Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-92960-92961-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/92961 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

🚨“ አቶ ክርስቲያን ታደለና ዮሐንስ ቧያለው ዛሬ የሐኪም ቀጠሮ ነበራቸው ማረሚያ ቤቱ አልወሰዳቸውም ” - ቤተሰቦቻቸው

🔴 “ በሕይወት የመኖር መብታቸውን ነው ያሳጧቸው። የእስረኛ ዝውውር ወይስ በሕይወት የመኖር መብት ነው የሚቀድመው ? ” - ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ

አዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት ባደረባቸው የጤና እክል በወቅቱ ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት ህመም የተዳረጉት አቶ ክርስቲያን ታደለና አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣ ሰሞኑን የቀዶ ህክምና ተደርጎላቸው ወዲያው ወደ ማረሚያ ቤት በመመለሳቸው ደም እየፈሰሳቸው እንደሆነ፣ ዛሬም የሀኪም ቤት ቀጠሮ እንደነበራቸው ቤተሰቦቻቸው ትላንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

ለዛሬው ሀኪም ቤት ቀጠሯቸው ሄዱ ?

ሁሉቱም ዛሬ (ሐሙስ ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ/ም) ለቸካፕ ቀጠሮ የነበራቸው ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ እንዳልወሰዳቸው ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። 

አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ተደጋጋሚ የደም መፍሰስ እያጋጠማቸው በመሆኑ ቁስላቸው ለኢንፌክሽን እንዳይጋለጥ ለቸካፕ ለዛሬ በመቅረዝ ሆስፒታል ቀጠሮ እንደነበራቸው አስረድተዋል።

ቀጠሮው ስለሰርጀሪው ፣ ለቅድመ ካንሰር ምርመራ ውጤቱ፣ ለቀጣይ ተከታታይ ህክምና የሚሰጣቸውን የቀጠሮ ቀን የሚውቁበት እንደነበር ገልጸው፣ “ ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ አልወሰዳቸውም ” ሲሉ ወቅሰዋል።

የእነ የአቶ ክርስቲያንና ዮሐንስ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ በበኩላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

በቀጠሮው አለመሄዳቸው ጉዳት ያመጣል። ለሁለት ነገር ነው በምርመራ ላይ ያሉት። አንደኛ በፊንጢጣ በኩል ኦፕራሲዮን ተደርገው ደም እየፈሰሳቸው ነው።

አዋሽ አርባ በነበሩበት ወቅት የአንጀት ድርቀት ገጥሟቸው ባለመታከማቸው በኋላ ላይም በሽብር ወንጀል ተከሰው ፍርድ ቤት ከቀረቡ በኋላ በብዙ ጭቅጭቅ ማረሚያ ቤቱ ወደ ሀኪም ቤት ቢሄዱም የሰርጀሪ ደሙ አልቆመም። 

ሆስፒታሉም ‘በዚህ ቀን ይዛችሁ ኑ’ ብሎ ፐርስክርፒሽን ሰጥቷል። ይሄ ህመም ነው የጤና ጉዳይ ነው። የዛሬ የሆስፒታል ቀጠሮ የሚፈሰውን ደምና የቁስሉን ምንነት ለማረጋጠጥ ነበር።

ሁለተኛ የአንጀታቸውን በተመለከተ ኦፕራሲዮን ለማድረግ የካንሰር ምርመራ አድርገዋል። ውጤት ለማወቅ ነበር ቀጠሮው። ግን ከቤተሰቦቻቸው የሰማሁት በቀጠሯቸው መመሠረት ሀኪም ቤት እንዳልወሰዷቸው ነው።

ማረሚያ ቤቱ ያቀረበው ምክንያት ‘እስረኞቹን ወደ ሌላ ቦታ እያዘዋወርን በመሆኑ አጃቢና መኪና ስሌለ ነው’ በሚል ነው። ይሄን በተመለከተ ፍርድ ቤት ምስክር በምናሰማቸው በነ ዶክተር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ ዐቃቢ ህግ ምስክር እያሰማ እዛው ውለናል ከትላንትና ትላንት ወዲያ።

‘እስረኛ እያዘዋወርን ስለሆነ አናመጣቸውም’ የሚል ወረቀት ቢያስገቡም ‘አይቻልም’ ብሎ ፍርድ ቤቱም ትዕዛዝ ስለሰጣቸው ትላንትናም አምጥተዋቸዋል። ትላንትም ምስክር ሰምተናል፣ ዛሬም ምስክር ሰምተናል።

ታዲያ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሲሆን ብቻ ነው እንዴ እነርሱ የሚያከብሩት ? በእርግጥ እስረኛ እያዘዋወሩ እንደሆነ ይታወቃል። ግን ምስክር ለመስማት ‘አምጡ’ ሲባሉ ነው ተገደው ማምጣት ያለባቸው ወይስ የሕይወትና የሞት ጉዳይ ሲሆን ነው አፋጣኝ እርምጃ ወስደው ማምጣት ያለባቸው ?

መቼም የማረሚያ ቤት አስተዳደር ብዙ ጠባቂዎች አሉ። እንደምንም ተፈልጎም መኪናም ተከራይተውም ቢሆን የሕይወት ጉዳይ ስለሆነ በቀጠሯቸው መሠረት አምጥተው ማሳከም ነበረባቸው። 

ስለዚህ ድርጊቱ አግባብ አይደለም። ይሄ በሕይወት የመኖር መብትንም የሚጣረስ ነው። እነዚህ ሰዎች አሁን ደም እየፈሰሳቸው ነው በቀጣይነት ደሙ ቢፈስስ? የቅድመ ካንሰር ምርመራ ሕይወት ወደማሰጣት ቢደርስስ ? 

በመሆኑም በሕይወት የመኖር መብታቸውን ነው ያሳጧቸው። የእስረኛ ዝውውር ነው ወይስ በሕይወት የመኖር መብት የሚቀድመው? በሕይወት የመኖር መብት ነው መቅድም ያለበት ”
ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/92961
Create:
Last Update:

#Update

🚨“ አቶ ክርስቲያን ታደለና ዮሐንስ ቧያለው ዛሬ የሐኪም ቀጠሮ ነበራቸው ማረሚያ ቤቱ አልወሰዳቸውም ” - ቤተሰቦቻቸው

🔴 “ በሕይወት የመኖር መብታቸውን ነው ያሳጧቸው። የእስረኛ ዝውውር ወይስ በሕይወት የመኖር መብት ነው የሚቀድመው ? ” - ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ

አዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት ባደረባቸው የጤና እክል በወቅቱ ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት ህመም የተዳረጉት አቶ ክርስቲያን ታደለና አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣ ሰሞኑን የቀዶ ህክምና ተደርጎላቸው ወዲያው ወደ ማረሚያ ቤት በመመለሳቸው ደም እየፈሰሳቸው እንደሆነ፣ ዛሬም የሀኪም ቤት ቀጠሮ እንደነበራቸው ቤተሰቦቻቸው ትላንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

ለዛሬው ሀኪም ቤት ቀጠሯቸው ሄዱ ?

ሁሉቱም ዛሬ (ሐሙስ ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ/ም) ለቸካፕ ቀጠሮ የነበራቸው ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ እንዳልወሰዳቸው ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። 

አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ተደጋጋሚ የደም መፍሰስ እያጋጠማቸው በመሆኑ ቁስላቸው ለኢንፌክሽን እንዳይጋለጥ ለቸካፕ ለዛሬ በመቅረዝ ሆስፒታል ቀጠሮ እንደነበራቸው አስረድተዋል።

ቀጠሮው ስለሰርጀሪው ፣ ለቅድመ ካንሰር ምርመራ ውጤቱ፣ ለቀጣይ ተከታታይ ህክምና የሚሰጣቸውን የቀጠሮ ቀን የሚውቁበት እንደነበር ገልጸው፣ “ ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ አልወሰዳቸውም ” ሲሉ ወቅሰዋል።

የእነ የአቶ ክርስቲያንና ዮሐንስ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ በበኩላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

በቀጠሮው አለመሄዳቸው ጉዳት ያመጣል። ለሁለት ነገር ነው በምርመራ ላይ ያሉት። አንደኛ በፊንጢጣ በኩል ኦፕራሲዮን ተደርገው ደም እየፈሰሳቸው ነው።

አዋሽ አርባ በነበሩበት ወቅት የአንጀት ድርቀት ገጥሟቸው ባለመታከማቸው በኋላ ላይም በሽብር ወንጀል ተከሰው ፍርድ ቤት ከቀረቡ በኋላ በብዙ ጭቅጭቅ ማረሚያ ቤቱ ወደ ሀኪም ቤት ቢሄዱም የሰርጀሪ ደሙ አልቆመም። 

ሆስፒታሉም ‘በዚህ ቀን ይዛችሁ ኑ’ ብሎ ፐርስክርፒሽን ሰጥቷል። ይሄ ህመም ነው የጤና ጉዳይ ነው። የዛሬ የሆስፒታል ቀጠሮ የሚፈሰውን ደምና የቁስሉን ምንነት ለማረጋጠጥ ነበር።

ሁለተኛ የአንጀታቸውን በተመለከተ ኦፕራሲዮን ለማድረግ የካንሰር ምርመራ አድርገዋል። ውጤት ለማወቅ ነበር ቀጠሮው። ግን ከቤተሰቦቻቸው የሰማሁት በቀጠሯቸው መመሠረት ሀኪም ቤት እንዳልወሰዷቸው ነው።

ማረሚያ ቤቱ ያቀረበው ምክንያት ‘እስረኞቹን ወደ ሌላ ቦታ እያዘዋወርን በመሆኑ አጃቢና መኪና ስሌለ ነው’ በሚል ነው። ይሄን በተመለከተ ፍርድ ቤት ምስክር በምናሰማቸው በነ ዶክተር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ ዐቃቢ ህግ ምስክር እያሰማ እዛው ውለናል ከትላንትና ትላንት ወዲያ።

‘እስረኛ እያዘዋወርን ስለሆነ አናመጣቸውም’ የሚል ወረቀት ቢያስገቡም ‘አይቻልም’ ብሎ ፍርድ ቤቱም ትዕዛዝ ስለሰጣቸው ትላንትናም አምጥተዋቸዋል። ትላንትም ምስክር ሰምተናል፣ ዛሬም ምስክር ሰምተናል።

ታዲያ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሲሆን ብቻ ነው እንዴ እነርሱ የሚያከብሩት ? በእርግጥ እስረኛ እያዘዋወሩ እንደሆነ ይታወቃል። ግን ምስክር ለመስማት ‘አምጡ’ ሲባሉ ነው ተገደው ማምጣት ያለባቸው ወይስ የሕይወትና የሞት ጉዳይ ሲሆን ነው አፋጣኝ እርምጃ ወስደው ማምጣት ያለባቸው ?

መቼም የማረሚያ ቤት አስተዳደር ብዙ ጠባቂዎች አሉ። እንደምንም ተፈልጎም መኪናም ተከራይተውም ቢሆን የሕይወት ጉዳይ ስለሆነ በቀጠሯቸው መሠረት አምጥተው ማሳከም ነበረባቸው። 

ስለዚህ ድርጊቱ አግባብ አይደለም። ይሄ በሕይወት የመኖር መብትንም የሚጣረስ ነው። እነዚህ ሰዎች አሁን ደም እየፈሰሳቸው ነው በቀጣይነት ደሙ ቢፈስስ? የቅድመ ካንሰር ምርመራ ሕይወት ወደማሰጣት ቢደርስስ ? 

በመሆኑም በሕይወት የመኖር መብታቸውን ነው ያሳጧቸው። የእስረኛ ዝውውር ነው ወይስ በሕይወት የመኖር መብት የሚቀድመው? በሕይወት የመኖር መብት ነው መቅድም ያለበት ”
ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/92961

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Under the Sebi Act, the regulator has the power to carry out search and seizure of books, registers, documents including electronics and digital devices from any person associated with the securities market. Recently, Durav wrote on his Telegram channel that users' right to privacy, in light of the war in Ukraine, is "sacred, now more than ever." He floated the idea of restricting the use of Telegram in Ukraine and Russia, a suggestion that was met with fierce opposition from users. Shortly after, Durov backed off the idea. Pavel Durov, a billionaire who embraces an all-black wardrobe and is often compared to the character Neo from "the Matrix," funds Telegram through his personal wealth and debt financing. And despite being one of the world's most popular tech companies, Telegram reportedly has only about 30 employees who defer to Durov for most major decisions about the platform. "Russians are really disconnected from the reality of what happening to their country," Andrey said. "So Telegram has become essential for understanding what's going on to the Russian-speaking world."
from ru


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American