Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94120-94121-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94120 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
“ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው ” - ጉዳዩን የሚከታተሉ አካል ለ1 ዓመት ከ5 ወር በእስራት ላይ የሚገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው አብረዋቸው ከነበሩት 41 እስረኞች ተለይተው “ ለሕይወታቸው አስጊ ወደሆነ ቦታ ” ለማዘወር ተገደዋል ይህ ደግሞ ጭንቀት ፈጥሮብናል…
“ ‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም ” - የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ

እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያለድ ትላንት የችሎት ቀጠሮ ነበራቸው።

ጉዳዩን የሚከታተሉ የቅርብ ሰዎች፣ “የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ነበር ትላንት ተዘጋጅተው የሄዱት ግን ያ ሳይሆን ቀርቷል” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በዝርዝር ምን አሉ ?

“ ትላንት ፍርድ ቤት የቀረቡት ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ክሱን አሻሽሎ ይቀርባል ተብሎ ስለተጠበቀ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ይሰጣሉ ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ሐምሌ 29/2016 ዓ/ም ላይ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ የስር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። ከዛ ‘አሻሽዬ አላቀርብም ብሎ ይግባኝ’ ብሎ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀረበ። 

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ የስር ፍርድ ቤቱ የወሰነው ትክክል ነው ብሎ ባለፈው ሐሙስ በድጋሚ ክሱን እንዲያሻሸል ትዕዛዝ ሰጥቶት ነበር። በዚያ መሠረት ትላንት አሻሽሎ መጥቶ የእምነት ክህደት ቃላተቸውን ይሰጣሉ፤ ክሱም ይሻሻላል ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ግን ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ አሻሽሎ አልመጣምና አሻሽሎ እንዲመጣ ብሎ ረዘም ያለ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር ፍርድ ቤቱ። ነገር ግን አቶ ዮሐንስና አቶ ክርስቲያን ባቀረቡት ጠንካራ ክርክር ምክንያት ክሱ ተሻሽሎ መጥቶ ለጥር 29 የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
" ብለዋል።

ስለትላንቱን የችሎት ውሎ ማብራሪያ የጠየቃቸው የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ፣ “ ከአራት ወራት በኋላ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማጽናት ነው ትላንት የቀረቡት ” ብለዋል።

“ ትላንትም ታግዶ የነበረው የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ተንቀሳቅሷል። ከዚህ በኋላ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ነው የሚሰጡት እርሱም ለጥር 29 ተቀጥሯል ” ነው ያሉት። 

እየ ክርስቲያን ትላንት የእምነት ክህደት ቃል አልሰጡም መባሉንና የጤንነታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የጠየቅናቸው ጠበቃቸው ምላሽ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

“ በስነ ስርዓት ህጉ መሠረት አንድ ለጊዜው የተዘጋ ፋይል መንቀሰቀስ አለበት፡፡ ከተንቀሳቀሰ በኋላ ነው ሌላው ሂደት የሚቀጥለው። በእለቱ መሆን ያለበት ፋይል ተንቀሳቅሶ ቀጠሮ መስጠት ነው እንጅ ሁለቱም አንድ ጊዜ አይታይም።

ስለዚህ እኛም ግልባጭ አምጥተን ከእግድም የተነሳ ነው በማለት ተዘግቶ የነበረው መዝገበ ተንቃሳቅሷል፡፡ ለእምነት ክህደት ቀጠሮ በማለት እንጅ በሌላ ምክንያት አይደለም።

ስለጤንነታቸውን በ6 እና በ3 ወራት የሚታወቅ ውጤት ስላለ ሙሉ ለሙሉ ተሸሏቸዋል ማለት አይቻለም፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ወደነበሩበት ሙሉ ጤና ተመልሰዋል ማለት አይቻልም ግን የህመም ስሜታቸው ቀንሷል”
  ብለዋል።

የፍርድ ሂደቱ በየወቅቱ እየተራዘመ ነው ያለው ፤ ታራሚዎቹም በህመም እየተሰቃዩ እንደሆነ በቤተሰቦቻቸው በተደጋጋሚ ተነግሯል ፤ የፍርድ ሂደቱ ምን መሆን ነበረበት ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

“ ተከሳሾቹም በችሎቱ የሚያነሱት ጉዳይ ነው፡፡ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ህገ መንግስታዊ መብት ነው ይሄ፡፡ ሕገ መንግስታዊ ብቻም ሳይሆን ዓለም ዓቀፋዊም መብት ነው፡።

‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም፡፡ 

ምንያቱም የሽብር ችሎት አንድ ችሎት ነው፡፡ ይሄ ችሎት ነው ከ10 ዓመታት በላይ መዝገብ ይዞ እያየ ያለው፡፡ በዳኞችም ሆነ በችሎቱ መፍረድ አይቻልም፡፡ የፍርድ ቤቱ የተለያዩ ችሎቶችን አለመመደብ ችግር ነው እንጂ የዳኞች ስራ አለመስራት ችግር አይደለም፡፡

ስለዚህ ትልቁ ችግር የችሎት ማነስ ነው፡፡ አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ የችሎት መታጠፍ አለ፡፡ ሦስት ችሎት ነበር ከዚህ በፊት። አሁን አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ በአንድ ችሎት ደግሞ ሊታይ አይችልም፡፡

ከዚያ ውጪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላይም ደግሞ 4፣ 5 ወራት ቆይቷል፡፡ የተጓደለ ፍትህ ፍትህ እንዳለማግኘት የሚቆጠር ነውና የፍትህ መዘግየት የፍትህን መጓደል የሚያሳይ ነው፡፡

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ 4፣ 5 ወራት ማቆየት አልነበረበትም፡፡ በተመሳሳይ ደግሞ በተመሳሳይ ጉዳይ፣ በተመሳሳይ መዝገብ የተወሰነ ውሳኔ አለ፡፡ ያ ውሳኔ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው የተወሰነው ይኼኛው ግን 4፣ 5 ወራት ነው የቆየው፡፡ አሁንም የፍትህ መዘግየት አለ።”

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94120
Create:
Last Update:

“ ‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም ” - የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ

እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያለድ ትላንት የችሎት ቀጠሮ ነበራቸው።

ጉዳዩን የሚከታተሉ የቅርብ ሰዎች፣ “የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ነበር ትላንት ተዘጋጅተው የሄዱት ግን ያ ሳይሆን ቀርቷል” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በዝርዝር ምን አሉ ?

“ ትላንት ፍርድ ቤት የቀረቡት ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ክሱን አሻሽሎ ይቀርባል ተብሎ ስለተጠበቀ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ይሰጣሉ ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ሐምሌ 29/2016 ዓ/ም ላይ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ የስር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። ከዛ ‘አሻሽዬ አላቀርብም ብሎ ይግባኝ’ ብሎ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀረበ። 

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ የስር ፍርድ ቤቱ የወሰነው ትክክል ነው ብሎ ባለፈው ሐሙስ በድጋሚ ክሱን እንዲያሻሸል ትዕዛዝ ሰጥቶት ነበር። በዚያ መሠረት ትላንት አሻሽሎ መጥቶ የእምነት ክህደት ቃላተቸውን ይሰጣሉ፤ ክሱም ይሻሻላል ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ግን ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ አሻሽሎ አልመጣምና አሻሽሎ እንዲመጣ ብሎ ረዘም ያለ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር ፍርድ ቤቱ። ነገር ግን አቶ ዮሐንስና አቶ ክርስቲያን ባቀረቡት ጠንካራ ክርክር ምክንያት ክሱ ተሻሽሎ መጥቶ ለጥር 29 የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
" ብለዋል።

ስለትላንቱን የችሎት ውሎ ማብራሪያ የጠየቃቸው የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ፣ “ ከአራት ወራት በኋላ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማጽናት ነው ትላንት የቀረቡት ” ብለዋል።

“ ትላንትም ታግዶ የነበረው የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ተንቀሳቅሷል። ከዚህ በኋላ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ነው የሚሰጡት እርሱም ለጥር 29 ተቀጥሯል ” ነው ያሉት። 

እየ ክርስቲያን ትላንት የእምነት ክህደት ቃል አልሰጡም መባሉንና የጤንነታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የጠየቅናቸው ጠበቃቸው ምላሽ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

“ በስነ ስርዓት ህጉ መሠረት አንድ ለጊዜው የተዘጋ ፋይል መንቀሰቀስ አለበት፡፡ ከተንቀሳቀሰ በኋላ ነው ሌላው ሂደት የሚቀጥለው። በእለቱ መሆን ያለበት ፋይል ተንቀሳቅሶ ቀጠሮ መስጠት ነው እንጅ ሁለቱም አንድ ጊዜ አይታይም።

ስለዚህ እኛም ግልባጭ አምጥተን ከእግድም የተነሳ ነው በማለት ተዘግቶ የነበረው መዝገበ ተንቃሳቅሷል፡፡ ለእምነት ክህደት ቀጠሮ በማለት እንጅ በሌላ ምክንያት አይደለም።

ስለጤንነታቸውን በ6 እና በ3 ወራት የሚታወቅ ውጤት ስላለ ሙሉ ለሙሉ ተሸሏቸዋል ማለት አይቻለም፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ወደነበሩበት ሙሉ ጤና ተመልሰዋል ማለት አይቻልም ግን የህመም ስሜታቸው ቀንሷል”
  ብለዋል።

የፍርድ ሂደቱ በየወቅቱ እየተራዘመ ነው ያለው ፤ ታራሚዎቹም በህመም እየተሰቃዩ እንደሆነ በቤተሰቦቻቸው በተደጋጋሚ ተነግሯል ፤ የፍርድ ሂደቱ ምን መሆን ነበረበት ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

“ ተከሳሾቹም በችሎቱ የሚያነሱት ጉዳይ ነው፡፡ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ህገ መንግስታዊ መብት ነው ይሄ፡፡ ሕገ መንግስታዊ ብቻም ሳይሆን ዓለም ዓቀፋዊም መብት ነው፡።

‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም፡፡ 

ምንያቱም የሽብር ችሎት አንድ ችሎት ነው፡፡ ይሄ ችሎት ነው ከ10 ዓመታት በላይ መዝገብ ይዞ እያየ ያለው፡፡ በዳኞችም ሆነ በችሎቱ መፍረድ አይቻልም፡፡ የፍርድ ቤቱ የተለያዩ ችሎቶችን አለመመደብ ችግር ነው እንጂ የዳኞች ስራ አለመስራት ችግር አይደለም፡፡

ስለዚህ ትልቁ ችግር የችሎት ማነስ ነው፡፡ አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ የችሎት መታጠፍ አለ፡፡ ሦስት ችሎት ነበር ከዚህ በፊት። አሁን አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ በአንድ ችሎት ደግሞ ሊታይ አይችልም፡፡

ከዚያ ውጪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላይም ደግሞ 4፣ 5 ወራት ቆይቷል፡፡ የተጓደለ ፍትህ ፍትህ እንዳለማግኘት የሚቆጠር ነውና የፍትህ መዘግየት የፍትህን መጓደል የሚያሳይ ነው፡፡

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ 4፣ 5 ወራት ማቆየት አልነበረበትም፡፡ በተመሳሳይ ደግሞ በተመሳሳይ ጉዳይ፣ በተመሳሳይ መዝገብ የተወሰነ ውሳኔ አለ፡፡ ያ ውሳኔ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው የተወሰነው ይኼኛው ግን 4፣ 5 ወራት ነው የቆየው፡፡ አሁንም የፍትህ መዘግየት አለ።”

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94120

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

You may recall that, back when Facebook started changing WhatsApp’s terms of service, a number of news outlets reported on, and even recommended, switching to Telegram. Pavel Durov even said that users should delete WhatsApp “unless you are cool with all of your photos and messages becoming public one day.” But Telegram can’t be described as a more-secure version of WhatsApp. Pavel Durov, Telegram's CEO, is known as "the Russian Mark Zuckerberg," for co-founding VKontakte, which is Russian for "in touch," a Facebook imitator that became the country's most popular social networking site. For example, WhatsApp restricted the number of times a user could forward something, and developed automated systems that detect and flag objectionable content. I want a secure messaging app, should I use Telegram? "For Telegram, accountability has always been a problem, which is why it was so popular even before the full-scale war with far-right extremists and terrorists from all over the world," she told AFP from her safe house outside the Ukrainian capital.
from ru


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American