Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94120-94121-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94121 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
“ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው ” - ጉዳዩን የሚከታተሉ አካል ለ1 ዓመት ከ5 ወር በእስራት ላይ የሚገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው አብረዋቸው ከነበሩት 41 እስረኞች ተለይተው “ ለሕይወታቸው አስጊ ወደሆነ ቦታ ” ለማዘወር ተገደዋል ይህ ደግሞ ጭንቀት ፈጥሮብናል…
“ ‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም ” - የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ

እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያለድ ትላንት የችሎት ቀጠሮ ነበራቸው።

ጉዳዩን የሚከታተሉ የቅርብ ሰዎች፣ “የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ነበር ትላንት ተዘጋጅተው የሄዱት ግን ያ ሳይሆን ቀርቷል” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በዝርዝር ምን አሉ ?

“ ትላንት ፍርድ ቤት የቀረቡት ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ክሱን አሻሽሎ ይቀርባል ተብሎ ስለተጠበቀ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ይሰጣሉ ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ሐምሌ 29/2016 ዓ/ም ላይ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ የስር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። ከዛ ‘አሻሽዬ አላቀርብም ብሎ ይግባኝ’ ብሎ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀረበ። 

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ የስር ፍርድ ቤቱ የወሰነው ትክክል ነው ብሎ ባለፈው ሐሙስ በድጋሚ ክሱን እንዲያሻሸል ትዕዛዝ ሰጥቶት ነበር። በዚያ መሠረት ትላንት አሻሽሎ መጥቶ የእምነት ክህደት ቃላተቸውን ይሰጣሉ፤ ክሱም ይሻሻላል ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ግን ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ አሻሽሎ አልመጣምና አሻሽሎ እንዲመጣ ብሎ ረዘም ያለ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር ፍርድ ቤቱ። ነገር ግን አቶ ዮሐንስና አቶ ክርስቲያን ባቀረቡት ጠንካራ ክርክር ምክንያት ክሱ ተሻሽሎ መጥቶ ለጥር 29 የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
" ብለዋል።

ስለትላንቱን የችሎት ውሎ ማብራሪያ የጠየቃቸው የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ፣ “ ከአራት ወራት በኋላ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማጽናት ነው ትላንት የቀረቡት ” ብለዋል።

“ ትላንትም ታግዶ የነበረው የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ተንቀሳቅሷል። ከዚህ በኋላ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ነው የሚሰጡት እርሱም ለጥር 29 ተቀጥሯል ” ነው ያሉት። 

እየ ክርስቲያን ትላንት የእምነት ክህደት ቃል አልሰጡም መባሉንና የጤንነታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የጠየቅናቸው ጠበቃቸው ምላሽ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

“ በስነ ስርዓት ህጉ መሠረት አንድ ለጊዜው የተዘጋ ፋይል መንቀሰቀስ አለበት፡፡ ከተንቀሳቀሰ በኋላ ነው ሌላው ሂደት የሚቀጥለው። በእለቱ መሆን ያለበት ፋይል ተንቀሳቅሶ ቀጠሮ መስጠት ነው እንጅ ሁለቱም አንድ ጊዜ አይታይም።

ስለዚህ እኛም ግልባጭ አምጥተን ከእግድም የተነሳ ነው በማለት ተዘግቶ የነበረው መዝገበ ተንቃሳቅሷል፡፡ ለእምነት ክህደት ቀጠሮ በማለት እንጅ በሌላ ምክንያት አይደለም።

ስለጤንነታቸውን በ6 እና በ3 ወራት የሚታወቅ ውጤት ስላለ ሙሉ ለሙሉ ተሸሏቸዋል ማለት አይቻለም፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ወደነበሩበት ሙሉ ጤና ተመልሰዋል ማለት አይቻልም ግን የህመም ስሜታቸው ቀንሷል”
  ብለዋል።

የፍርድ ሂደቱ በየወቅቱ እየተራዘመ ነው ያለው ፤ ታራሚዎቹም በህመም እየተሰቃዩ እንደሆነ በቤተሰቦቻቸው በተደጋጋሚ ተነግሯል ፤ የፍርድ ሂደቱ ምን መሆን ነበረበት ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

“ ተከሳሾቹም በችሎቱ የሚያነሱት ጉዳይ ነው፡፡ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ህገ መንግስታዊ መብት ነው ይሄ፡፡ ሕገ መንግስታዊ ብቻም ሳይሆን ዓለም ዓቀፋዊም መብት ነው፡።

‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም፡፡ 

ምንያቱም የሽብር ችሎት አንድ ችሎት ነው፡፡ ይሄ ችሎት ነው ከ10 ዓመታት በላይ መዝገብ ይዞ እያየ ያለው፡፡ በዳኞችም ሆነ በችሎቱ መፍረድ አይቻልም፡፡ የፍርድ ቤቱ የተለያዩ ችሎቶችን አለመመደብ ችግር ነው እንጂ የዳኞች ስራ አለመስራት ችግር አይደለም፡፡

ስለዚህ ትልቁ ችግር የችሎት ማነስ ነው፡፡ አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ የችሎት መታጠፍ አለ፡፡ ሦስት ችሎት ነበር ከዚህ በፊት። አሁን አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ በአንድ ችሎት ደግሞ ሊታይ አይችልም፡፡

ከዚያ ውጪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላይም ደግሞ 4፣ 5 ወራት ቆይቷል፡፡ የተጓደለ ፍትህ ፍትህ እንዳለማግኘት የሚቆጠር ነውና የፍትህ መዘግየት የፍትህን መጓደል የሚያሳይ ነው፡፡

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ 4፣ 5 ወራት ማቆየት አልነበረበትም፡፡ በተመሳሳይ ደግሞ በተመሳሳይ ጉዳይ፣ በተመሳሳይ መዝገብ የተወሰነ ውሳኔ አለ፡፡ ያ ውሳኔ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው የተወሰነው ይኼኛው ግን 4፣ 5 ወራት ነው የቆየው፡፡ አሁንም የፍትህ መዘግየት አለ።”

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94121
Create:
Last Update:

“ ‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም ” - የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ

እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያለድ ትላንት የችሎት ቀጠሮ ነበራቸው።

ጉዳዩን የሚከታተሉ የቅርብ ሰዎች፣ “የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ነበር ትላንት ተዘጋጅተው የሄዱት ግን ያ ሳይሆን ቀርቷል” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በዝርዝር ምን አሉ ?

“ ትላንት ፍርድ ቤት የቀረቡት ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ክሱን አሻሽሎ ይቀርባል ተብሎ ስለተጠበቀ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ይሰጣሉ ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ሐምሌ 29/2016 ዓ/ም ላይ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ የስር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። ከዛ ‘አሻሽዬ አላቀርብም ብሎ ይግባኝ’ ብሎ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀረበ። 

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ የስር ፍርድ ቤቱ የወሰነው ትክክል ነው ብሎ ባለፈው ሐሙስ በድጋሚ ክሱን እንዲያሻሸል ትዕዛዝ ሰጥቶት ነበር። በዚያ መሠረት ትላንት አሻሽሎ መጥቶ የእምነት ክህደት ቃላተቸውን ይሰጣሉ፤ ክሱም ይሻሻላል ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ግን ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ አሻሽሎ አልመጣምና አሻሽሎ እንዲመጣ ብሎ ረዘም ያለ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር ፍርድ ቤቱ። ነገር ግን አቶ ዮሐንስና አቶ ክርስቲያን ባቀረቡት ጠንካራ ክርክር ምክንያት ክሱ ተሻሽሎ መጥቶ ለጥር 29 የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
" ብለዋል።

ስለትላንቱን የችሎት ውሎ ማብራሪያ የጠየቃቸው የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ፣ “ ከአራት ወራት በኋላ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማጽናት ነው ትላንት የቀረቡት ” ብለዋል።

“ ትላንትም ታግዶ የነበረው የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ተንቀሳቅሷል። ከዚህ በኋላ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ነው የሚሰጡት እርሱም ለጥር 29 ተቀጥሯል ” ነው ያሉት። 

እየ ክርስቲያን ትላንት የእምነት ክህደት ቃል አልሰጡም መባሉንና የጤንነታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የጠየቅናቸው ጠበቃቸው ምላሽ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

“ በስነ ስርዓት ህጉ መሠረት አንድ ለጊዜው የተዘጋ ፋይል መንቀሰቀስ አለበት፡፡ ከተንቀሳቀሰ በኋላ ነው ሌላው ሂደት የሚቀጥለው። በእለቱ መሆን ያለበት ፋይል ተንቀሳቅሶ ቀጠሮ መስጠት ነው እንጅ ሁለቱም አንድ ጊዜ አይታይም።

ስለዚህ እኛም ግልባጭ አምጥተን ከእግድም የተነሳ ነው በማለት ተዘግቶ የነበረው መዝገበ ተንቃሳቅሷል፡፡ ለእምነት ክህደት ቀጠሮ በማለት እንጅ በሌላ ምክንያት አይደለም።

ስለጤንነታቸውን በ6 እና በ3 ወራት የሚታወቅ ውጤት ስላለ ሙሉ ለሙሉ ተሸሏቸዋል ማለት አይቻለም፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ወደነበሩበት ሙሉ ጤና ተመልሰዋል ማለት አይቻልም ግን የህመም ስሜታቸው ቀንሷል”
  ብለዋል።

የፍርድ ሂደቱ በየወቅቱ እየተራዘመ ነው ያለው ፤ ታራሚዎቹም በህመም እየተሰቃዩ እንደሆነ በቤተሰቦቻቸው በተደጋጋሚ ተነግሯል ፤ የፍርድ ሂደቱ ምን መሆን ነበረበት ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

“ ተከሳሾቹም በችሎቱ የሚያነሱት ጉዳይ ነው፡፡ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ህገ መንግስታዊ መብት ነው ይሄ፡፡ ሕገ መንግስታዊ ብቻም ሳይሆን ዓለም ዓቀፋዊም መብት ነው፡።

‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም፡፡ 

ምንያቱም የሽብር ችሎት አንድ ችሎት ነው፡፡ ይሄ ችሎት ነው ከ10 ዓመታት በላይ መዝገብ ይዞ እያየ ያለው፡፡ በዳኞችም ሆነ በችሎቱ መፍረድ አይቻልም፡፡ የፍርድ ቤቱ የተለያዩ ችሎቶችን አለመመደብ ችግር ነው እንጂ የዳኞች ስራ አለመስራት ችግር አይደለም፡፡

ስለዚህ ትልቁ ችግር የችሎት ማነስ ነው፡፡ አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ የችሎት መታጠፍ አለ፡፡ ሦስት ችሎት ነበር ከዚህ በፊት። አሁን አንድ ችሎት ብቻ ነው ያለው፡፡ በአንድ ችሎት ደግሞ ሊታይ አይችልም፡፡

ከዚያ ውጪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ላይም ደግሞ 4፣ 5 ወራት ቆይቷል፡፡ የተጓደለ ፍትህ ፍትህ እንዳለማግኘት የሚቆጠር ነውና የፍትህ መዘግየት የፍትህን መጓደል የሚያሳይ ነው፡፡

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ 4፣ 5 ወራት ማቆየት አልነበረበትም፡፡ በተመሳሳይ ደግሞ በተመሳሳይ ጉዳይ፣ በተመሳሳይ መዝገብ የተወሰነ ውሳኔ አለ፡፡ ያ ውሳኔ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው የተወሰነው ይኼኛው ግን 4፣ 5 ወራት ነው የቆየው፡፡ አሁንም የፍትህ መዘግየት አለ።”

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94121

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Ukrainian President Volodymyr Zelensky said in a video message on Tuesday that Ukrainian forces "destroy the invaders wherever we can." On December 23rd, 2020, Pavel Durov posted to his channel that the company would need to start generating revenue. In early 2021, he added that any advertising on the platform would not use user data for targeting, and that it would be focused on “large one-to-many channels.” He pledged that ads would be “non-intrusive” and that most users would simply not notice any change. Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more. He adds: "Telegram has become my primary news source." On February 27th, Durov posted that Channels were becoming a source of unverified information and that the company lacks the ability to check on their veracity. He urged users to be mistrustful of the things shared on Channels, and initially threatened to block the feature in the countries involved for the length of the war, saying that he didn’t want Telegram to be used to aggravate conflict or incite ethnic hatred. He did, however, walk back this plan when it became clear that they had also become a vital communications tool for Ukrainian officials and citizens to help coordinate their resistance and evacuations.
from ru


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American