Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#መግለጫ : " የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " ሰኞ በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ በተመሳሳይ ሰዓት ይካሄዳል። ይህንን አስመልክቶ የተሰጠው መግለጫ ከላይ ተያይዟል። የዘንድሮው የእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads በአዲስ አበባ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል (ቦሌ መድኃኔዓለም) ፤ በድሬዳዋ ደግሞ ለገሀር አደባባይ ብቻ ነው የሚካሄደው። (መግለጫውን ያንብቡ)…
#የአእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads

“ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” - የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ (ኢጃት)

ታኅሳስ 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረውን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያው ጃንደረባ ትውልድ ያዘጋጀው “ልደትን በባለ ልደቱ ቤት” የተሰኘውን የአእላፍ ዝማሬ በተመለከተ አዘጋጆቹ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥተዋል።

የዝማሬ ጉባዔው በአዲስ አበባ በድሬዳዋ እንደሚከናወን የገለጹት አዘጋጆች፣ “ ላለፉት ስምንት ወራት ለዚህ ታላቅ የዝማሬ ጉባዔ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል ” ብለዋል።

የጉባዔው ዋነኛ ዓላማ በአልባሌ ቦታ የሚውሉ ወገኖች በዓሉን በቤተክርስቲያን የመላክትን ዝማሬ በመዘመር እንዲያሳልፉ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ቢንያም አሕመድ ፤  “ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” ብለዋል።

“ በሌሎች አካባቢዎች ላይ የተዘጋጁ ዝግጅቶች ካሉም በእዛው በመገኘት እንድታሳልፉ የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ ጥሪ ያቀርባል ” ሲሉ አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ በቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ ምንም አይነት ሽያጭ እንደማይከናውን አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል፣ “ አእላፋት ዝማሬ ነጭ ልብስ ልበሱ ” ተብሏል በሚል ነጭ ልብስ በተጋነነ ዋጋ የሚቸበችቡ ሁነቱን የተከተሉ ነጋዴዎች ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ነጭ ልብስ በውድ ወጋ እየተቸበቸበ ነው የሚል አስተያዬት እየተሰጠ ተስተውሏል፣ ለመርሀ ግብሩ ነጭ ልብስ ብቻ ለብሶ መምጣት ግዴታ ነው ? ሲል ለአዘጋጆቹ ጥያቄ አቅርቧል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ብንያም አሕመድ በሰጡት ምላሽም፣ “ ነጭ ልብስ የሌለን ያለንን ልብስ ንጹህ አድርገን እንምጣ። ዓላማችን ልብሱ ለመቁረቢያ እንዲሆን ነው ” ብለዋል።

“ ኦርቶዶክሳዊ ኢኮኖሚ እንዲፈጠር ይፈለጋል ግልጽ ነው። በዚህ ምክንያት ወደ ስራ የሚገቡ፣ ሥራቸውን የሚያስፋፉ፣ የሚለወጡ ኦርቶዶክሳዊያን ቢኖሩ ይሄ የማኀበራችን አንዱ ዓላማ ነው ” ሲሉ ነው የተናገሩት።

“ ስለዚህ ይህን በቀና ዓይን ነው የምናየው ” ያሉት አቶ ብንያም፣ “ በእርግጥ በዚሁ ምክንያት ደግሞ አጋጣሚውን የሚጠቀሙ፣ Accidental Entrprenuers የምንላቸው መጥተው ባለሃብት ለመሆን የሚጥሩ ይኖራሉ ” ሲሉም አክለዋል።

“ ልደቱ የሰዎች የመላክት ዝማሬ ነው። ስለዚህ ይህንን በማሰብ ነጭ ለብሰን እንመጣለን ” ብለው፣ “ ዘወትር ወደ ቤተ ክርስቲያን ስንሄድ የምናደርገው ነው፣ የተለዬ ነገር የለውም ” ነው ያሉት።

ሆኖም ነጭ ልብስ የሌላቸው ያላቸውን ልብስ በአግባቡ ለብሰው በዝማሬ መርሀ ግብሩ መገኘታቸው እንዳይዘነጋ መልዕክት ተላልፏል። 

ዝማሬው ዘማሪያን እየዘመሩ ምዕመናን የሚቀበሉበት ሂደት ሳይሆን ልደቱን በሚያወሱ ዝማሬዎች ሁሉም በጋራ ምስጋና እንዲያቀርብ መሆኑ ተሰምሮበታል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93419
Create:
Last Update:

#የአእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads

“ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” - የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ (ኢጃት)

ታኅሳስ 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረውን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያው ጃንደረባ ትውልድ ያዘጋጀው “ልደትን በባለ ልደቱ ቤት” የተሰኘውን የአእላፍ ዝማሬ በተመለከተ አዘጋጆቹ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥተዋል።

የዝማሬ ጉባዔው በአዲስ አበባ በድሬዳዋ እንደሚከናወን የገለጹት አዘጋጆች፣ “ ላለፉት ስምንት ወራት ለዚህ ታላቅ የዝማሬ ጉባዔ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል ” ብለዋል።

የጉባዔው ዋነኛ ዓላማ በአልባሌ ቦታ የሚውሉ ወገኖች በዓሉን በቤተክርስቲያን የመላክትን ዝማሬ በመዘመር እንዲያሳልፉ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ቢንያም አሕመድ ፤  “ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” ብለዋል።

“ በሌሎች አካባቢዎች ላይ የተዘጋጁ ዝግጅቶች ካሉም በእዛው በመገኘት እንድታሳልፉ የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ ጥሪ ያቀርባል ” ሲሉ አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ በቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ ምንም አይነት ሽያጭ እንደማይከናውን አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል፣ “ አእላፋት ዝማሬ ነጭ ልብስ ልበሱ ” ተብሏል በሚል ነጭ ልብስ በተጋነነ ዋጋ የሚቸበችቡ ሁነቱን የተከተሉ ነጋዴዎች ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ነጭ ልብስ በውድ ወጋ እየተቸበቸበ ነው የሚል አስተያዬት እየተሰጠ ተስተውሏል፣ ለመርሀ ግብሩ ነጭ ልብስ ብቻ ለብሶ መምጣት ግዴታ ነው ? ሲል ለአዘጋጆቹ ጥያቄ አቅርቧል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ብንያም አሕመድ በሰጡት ምላሽም፣ “ ነጭ ልብስ የሌለን ያለንን ልብስ ንጹህ አድርገን እንምጣ። ዓላማችን ልብሱ ለመቁረቢያ እንዲሆን ነው ” ብለዋል።

“ ኦርቶዶክሳዊ ኢኮኖሚ እንዲፈጠር ይፈለጋል ግልጽ ነው። በዚህ ምክንያት ወደ ስራ የሚገቡ፣ ሥራቸውን የሚያስፋፉ፣ የሚለወጡ ኦርቶዶክሳዊያን ቢኖሩ ይሄ የማኀበራችን አንዱ ዓላማ ነው ” ሲሉ ነው የተናገሩት።

“ ስለዚህ ይህን በቀና ዓይን ነው የምናየው ” ያሉት አቶ ብንያም፣ “ በእርግጥ በዚሁ ምክንያት ደግሞ አጋጣሚውን የሚጠቀሙ፣ Accidental Entrprenuers የምንላቸው መጥተው ባለሃብት ለመሆን የሚጥሩ ይኖራሉ ” ሲሉም አክለዋል።

“ ልደቱ የሰዎች የመላክት ዝማሬ ነው። ስለዚህ ይህንን በማሰብ ነጭ ለብሰን እንመጣለን ” ብለው፣ “ ዘወትር ወደ ቤተ ክርስቲያን ስንሄድ የምናደርገው ነው፣ የተለዬ ነገር የለውም ” ነው ያሉት።

ሆኖም ነጭ ልብስ የሌላቸው ያላቸውን ልብስ በአግባቡ ለብሰው በዝማሬ መርሀ ግብሩ መገኘታቸው እንዳይዘነጋ መልዕክት ተላልፏል። 

ዝማሬው ዘማሪያን እየዘመሩ ምዕመናን የሚቀበሉበት ሂደት ሳይሆን ልደቱን በሚያወሱ ዝማሬዎች ሁሉም በጋራ ምስጋና እንዲያቀርብ መሆኑ ተሰምሮበታል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA










Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93419

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

'Wild West' If you initiate a Secret Chat, however, then these communications are end-to-end encrypted and are tied to the device you are using. That means it’s less convenient to access them across multiple platforms, but you are at far less risk of snooping. Back in the day, Secret Chats received some praise from the EFF, but the fact that its standard system isn’t as secure earned it some criticism. If you’re looking for something that is considered more reliable by privacy advocates, then Signal is the EFF’s preferred platform, although that too is not without some caveats. Unlike Silicon Valley giants such as Facebook and Twitter, which run very public anti-disinformation programs, Brooking said: "Telegram is famously lax or absent in its content moderation policy." Ukrainian forces successfully attacked Russian vehicles in the capital city of Kyiv thanks to a public tip made through the encrypted messaging app Telegram, Ukraine's top law-enforcement agency said on Tuesday. "He has kind of an old-school cyber-libertarian world view where technology is there to set you free," Maréchal said.
from ru


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American