Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል አስራ ሶስት
ትዝታ ከቤት እንደወጣች ብሌን በእፎይታ ሶፋው ላይ ተወረወረች። እዮብ ቢሆን እንደዚች አይነቷን አይደለም ለጓደኝነት ለአይንም ቢሆን ይጠየፋት ነበር ስትል አሰበች። መልካቸው ብቻ ነው ለካ የሚመሳሰለው አለች በልቧ። ምንም ስለአልአዛር የግል ህይወት አያገባኝም! ግን ምን ሲሆን ከእንደዚች አይነቷ ጋር ሆነ? ብሌን ከቅሬታዋ በላይ የሚሰማት ብስጭት መንስኤውን አለማወቋ አሳሰባት። ምን አልባት አልአዛርን እንደ እዮብ ቆጥራው ይሆናል። ወይም የወንድሙ ውለታ ስለሱ እንድትጨነቅ አስገድዷትም ይሆናል። ብቻ ተበሳጭታለች። ማታ አልአዛር እስኪመጣ መታገስ አቃታት።

እንደምንም መሸና አልአዛር ቤት መጣ። እራት ካቀረበች በኃላ "ትዝታ የምትባል ሴት መጥታ ነበር።" እዚ ስታጣህ ሱቅ ይኖራል ብዬ ብነግራትም ነገ መጣለው ብላ ሄደች አለች በዝምታ የተዋጠውን ማዕድ በማደፍረስ። እና ምን አለችሽ? የሚያስቀይም ነገር ተናገረችሽ? ጥያቄውን አከታትሎ ጠየቃት። አይ ምንም አልተናገረችም የናትናኤል እጮኛ ነኝ ብዬ ስነግራት ያመነችኝ ትመስላለች ... ብሌን እናቷን ስትዋሻት ሁሌም ታውቅባት ነበር። ትዝታ ግን አለማወቋ አስደስቷታል።

አልአዛር የብሌን ትዝታን ማየት ረፍት ነሳው። የትዝታ መጥፎ ባህሪያቶች ብቻ ሳይሆን ብሌን ከነጭራሹ ከትዝታ ጋር የነበረውን ነገር ባታውቅበት ይመርጣል። ዛሬ ካለወትሮው ወደ ስራ ለምን እንደሄደ አሰበ "ሽሽት" አለ በሆዱ። እኮ ከምን? መልሶ ራሱን ጠየቀ። ከብሌን? እሱማ አይሆንም በሌላ ያሳበበው ስጋቱ እየተገለጠ ነው።

ጠዋት ይወጣል ማታ ይገባል። በሚገናኙበት ጊዜም ብዙም እንዲያወሩ አይፈልግም። የብሌን ትህትና መልክ አነጋገር ለወንዶች ቀዝቃዛ ወጥመድም ነው። በወጥመዱም ላለመያዝ ይሸሻል ግን ስሜቱ ባላወቀው መንገድ የተሸነፈ ይመስላል ወንድሙን እዮብን የከዳ ቃልኪዳኑን ያጠፈ ስሜት እስኪሰማው ያህል።

መሸሻ ፈለገ ከቤቱ የት ይሂድ? ብሌን ደግሞ እሷን ለአይኑ እንኳን የጠላት መስሏታል። ሊያናግራት አለመፈለጉ አይኖቹን ከእሷ ማሸሹ  ለወንድሙ ሞት ተጠያቂ እሷ የሆነች አድርጎ ያሰበ መሰላት። ትክክል ነው ከኔ ውጪ ለእዮብ ሞት ተጠያቂ ማነው? እዮብን ስታስብ በፀፀት ልትሞት ትደርሳለች። ስለ እሱም ላለመስማት ላለማሰብ ጥረት አድርጋለች ግን ከጭንቅላቷ ሊወጣላት አልቻለም። ቀስ በቀስ ድባቴ ውስጥ መግባት ጀመረች። ቀን ላይ ስለነበራት ህይወት አሁን ስላለችበት ስለወደፊቷ በማሰብ ራሷን ታስጨንቃለች። መሽቶም አልአዛር ሲመጣ ከአንድ ሁለት ቃላት ውጪ ንግግር ስለማይኖራቸው የመሰልቸት የተጠያቂነት ስሜቷ አየለባት።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/129
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል አስራ ሶስት
ትዝታ ከቤት እንደወጣች ብሌን በእፎይታ ሶፋው ላይ ተወረወረች። እዮብ ቢሆን እንደዚች አይነቷን አይደለም ለጓደኝነት ለአይንም ቢሆን ይጠየፋት ነበር ስትል አሰበች። መልካቸው ብቻ ነው ለካ የሚመሳሰለው አለች በልቧ። ምንም ስለአልአዛር የግል ህይወት አያገባኝም! ግን ምን ሲሆን ከእንደዚች አይነቷ ጋር ሆነ? ብሌን ከቅሬታዋ በላይ የሚሰማት ብስጭት መንስኤውን አለማወቋ አሳሰባት። ምን አልባት አልአዛርን እንደ እዮብ ቆጥራው ይሆናል። ወይም የወንድሙ ውለታ ስለሱ እንድትጨነቅ አስገድዷትም ይሆናል። ብቻ ተበሳጭታለች። ማታ አልአዛር እስኪመጣ መታገስ አቃታት።

እንደምንም መሸና አልአዛር ቤት መጣ። እራት ካቀረበች በኃላ "ትዝታ የምትባል ሴት መጥታ ነበር።" እዚ ስታጣህ ሱቅ ይኖራል ብዬ ብነግራትም ነገ መጣለው ብላ ሄደች አለች በዝምታ የተዋጠውን ማዕድ በማደፍረስ። እና ምን አለችሽ? የሚያስቀይም ነገር ተናገረችሽ? ጥያቄውን አከታትሎ ጠየቃት። አይ ምንም አልተናገረችም የናትናኤል እጮኛ ነኝ ብዬ ስነግራት ያመነችኝ ትመስላለች ... ብሌን እናቷን ስትዋሻት ሁሌም ታውቅባት ነበር። ትዝታ ግን አለማወቋ አስደስቷታል።

አልአዛር የብሌን ትዝታን ማየት ረፍት ነሳው። የትዝታ መጥፎ ባህሪያቶች ብቻ ሳይሆን ብሌን ከነጭራሹ ከትዝታ ጋር የነበረውን ነገር ባታውቅበት ይመርጣል። ዛሬ ካለወትሮው ወደ ስራ ለምን እንደሄደ አሰበ "ሽሽት" አለ በሆዱ። እኮ ከምን? መልሶ ራሱን ጠየቀ። ከብሌን? እሱማ አይሆንም በሌላ ያሳበበው ስጋቱ እየተገለጠ ነው።

ጠዋት ይወጣል ማታ ይገባል። በሚገናኙበት ጊዜም ብዙም እንዲያወሩ አይፈልግም። የብሌን ትህትና መልክ አነጋገር ለወንዶች ቀዝቃዛ ወጥመድም ነው። በወጥመዱም ላለመያዝ ይሸሻል ግን ስሜቱ ባላወቀው መንገድ የተሸነፈ ይመስላል ወንድሙን እዮብን የከዳ ቃልኪዳኑን ያጠፈ ስሜት እስኪሰማው ያህል።

መሸሻ ፈለገ ከቤቱ የት ይሂድ? ብሌን ደግሞ እሷን ለአይኑ እንኳን የጠላት መስሏታል። ሊያናግራት አለመፈለጉ አይኖቹን ከእሷ ማሸሹ  ለወንድሙ ሞት ተጠያቂ እሷ የሆነች አድርጎ ያሰበ መሰላት። ትክክል ነው ከኔ ውጪ ለእዮብ ሞት ተጠያቂ ማነው? እዮብን ስታስብ በፀፀት ልትሞት ትደርሳለች። ስለ እሱም ላለመስማት ላለማሰብ ጥረት አድርጋለች ግን ከጭንቅላቷ ሊወጣላት አልቻለም። ቀስ በቀስ ድባቴ ውስጥ መግባት ጀመረች። ቀን ላይ ስለነበራት ህይወት አሁን ስላለችበት ስለወደፊቷ በማሰብ ራሷን ታስጨንቃለች። መሽቶም አልአዛር ሲመጣ ከአንድ ሁለት ቃላት ውጪ ንግግር ስለማይኖራቸው የመሰልቸት የተጠያቂነት ስሜቷ አየለባት።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/129

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

This provided opportunity to their linked entities to offload their shares at higher prices and make significant profits at the cost of unsuspecting retail investors. Channels are not fully encrypted, end-to-end. All communications on a Telegram channel can be seen by anyone on the channel and are also visible to Telegram. Telegram may be asked by a government to hand over the communications from a channel. Telegram has a history of standing up to Russian government requests for data, but how comfortable you are relying on that history to predict future behavior is up to you. Because Telegram has this data, it may also be stolen by hackers or leaked by an internal employee. Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more. The regulator said it had received information that messages containing stock tips and other investment advice with respect to selected listed companies are being widely circulated through websites and social media platforms such as Telegram, Facebook, WhatsApp and Instagram. "There is a significant risk of insider threat or hacking of Telegram systems that could expose all of these chats to the Russian government," said Eva Galperin with the Electronic Frontier Foundation, which has called for Telegram to improve its privacy practices.
from pl


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American