Telegram Group & Telegram Channel
<ቅናተኛ> ነኝ! በተለይ በእሷማ ቀናለሁ!

የዕድሜ'ዬን ግማሽ የኖርኩት እሷን 'ልመስል' ስፅፍ ሳጠፋ ነው። ግን እሷን 'መሆን' አልቻልኩም።

የመሰልኩ በመሰለኝ ሰአትም ፊቱ ስቆም ከሙሉዕነቴ ይልቅ ባዶነቴ ያሳብቅብኛል።

ፈት ነኝ! አምስቴ አግብቼ ፈትቻለው። ያፈገገልኝ ሁሉ ጓዶሎዬን መሙያ እየመሰለኝ ከመኝታ ለመሰየም ቀናት አይፈጅብኝም።

. . .እሷን ግን መሆን አልቻልኩም።

ራሴው ለገፋውት አጨብጫቢ እሻለው፣ ያላከበርኩትን ክብር እንዲከብር ስንቴ ጠብቄሃለሁ ግን እንኳን መሆን መምሰል ራሱ አልቻልኩም።

መቼ'ለት ነው . . . ወግ ማዕረግ በደምግባት አገኝ ብዬ ከአንዱ ልባም ተጠጋው....ምን ዋጋ አለው? ፈጣሪን አለመፍራቴ አይሎብኝ "ውበት ሀሰት ነው" ብሎ ተረተብኝ።

ያቺ አጥንቴ የነቀዘላት ሴት ግን የከበረች፣ በጎዳና ከመታየት ይልቅ በጓዳዋ የተሸሸገች ናት።

. . .አንድ ባል ነው ያላት እንደ ንጉስ ያከበረችው ከመኳንንት ጋር ሲቀመጥ 'ፐ'! ሞገስስ በሱ ቀረ የሚባልላት!

ከመስታዎቴ ቆሜ ገፄ ላይ እሷን ስስል ውዬ አድራለው። የኀላ ኀላ አለመሆኔ ጎልቶ ከወደ ህሊናዬ ያንቧርቅብኛል።

'ራስን መሆን' የሚባል መድኃኒት አለ። በሌላ መስታዎት ራሴን ለማየት ስፍጨረጨር ለካስ የማላድን መድኃኒተኛ ኖሬያለሁ። ፍለጋዬን አስተካክያለው "በአንዱ ቀመር የሌላው ስሌት አይሰራም!"

አሁን የተስፋ ጭላንጭል አለኝ። እኔ ውስጥ እሷን ከመፈለግ የሚልቀው እኔነቴ ጥልቀት እኔን መፈለጉ ነው። ምን አልባት መሲሁ ይመጣ ይሆናል። ጉዴን ነግሮ በፃፈለኝ ማንነት ሌላውን እሆን ብዬ የሰረዝኩ የደለዝኩትን ሽሮ በራስን መሆን ባህር ዳግም ካጠመቀኝ... እጠብቃለው!

እስከዚያው ግን:
የማያቋርጥ ጠፈጠፍ፣ በዝናብ ጊዜ የሚያፈስ ቤት የሚመስለውን አመሌን ይዤ ወጣለው። 'አእምሮ የጎደለው' አገኝ ይሆን ብዬ... 'ከአላዋቂዎች' መካከል ልዝብ አንደበቴን ሰምቶ የሚሳብ ልቦናዬን በጌጤ የመዘነ አይጠፋምና።

አርያም ተስፋዬ(2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/118
Create:
Last Update:

<ቅናተኛ> ነኝ! በተለይ በእሷማ ቀናለሁ!

የዕድሜ'ዬን ግማሽ የኖርኩት እሷን 'ልመስል' ስፅፍ ሳጠፋ ነው። ግን እሷን 'መሆን' አልቻልኩም።

የመሰልኩ በመሰለኝ ሰአትም ፊቱ ስቆም ከሙሉዕነቴ ይልቅ ባዶነቴ ያሳብቅብኛል።

ፈት ነኝ! አምስቴ አግብቼ ፈትቻለው። ያፈገገልኝ ሁሉ ጓዶሎዬን መሙያ እየመሰለኝ ከመኝታ ለመሰየም ቀናት አይፈጅብኝም።

. . .እሷን ግን መሆን አልቻልኩም።

ራሴው ለገፋውት አጨብጫቢ እሻለው፣ ያላከበርኩትን ክብር እንዲከብር ስንቴ ጠብቄሃለሁ ግን እንኳን መሆን መምሰል ራሱ አልቻልኩም።

መቼ'ለት ነው . . . ወግ ማዕረግ በደምግባት አገኝ ብዬ ከአንዱ ልባም ተጠጋው....ምን ዋጋ አለው? ፈጣሪን አለመፍራቴ አይሎብኝ "ውበት ሀሰት ነው" ብሎ ተረተብኝ።

ያቺ አጥንቴ የነቀዘላት ሴት ግን የከበረች፣ በጎዳና ከመታየት ይልቅ በጓዳዋ የተሸሸገች ናት።

. . .አንድ ባል ነው ያላት እንደ ንጉስ ያከበረችው ከመኳንንት ጋር ሲቀመጥ 'ፐ'! ሞገስስ በሱ ቀረ የሚባልላት!

ከመስታዎቴ ቆሜ ገፄ ላይ እሷን ስስል ውዬ አድራለው። የኀላ ኀላ አለመሆኔ ጎልቶ ከወደ ህሊናዬ ያንቧርቅብኛል።

'ራስን መሆን' የሚባል መድኃኒት አለ። በሌላ መስታዎት ራሴን ለማየት ስፍጨረጨር ለካስ የማላድን መድኃኒተኛ ኖሬያለሁ። ፍለጋዬን አስተካክያለው "በአንዱ ቀመር የሌላው ስሌት አይሰራም!"

አሁን የተስፋ ጭላንጭል አለኝ። እኔ ውስጥ እሷን ከመፈለግ የሚልቀው እኔነቴ ጥልቀት እኔን መፈለጉ ነው። ምን አልባት መሲሁ ይመጣ ይሆናል። ጉዴን ነግሮ በፃፈለኝ ማንነት ሌላውን እሆን ብዬ የሰረዝኩ የደለዝኩትን ሽሮ በራስን መሆን ባህር ዳግም ካጠመቀኝ... እጠብቃለው!

እስከዚያው ግን:
የማያቋርጥ ጠፈጠፍ፣ በዝናብ ጊዜ የሚያፈስ ቤት የሚመስለውን አመሌን ይዤ ወጣለው። 'አእምሮ የጎደለው' አገኝ ይሆን ብዬ... 'ከአላዋቂዎች' መካከል ልዝብ አንደበቴን ሰምቶ የሚሳብ ልቦናዬን በጌጤ የመዘነ አይጠፋምና።

አርያም ተስፋዬ(2013)

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/118

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Russians and Ukrainians are both prolific users of Telegram. They rely on the app for channels that act as newsfeeds, group chats (both public and private), and one-to-one communication. Since the Russian invasion of Ukraine, Telegram has remained an important lifeline for both Russians and Ukrainians, as a way of staying aware of the latest news and keeping in touch with loved ones. On December 23rd, 2020, Pavel Durov posted to his channel that the company would need to start generating revenue. In early 2021, he added that any advertising on the platform would not use user data for targeting, and that it would be focused on “large one-to-many channels.” He pledged that ads would be “non-intrusive” and that most users would simply not notice any change. Groups are also not fully encrypted, end-to-end. This includes private groups. Private groups cannot be seen by other Telegram users, but Telegram itself can see the groups and all of the communications that you have in them. All of the same risks and warnings about channels can be applied to groups. Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more.
from ru


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American