Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 " ዩኒቨርሲቲያችን እንደ ሁሉም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም ነዉ " - የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ➡️ " ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እንዳንገባ ተደርገናል በዚህም ምክንያት በሁለት መስጊዶች ተጠልለን እንገኛለን " - ሙስሊም ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት የእስልምና እምነት ተከታይ / ሙስሊም…
#Update

“ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡

ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር።

ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ?

ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል።

" በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል።

በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡

በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡

የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ?

" በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡

በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡

አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡

የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል
" ብሏል፡፡

የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94118
Create:
Last Update:

#Update

“ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡

ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር።

ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ?

ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል።

" በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል።

በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡

በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡

የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ?

" በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡

በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡

አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡

የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል
" ብሏል፡፡

የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94118

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

At its heart, Telegram is little more than a messaging app like WhatsApp or Signal. But it also offers open channels that enable a single user, or a group of users, to communicate with large numbers in a method similar to a Twitter account. This has proven to be both a blessing and a curse for Telegram and its users, since these channels can be used for both good and ill. Right now, as Wired reports, the app is a key way for Ukrainians to receive updates from the government during the invasion. Emerson Brooking, a disinformation expert at the Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, said: "Back in the Wild West period of content moderation, like 2014 or 2015, maybe they could have gotten away with it, but it stands in marked contrast with how other companies run themselves today." False news often spreads via public groups, or chats, with potentially fatal effects. "There is a significant risk of insider threat or hacking of Telegram systems that could expose all of these chats to the Russian government," said Eva Galperin with the Electronic Frontier Foundation, which has called for Telegram to improve its privacy practices. And indeed, volatility has been a hallmark of the market environment so far in 2022, with the S&P 500 still down more than 10% for the year-to-date after first sliding into a correction last month. The CBOE Volatility Index, or VIX, has held at a lofty level of more than 30.
from ru


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American