Telegram Group & Telegram Channel
“ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶታል” - ጤና ሳይንስ ኮሌጁ

የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥበበ ግዮን ግቢ ስፔሻላንስድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ዳኘ በተተኮሰባቸው ጥይት መገዳላቸውን ዩኒቨርሲቲውና ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ለደህንነታቸው ሲባል ስሜ ከመነገር ይቆይ ያሉ አንድ የዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶበታል ” ሲሉ አስረድተዋል።

ተኩሱ ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃዎች በፊት በአካባቢው እንዳለፉ የገለጹት እኝሁ አካል ስለ ዶክተር አንዷለም ሲገልጹ፣ “ ከሥራ እየተመለሰ በነበረበት ወቅት ቆሸ የሚባለው ሰፈር ተኩስ ተከፈተበት ” ነው ያሉት።

“ አንዷለምን የምናውቀው ደግ፣ ሩህሩህ፣ የሁላችንም ምሳሌ አድርገን ነው። ሰው ነው ከሰውም ሰው ” ሲሉ እያለቀሱ ተናግረዋል።

የገዳዮቹ ማንነት ታውቋል ? የለበሱት ልብስ ምን አይነት ነበር ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ “ እርግጠኛ ሆኖ አሁን መናገር አይቻልም ” ብለዋል።

አክለው፣“ አንድ ከዶ/ር አንዷለም በፊት ሲጓዝ የነበረ ሀኪም ተተኩሶበት ተርፏል። ‘ሦስት የሚተኩሱ ሰዎች ነበሩ፤ የምን እንደሆነ አላውቅም ዩኒፎርም ነገር ለብሰዋል’ ብሎናል ” ሲሉ አስረድተዋል።

በጥበበ ግዮን ግቢ ህክምና ጤና ሳይንስ ኢንተርን ሀኪሞች በበኩላቸው፣ “ ዶክተር አንዷለም ከከተማ ከሥራ ውሎ ሲመለስ ምሽት ላይ ነው የተመታው። ግን ማን እንደመታው የተረጋገጠ ነገር የለም ” ሲሉ ነግረውናል።

“ አስከሬኑም ለፓሊስ ተደውሎ ነው ማታ የተነሳው ” ያሉት ኢንተርን ሀኪሞቹ፣ “ አሁን ሀኪሞቹም፣ ሬዚደንቶቹም ሁሉም የባሕር ዳር ዩኑቨርሲቲ ተማሪዎችና ሠራተኞች ሀዘኑን እየተካፈልን ነው ያለነው ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቃቸው የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶክተር መንገሻ ከሰዓታት በፊት በሰጡን ቃል “ አስከሬን ይዘን ከቤት ወደ ቤተክርስቲያን እየወጣን ነው ” የሚል አጭር ማረጋጠጫ ብቻ ሰጥተዋል።

ስለገዳዮቹ ማንነት የታወቀ ነገር እንዳለ የጠየቅነው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጸጥታ ክፍል በሰጠን ምላሽ፣ “ ግድያው ከግቢ ውጪ ስለተፈጠረ ምንም ያወቅነው ነገር የለም ” ብሏል።

“ ያወቅነው መረጃ የለንም። እኛም እንደማንኛውም ሰው መሞቱን ብቻ ነው የሰማነው ” ሲል አክሏል።

የሚመለከታቸውን የከተማውን የጸጥታ አካላት ለጉዳዩ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጥያቄ የምናቀርብ ይሆናል።

ዶክተር አንዷለም ዳኘ የዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ስፔሻሊስት፤ የጉበት፣ የቆሽት፣ የሀሞት ጠጠር መስመር ሰብ ስፐረሻሊስት ሀኪም፣ እንዲሁም የልጆች አባት እንደነበር ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። 

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94201
Create:
Last Update:

“ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶታል” - ጤና ሳይንስ ኮሌጁ

የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥበበ ግዮን ግቢ ስፔሻላንስድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ዳኘ በተተኮሰባቸው ጥይት መገዳላቸውን ዩኒቨርሲቲውና ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ለደህንነታቸው ሲባል ስሜ ከመነገር ይቆይ ያሉ አንድ የዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶበታል ” ሲሉ አስረድተዋል።

ተኩሱ ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃዎች በፊት በአካባቢው እንዳለፉ የገለጹት እኝሁ አካል ስለ ዶክተር አንዷለም ሲገልጹ፣ “ ከሥራ እየተመለሰ በነበረበት ወቅት ቆሸ የሚባለው ሰፈር ተኩስ ተከፈተበት ” ነው ያሉት።

“ አንዷለምን የምናውቀው ደግ፣ ሩህሩህ፣ የሁላችንም ምሳሌ አድርገን ነው። ሰው ነው ከሰውም ሰው ” ሲሉ እያለቀሱ ተናግረዋል።

የገዳዮቹ ማንነት ታውቋል ? የለበሱት ልብስ ምን አይነት ነበር ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ “ እርግጠኛ ሆኖ አሁን መናገር አይቻልም ” ብለዋል።

አክለው፣“ አንድ ከዶ/ር አንዷለም በፊት ሲጓዝ የነበረ ሀኪም ተተኩሶበት ተርፏል። ‘ሦስት የሚተኩሱ ሰዎች ነበሩ፤ የምን እንደሆነ አላውቅም ዩኒፎርም ነገር ለብሰዋል’ ብሎናል ” ሲሉ አስረድተዋል።

በጥበበ ግዮን ግቢ ህክምና ጤና ሳይንስ ኢንተርን ሀኪሞች በበኩላቸው፣ “ ዶክተር አንዷለም ከከተማ ከሥራ ውሎ ሲመለስ ምሽት ላይ ነው የተመታው። ግን ማን እንደመታው የተረጋገጠ ነገር የለም ” ሲሉ ነግረውናል።

“ አስከሬኑም ለፓሊስ ተደውሎ ነው ማታ የተነሳው ” ያሉት ኢንተርን ሀኪሞቹ፣ “ አሁን ሀኪሞቹም፣ ሬዚደንቶቹም ሁሉም የባሕር ዳር ዩኑቨርሲቲ ተማሪዎችና ሠራተኞች ሀዘኑን እየተካፈልን ነው ያለነው ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቃቸው የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶክተር መንገሻ ከሰዓታት በፊት በሰጡን ቃል “ አስከሬን ይዘን ከቤት ወደ ቤተክርስቲያን እየወጣን ነው ” የሚል አጭር ማረጋጠጫ ብቻ ሰጥተዋል።

ስለገዳዮቹ ማንነት የታወቀ ነገር እንዳለ የጠየቅነው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጸጥታ ክፍል በሰጠን ምላሽ፣ “ ግድያው ከግቢ ውጪ ስለተፈጠረ ምንም ያወቅነው ነገር የለም ” ብሏል።

“ ያወቅነው መረጃ የለንም። እኛም እንደማንኛውም ሰው መሞቱን ብቻ ነው የሰማነው ” ሲል አክሏል።

የሚመለከታቸውን የከተማውን የጸጥታ አካላት ለጉዳዩ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጥያቄ የምናቀርብ ይሆናል።

ዶክተር አንዷለም ዳኘ የዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ስፔሻሊስት፤ የጉበት፣ የቆሽት፣ የሀሞት ጠጠር መስመር ሰብ ስፐረሻሊስት ሀኪም፣ እንዲሁም የልጆች አባት እንደነበር ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። 

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94201

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

These administrators had built substantial positions in these scrips prior to the circulation of recommendations and offloaded their positions subsequent to rise in price of these scrips, making significant profits at the expense of unsuspecting investors, Sebi noted. READ MORE In addition, Telegram's architecture limits the ability to slow the spread of false information: the lack of a central public feed, and the fact that comments are easily disabled in channels, reduce the space for public pushback. Stocks dropped on Friday afternoon, as gains made earlier in the day on hopes for diplomatic progress between Russia and Ukraine turned to losses. Technology stocks were hit particularly hard by higher bond yields. In a message on his Telegram channel recently recounting the episode, Durov wrote: "I lost my company and my home, but would do it again – without hesitation."
from pl


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American