራምፕ በመጀመሪያ የሥልጣን ቀናቸው በርካታ ትዕዛዞችን ለማስተላለፍ ቃል ገቡ።

የዶናልድ ትራምፕ በዓለ ሲመት ዛሬ የሚከናወን ሲሆን ቃለ መሐላ በፈፀሙ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ " በታሪካዊ ፍጥነት እና ጥንካሬ " እንደሚንቀሳቀሱ ተናግረዋል።

ይህ የተናገሩት በዋሺንግተን ዲሲ በሺዎች ለሚቆጠሩ ደጋፊዎች ንግግር ባደረጉበት ወቅት ነው።

ትራምፕ ያላቸውን ፕሬዝደንታዊ ኃይል ሁሉ ተጠቅመው ስደተኞችን በገፍ ለማባረር፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ላይ የሚያተኩሩ መመሪያዎችን ለመቀነስ እና የስብጥር (ዳይቨርሲቲ) ፕሮግራሞችን ለማስቆም ቃል ገብተዋል።

" ቅድሚያ የምንሰጠው ለአሜሪካ ነው። እሱ ደግሞ ነገ ይጀምራል " ሲሉ ተናግረዋል።

አክለው " ነገ ቴሌቪዥን ስትመለከቱ እንደምትዝናኑ እርግጠኛ ነኝ " ብለዋል።

ትራምፕ ከበዓለ ሲመታቸው በኋላ 200 ገደማ ትዕዛዞች ላይ ፊርማቸውን እንደሚያሰፍሩ ይጠበቃል።

አንዳንዶቹ ትዕዛዞች እንደ ሕግ የሚቆጠሩ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ፕሬዝደንታዊ መመሪያዎች ናቸው።

ትራምፕ " እኔ ሥልጣን በያዝኩ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ የባይደን አስተዳደር ያስተላለፋቸው ትዕዛዞች ይሰረዛሉ " ብለዋል።

የሰው ሰራሽ ክህሎትን (AI) ዕድገት የሚያፋጥን እንዲሁም ኢላን መስክ የሚመራው ዶጅ የተባለ መሥሪያ ቤት እንዲቋቋም የሚወጣ ትዕዛዝ እንደሚፈርሙ አሳውቀዋል።

በተጨማሪ፦

➡️ እኤአ በ1963 ስለተገደሉት ጆን ኤፍ ኬኔዲ መረጃዎችን እንደሚለቁ፤

➡️ ወታደራዊ ኃይሉን 'አይረን ዶም' እንዲሠራ እንደሚያዙ፤

➡️ ብዝሀነት፣ እኩልነት እና አካታችነት የሚባሉ ፖሊሲዎችን ከጦር ሠራዊቱ እንደሚያስወግዱ፤

➡️ ፆታ የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት እንዳይሳተፉ እንደሚያደርጉ፤

➡️ የትምህርትን ሥልጣን ለአሜሪካ ግዛቶች አሳልፈው እንደሚሰጡ ቃል ገብተዋል።

ትራምፕ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕጋዊ ወረቀት የሌላቸውን ስደተኞች ከአሜሪካ እንደሚያባርሩ ገልጸዋል።

" እናንተን በጣም ደስተኛ የሚያደርጉ ብዙ ትዕዛዞች ማየታችሁ አይቀርም " ሲሉ ለደጋፊዎቻቸው ተናግረዋል።

#BBC

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA




❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93889

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The regulator took order for the search and seizure operation from Judge Purushottam B Jadhav, Sebi Special Judge / Additional Sessions Judge. He adds: "Telegram has become my primary news source." If you initiate a Secret Chat, however, then these communications are end-to-end encrypted and are tied to the device you are using. That means it’s less convenient to access them across multiple platforms, but you are at far less risk of snooping. Back in the day, Secret Chats received some praise from the EFF, but the fact that its standard system isn’t as secure earned it some criticism. If you’re looking for something that is considered more reliable by privacy advocates, then Signal is the EFF’s preferred platform, although that too is not without some caveats. Telegram has become more interventionist over time, and has steadily increased its efforts to shut down these accounts. But this has also meant that the company has also engaged with lawmakers more generally, although it maintains that it doesn’t do so willingly. For instance, in September 2021, Telegram reportedly blocked a chat bot in support of (Putin critic) Alexei Navalny during Russia’s most recent parliamentary elections. Pavel Durov was quoted at the time saying that the company was obliged to follow a “legitimate” law of the land. He added that as Apple and Google both follow the law, to violate it would give both platforms a reason to boot the messenger from its stores. The War on Fakes channel has repeatedly attempted to push conspiracies that footage from Ukraine is somehow being falsified. One post on the channel from February 24 claimed without evidence that a widely viewed photo of a Ukrainian woman injured in an airstrike in the city of Chuhuiv was doctored and that the woman was seen in a different photo days later without injuries. The post, which has over 600,000 views, also baselessly claimed that the woman's blood was actually makeup or grape juice.
from pl


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American