Telegram Group & Telegram Channel
ትልቅነቴን ያየሁበትን ቀን መቼም አልረሳውም።ከኋላ የሚከተለኝ ጥላ ከቁመቴ በላይ ግዙፍ ነው። በብርሃን ውስጥ ራሴን የፈለግኩበትን ዘመን ረገምኩት። ለካስ በባትሪ የሚፈለገው ነው ዕንቁ . . . የቀን የቀኑማ ተመሳስሎ የተሰደረ ብረት ብቻ!

'ፅልማሞት' እወዳለሁ። 'ፅልም ያኮስ' እቅፍ ውስጥ ድብቅ ስል ነገር አለሜን እረሳለው። ሊጠፋ ባቆበቆበው ብርሃን የጠቆረው ጥላዬ ከእኔነቴ ገዝፎ ሳየው አሸናፊነት ይሰማኛል።

''መማፀኛ ከተማዬ'' ነው። ነፍስ አጥፍቶ ከደም ተበቃይ የሚሸሽ ሰውን ይመስል ውሽቅ የምልበት 'ቤቴ' . . . በብርሃን ቢገለጥ የሚሰነፍጠውን ሕይወቴን ሸሽቼ የምሸሸግበት ከተማ. . . በድንግዝግዝ ስራመድ ሁሉም መንገድ መዳረሻ፣ ከገንቦ ጠብታ የማልቆጠረውን የኢያሪኮን ሞገስ የሚሰጥ፣ ኃጢአቴ ህያው የማይሆንበት ለኔ እንደ እናት ቤት የሚሞቅ ድሎቴ ነው።

አዎ! 'ጨለማ' እወዳለሁ! 'ሆድና ጀርባ' የሆነውን ማንነቴን ያስታርቅልኛል። 'እየተልመዘመዘ' የሚያስቸግረኝን እኔነቴን 'አደብ' ያስገዛልኛል።

'ፅልመትን' በመገኘቴ ስደምረው <ሽንተ መልካም> የሆንኩ ያህል እከበባለሁ። 'ቅርሽም' ያለው ነገዬ ይጠገናል። 'እየበተበተ' ያለቀው ትላንትናዬ ይፈካል።

'ከከቸችኩ' ሰንብቻለው! ድኩሙ ጉልበቴ ለእርምጃ አሻፈረኝ ብሎኛል። እንደ አረረ ወጥ 'የጎረናው' ስሜ ከሽታው በላይ ጣዕሙ መንችኮብኛል። እከሊት 'ደሰቃም' ናት የሚል ስያሜ ከተሰጠኝ ውሎ አድሯል። ይታወቀኛል። አውቀዋለሁ. . . የኔ ማንነት እሱ ነው <ሀገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው!>

ግን እኮ .... እኔ'ኮ <<ፅላቱ>> ነኝ ለ. . . 'ፅልመት'። ለጥልም ያ'ኮስ ጥሞናው፣ የብርሃንነቴ ፅህፈት ማንፀባረቂያው ነኝ። ጨለማ ውስጥ ለሚያየኝ ኔፍሊም!

ለዛ'ም ነው ጨለማን የምወደው. . . ድቅድቅ ውስጥ የምሸሸገው! . . . ቀን ያጨመተረውን፣ ጭምግግ፣ ጥፍግግ አድርጎ ያሰረውን እኔ'ነቴን የማታ ፅህፈት ስለሚያነፃኝ! ለዛ'ም ነው ጥልመት የምናፍቀው ለዚህም ነው በእሱ የምኖረው!

'አርነቴ' ነው! ያረጀ ያፈጀ ተረታ ተረቶችን የምረሳበት በውስጡ ራ'ሴን ሳየሁ ምሉዕነቴ የሚያሳብቅብኝ!
አርያም ተስፋዬ (2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/114
Create:
Last Update:

ትልቅነቴን ያየሁበትን ቀን መቼም አልረሳውም።ከኋላ የሚከተለኝ ጥላ ከቁመቴ በላይ ግዙፍ ነው። በብርሃን ውስጥ ራሴን የፈለግኩበትን ዘመን ረገምኩት። ለካስ በባትሪ የሚፈለገው ነው ዕንቁ . . . የቀን የቀኑማ ተመሳስሎ የተሰደረ ብረት ብቻ!

'ፅልማሞት' እወዳለሁ። 'ፅልም ያኮስ' እቅፍ ውስጥ ድብቅ ስል ነገር አለሜን እረሳለው። ሊጠፋ ባቆበቆበው ብርሃን የጠቆረው ጥላዬ ከእኔነቴ ገዝፎ ሳየው አሸናፊነት ይሰማኛል።

''መማፀኛ ከተማዬ'' ነው። ነፍስ አጥፍቶ ከደም ተበቃይ የሚሸሽ ሰውን ይመስል ውሽቅ የምልበት 'ቤቴ' . . . በብርሃን ቢገለጥ የሚሰነፍጠውን ሕይወቴን ሸሽቼ የምሸሸግበት ከተማ. . . በድንግዝግዝ ስራመድ ሁሉም መንገድ መዳረሻ፣ ከገንቦ ጠብታ የማልቆጠረውን የኢያሪኮን ሞገስ የሚሰጥ፣ ኃጢአቴ ህያው የማይሆንበት ለኔ እንደ እናት ቤት የሚሞቅ ድሎቴ ነው።

አዎ! 'ጨለማ' እወዳለሁ! 'ሆድና ጀርባ' የሆነውን ማንነቴን ያስታርቅልኛል። 'እየተልመዘመዘ' የሚያስቸግረኝን እኔነቴን 'አደብ' ያስገዛልኛል።

'ፅልመትን' በመገኘቴ ስደምረው <ሽንተ መልካም> የሆንኩ ያህል እከበባለሁ። 'ቅርሽም' ያለው ነገዬ ይጠገናል። 'እየበተበተ' ያለቀው ትላንትናዬ ይፈካል።

'ከከቸችኩ' ሰንብቻለው! ድኩሙ ጉልበቴ ለእርምጃ አሻፈረኝ ብሎኛል። እንደ አረረ ወጥ 'የጎረናው' ስሜ ከሽታው በላይ ጣዕሙ መንችኮብኛል። እከሊት 'ደሰቃም' ናት የሚል ስያሜ ከተሰጠኝ ውሎ አድሯል። ይታወቀኛል። አውቀዋለሁ. . . የኔ ማንነት እሱ ነው <ሀገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው!>

ግን እኮ .... እኔ'ኮ <<ፅላቱ>> ነኝ ለ. . . 'ፅልመት'። ለጥልም ያ'ኮስ ጥሞናው፣ የብርሃንነቴ ፅህፈት ማንፀባረቂያው ነኝ። ጨለማ ውስጥ ለሚያየኝ ኔፍሊም!

ለዛ'ም ነው ጨለማን የምወደው. . . ድቅድቅ ውስጥ የምሸሸገው! . . . ቀን ያጨመተረውን፣ ጭምግግ፣ ጥፍግግ አድርጎ ያሰረውን እኔ'ነቴን የማታ ፅህፈት ስለሚያነፃኝ! ለዛ'ም ነው ጥልመት የምናፍቀው ለዚህም ነው በእሱ የምኖረው!

'አርነቴ' ነው! ያረጀ ያፈጀ ተረታ ተረቶችን የምረሳበት በውስጡ ራ'ሴን ሳየሁ ምሉዕነቴ የሚያሳብቅብኝ!
አርያም ተስፋዬ (2013)

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/114

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram does offer end-to-end encrypted communications through Secret Chats, but this is not the default setting. Standard conversations use the MTProto method, enabling server-client encryption but with them stored on the server for ease-of-access. This makes using Telegram across multiple devices simple, but also means that the regular Telegram chats you’re having with folks are not as secure as you may believe. "Like the bombing of the maternity ward in Mariupol," he said, "Even before it hits the news, you see the videos on the Telegram channels." On December 23rd, 2020, Pavel Durov posted to his channel that the company would need to start generating revenue. In early 2021, he added that any advertising on the platform would not use user data for targeting, and that it would be focused on “large one-to-many channels.” He pledged that ads would be “non-intrusive” and that most users would simply not notice any change. Additionally, investors are often instructed to deposit monies into personal bank accounts of individuals who claim to represent a legitimate entity, and/or into an unrelated corporate account. To lend credence and to lure unsuspecting victims, perpetrators usually claim that their entity and/or the investment schemes are approved by financial authorities. In addition, Telegram's architecture limits the ability to slow the spread of false information: the lack of a central public feed, and the fact that comments are easily disabled in channels, reduce the space for public pushback.
from ru


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American