Telegram Group & Telegram Channel
ትልቅነቴን ያየሁበትን ቀን መቼም አልረሳውም።ከኋላ የሚከተለኝ ጥላ ከቁመቴ በላይ ግዙፍ ነው። በብርሃን ውስጥ ራሴን የፈለግኩበትን ዘመን ረገምኩት። ለካስ በባትሪ የሚፈለገው ነው ዕንቁ . . . የቀን የቀኑማ ተመሳስሎ የተሰደረ ብረት ብቻ!

'ፅልማሞት' እወዳለሁ። 'ፅልም ያኮስ' እቅፍ ውስጥ ድብቅ ስል ነገር አለሜን እረሳለው። ሊጠፋ ባቆበቆበው ብርሃን የጠቆረው ጥላዬ ከእኔነቴ ገዝፎ ሳየው አሸናፊነት ይሰማኛል።

''መማፀኛ ከተማዬ'' ነው። ነፍስ አጥፍቶ ከደም ተበቃይ የሚሸሽ ሰውን ይመስል ውሽቅ የምልበት 'ቤቴ' . . . በብርሃን ቢገለጥ የሚሰነፍጠውን ሕይወቴን ሸሽቼ የምሸሸግበት ከተማ. . . በድንግዝግዝ ስራመድ ሁሉም መንገድ መዳረሻ፣ ከገንቦ ጠብታ የማልቆጠረውን የኢያሪኮን ሞገስ የሚሰጥ፣ ኃጢአቴ ህያው የማይሆንበት ለኔ እንደ እናት ቤት የሚሞቅ ድሎቴ ነው።

አዎ! 'ጨለማ' እወዳለሁ! 'ሆድና ጀርባ' የሆነውን ማንነቴን ያስታርቅልኛል። 'እየተልመዘመዘ' የሚያስቸግረኝን እኔነቴን 'አደብ' ያስገዛልኛል።

'ፅልመትን' በመገኘቴ ስደምረው <ሽንተ መልካም> የሆንኩ ያህል እከበባለሁ። 'ቅርሽም' ያለው ነገዬ ይጠገናል። 'እየበተበተ' ያለቀው ትላንትናዬ ይፈካል።

'ከከቸችኩ' ሰንብቻለው! ድኩሙ ጉልበቴ ለእርምጃ አሻፈረኝ ብሎኛል። እንደ አረረ ወጥ 'የጎረናው' ስሜ ከሽታው በላይ ጣዕሙ መንችኮብኛል። እከሊት 'ደሰቃም' ናት የሚል ስያሜ ከተሰጠኝ ውሎ አድሯል። ይታወቀኛል። አውቀዋለሁ. . . የኔ ማንነት እሱ ነው <ሀገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው!>

ግን እኮ .... እኔ'ኮ <<ፅላቱ>> ነኝ ለ. . . 'ፅልመት'። ለጥልም ያ'ኮስ ጥሞናው፣ የብርሃንነቴ ፅህፈት ማንፀባረቂያው ነኝ። ጨለማ ውስጥ ለሚያየኝ ኔፍሊም!

ለዛ'ም ነው ጨለማን የምወደው. . . ድቅድቅ ውስጥ የምሸሸገው! . . . ቀን ያጨመተረውን፣ ጭምግግ፣ ጥፍግግ አድርጎ ያሰረውን እኔ'ነቴን የማታ ፅህፈት ስለሚያነፃኝ! ለዛ'ም ነው ጥልመት የምናፍቀው ለዚህም ነው በእሱ የምኖረው!

'አርነቴ' ነው! ያረጀ ያፈጀ ተረታ ተረቶችን የምረሳበት በውስጡ ራ'ሴን ሳየሁ ምሉዕነቴ የሚያሳብቅብኝ!
አርያም ተስፋዬ (2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/114
Create:
Last Update:

ትልቅነቴን ያየሁበትን ቀን መቼም አልረሳውም።ከኋላ የሚከተለኝ ጥላ ከቁመቴ በላይ ግዙፍ ነው። በብርሃን ውስጥ ራሴን የፈለግኩበትን ዘመን ረገምኩት። ለካስ በባትሪ የሚፈለገው ነው ዕንቁ . . . የቀን የቀኑማ ተመሳስሎ የተሰደረ ብረት ብቻ!

'ፅልማሞት' እወዳለሁ። 'ፅልም ያኮስ' እቅፍ ውስጥ ድብቅ ስል ነገር አለሜን እረሳለው። ሊጠፋ ባቆበቆበው ብርሃን የጠቆረው ጥላዬ ከእኔነቴ ገዝፎ ሳየው አሸናፊነት ይሰማኛል።

''መማፀኛ ከተማዬ'' ነው። ነፍስ አጥፍቶ ከደም ተበቃይ የሚሸሽ ሰውን ይመስል ውሽቅ የምልበት 'ቤቴ' . . . በብርሃን ቢገለጥ የሚሰነፍጠውን ሕይወቴን ሸሽቼ የምሸሸግበት ከተማ. . . በድንግዝግዝ ስራመድ ሁሉም መንገድ መዳረሻ፣ ከገንቦ ጠብታ የማልቆጠረውን የኢያሪኮን ሞገስ የሚሰጥ፣ ኃጢአቴ ህያው የማይሆንበት ለኔ እንደ እናት ቤት የሚሞቅ ድሎቴ ነው።

አዎ! 'ጨለማ' እወዳለሁ! 'ሆድና ጀርባ' የሆነውን ማንነቴን ያስታርቅልኛል። 'እየተልመዘመዘ' የሚያስቸግረኝን እኔነቴን 'አደብ' ያስገዛልኛል።

'ፅልመትን' በመገኘቴ ስደምረው <ሽንተ መልካም> የሆንኩ ያህል እከበባለሁ። 'ቅርሽም' ያለው ነገዬ ይጠገናል። 'እየበተበተ' ያለቀው ትላንትናዬ ይፈካል።

'ከከቸችኩ' ሰንብቻለው! ድኩሙ ጉልበቴ ለእርምጃ አሻፈረኝ ብሎኛል። እንደ አረረ ወጥ 'የጎረናው' ስሜ ከሽታው በላይ ጣዕሙ መንችኮብኛል። እከሊት 'ደሰቃም' ናት የሚል ስያሜ ከተሰጠኝ ውሎ አድሯል። ይታወቀኛል። አውቀዋለሁ. . . የኔ ማንነት እሱ ነው <ሀገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው!>

ግን እኮ .... እኔ'ኮ <<ፅላቱ>> ነኝ ለ. . . 'ፅልመት'። ለጥልም ያ'ኮስ ጥሞናው፣ የብርሃንነቴ ፅህፈት ማንፀባረቂያው ነኝ። ጨለማ ውስጥ ለሚያየኝ ኔፍሊም!

ለዛ'ም ነው ጨለማን የምወደው. . . ድቅድቅ ውስጥ የምሸሸገው! . . . ቀን ያጨመተረውን፣ ጭምግግ፣ ጥፍግግ አድርጎ ያሰረውን እኔ'ነቴን የማታ ፅህፈት ስለሚያነፃኝ! ለዛ'ም ነው ጥልመት የምናፍቀው ለዚህም ነው በእሱ የምኖረው!

'አርነቴ' ነው! ያረጀ ያፈጀ ተረታ ተረቶችን የምረሳበት በውስጡ ራ'ሴን ሳየሁ ምሉዕነቴ የሚያሳብቅብኝ!
አርያም ተስፋዬ (2013)

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/114

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Either way, Durov says that he withdrew his resignation but that he was ousted from his company anyway. Subsequently, control of the company was reportedly handed to oligarchs Alisher Usmanov and Igor Sechin, both allegedly close associates of Russian leader Vladimir Putin. In this regard, Sebi collaborated with the Telecom Regulatory Authority of India (TRAI) to reduce the vulnerability of the securities market to manipulation through misuse of mass communication medium like bulk SMS. "And that set off kind of a battle royale for control of the platform that Durov eventually lost," said Nathalie Maréchal of the Washington advocacy group Ranking Digital Rights. He adds: "Telegram has become my primary news source." Unlike Silicon Valley giants such as Facebook and Twitter, which run very public anti-disinformation programs, Brooking said: "Telegram is famously lax or absent in its content moderation policy."
from sa


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American