TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" እንዲህ አይነት አቅጣጫ ስታስቀምጥ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት፣ የቴሌኮም አገልግሎት መስፋፋትን፣ የሞባይል ስልክ ስርጭትን፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ማደግን ማየት አለብህ " - የባንክ ባለሙያ
የገንዘብ ሚኒስቴር በግብይት ወቅት ከ 10,000 ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም የሚከለክል ህግ ሊያወጣ እንደሆነ ተሰምቷል፡፡
በሒደት ላይ የሚገኘው የገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅ ሲፀድቅ ከ10,000 ብር በላይ ግብይትን በጥሬ ገንዘብ መፈፀምም እንደሚያስቀጣ ተዘግቧል።
በረቂቅ አዋጁ ላይ ከባለሙያዎች ጋር ውይይት እንደተደረገና አዋጁ ያስፈለገው በጥሬ ገንዘብ የሚፈፀም ግብይትን ለመገደብ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው አንድ ከፍተኛ የባንክ ባለሙያ አሰራሩ ተገቢና ከረዥመም ጊዜ በፊት ጀምሮ ሲነሳ የነበረ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ሆኖም ግን ይህን አቅጣጫ የመስጠት ስልጣን የብሔራዊ ባንክ ነው ትግበራውም በአንዴ ሳይሆን ጊዜ ይፈልጋል ሲሉ ስሜ እንዳይጠቀስ ያሉት ባለሙያ ገልፀዋል፡፡
ባለሙያው በዝርዝር ምን አሉ ?
" የዚህ ዓይነቱ አሰራር እንዲተገበር ምክረ ሀሳብ የቀረበው የዛሬ አስራ አምስት አመት ነበር፡፡ ከያኔው ጀምሮ ከወረቀት/ ከብር ኖት ጋር የማይያያዝ/ፔፐርለስ አገልግሎት መስጠት አለብን የሚል ሀሳብ ሲቀርብ ነበር፡፡
ህዝቡ ብር በጆንያ እና በአይሱዙ እያጓጓዘ መኖር የለበትም፡፡ እንዲህ ዓይነት አሰራር በሌላውም አለም በአውሮፓም በአሜሪካም የተለመደ ነው፡፡ ለግብይት በጥሬ ገንዘብ ይዘህ የምትንቀሳቀሰው መጠን ገደብ አለው፡፡
በጀርመን ከሁለት ሺህ ዩሮ/ማርክ በላይ ይዘህ መንቀሳቀስ አትችልም ከያዝክ ደግሞ ይወረሳል፡፡ ይህ ደግሞ ጥቅም አለው፡፡
በዚህ አይነቱ አሰራር ህዝብረተሰቡን ወደ ዲጂታላዊ የፋይናንስ አገልግሎት ታመጣዋለህ፡፡
ሌላው ደግሞ ለብር ማተሚያ የሚወጣ ለማጓጓዣና የተበላሸ ብር/Mutilated currency (የተቀደደ፣ የተጣጠፈ፣ የተጎዳ) ብር ለማስወገድ የምታወጣውን በቢሊዮን የሚገመትን ወጪ ታድናለህ፡፡
መንግስት በዚህ አሰራር የሚያድነውን ወጪ ለህዝቡ ትራክተርና ማዳበሪያ ሊገዛለት፣ ትምህርት ቤትና ሆስፒታል ሊገነባለት ይችላል፡፡
ህዝቡ ጥሬ ገንዘብ ይዞ ሲዘዋወር ወይም እቤቱ በማስቀመጥ የሚገጥመውን የዘረፋ ወንጀልም ትቀንሳለህ፡፡ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ትቆጣጠራለህ፡፡
ይህ አሰራር ግን በአንድ ሌሊት ይተግበር መባል የለበትም፡፡ የቴሌኮም ኔትወርክ ካደገ በኋላ ፣ የባንክ አገልግሎት ተስፋፍቶ፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ሲጠናከርና ብሔራዊ ባንክም ተዘጋጅቶበት፣ ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ትምህርት ሰጥቶ ነው እንዲህ ዓይነት ውሳኔ መተላለፍ ያለበት፡፡ ብሔራዊ ባንክ አቅጣጫ አስቀምጦ ነው መደረግ ያለበት፡፡
አሁን በገንዘብ ሚኒስቴር የተቀመጠውን አቅጣጫ ብሔራዊ ባንክ ተቀብሎታል ወይ ? ነው፡፡ ይህን አቅጣጫ ማስቀመጥ ያለበት እሱ ነው ገንዘብ ሚኒስቴር አይደለም፡፡
የገንዘብ ማስተላለፍን ስርዓት የሚወስነው ብሄራዊ ባንክ ነው ገንዘቡን የሚያትመው እሱ ስለሆነ፡፡ ስለ ገንዘብ ዝውውርና ልውውጥ ገደብ ማውጣት ያለበት እሱ ነው፡፡
ለአምጪው እንዲከፈል ህግ ያስገድዳል የሚለውን የባንኩን ህግ ጥሰህ በዲጂታል ካልሆነ በቀር ብርን አልቀበልም ማለት እንዴት ይቻላል ? የብሩ ባለቤት እኮ ብሔራዊ ባንክ ነው፡፡ አሁን ይህን አቅጣጫ ሲቀይሱ ብሔራዊ ባንክን አማክረዋል ወይ ? የሚለው ሊታይ ይገባል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ትንሽ ቆዩ መጀመሪያ ህዝቡን ላስተምር ሊላቸው ይችላል፡፡
ገንዘብ ነክ ጉዳይ ሁሉ በብሔራዊ ባንክ ነው የሚከናወነው፡፡ የገንዘብ ዝውውርን፣ ፍሰትን፣ ልውውጥን የሚመለከቱ መመሪያዎች፣ ህጎችና ደንቦች በዚህ ነፃ ተቋም ነው መውጣትና መመራት ያለባቸው፡፡
ዲጂታላይዜሽን መጣ ሲባል የክፍያ ሁኔታም እንደዚሁ ዲጂታላይዝ እንደሚደረግ ስለሚታወቅ ይህን አሰራር ማስተዋወቅ የሚገባው ብሔራዊ ባነክ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክስ ምን ይላል ?
ሌላው ደግሞ እንዲህ አይነት አቅጣጫ ስታስቀምጥ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት፣ የቴሌኮም አገልግሎት መስፋፋትን፣ የሞባይል ስልክ ስርጭትን፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ማደግን ማየት አለብህ፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ አለ ወይ ? ብለን መጠየቅ ይገባል፡፡
አብዛኛው የገጠሩ ህብረተሰብ የባንክ ተጠቃሚ አይደለም የባንክ ሒሳብ የለውም ፣ ስልክ አይጠቀምም፣ ሞባይል ስልክም የለውም፡፡ በሬውን ሲሸጥ እንዴት ነው ገንዘቡን የምትሰጠው፡፡ ነጋዴውስ እንዴት ነው ከገበሬው ለገዛው ሸቀጥ ክፍያ የሚፈፅመው፡፡ ገበሬው በዚህ ምክንያት ሸቀጥ መሸጥ ቢያቆም በከተማም እኮ የሸቀጥ እጥረት ሊፈጠር ይችላል፡፡
ስለዚህ አሰራሩን በየደረጃው የሚተገብሩት ነው የሚመስለኝ፡፡ እንደ ቦታው ርቀትና እንደ ቴክኖሎጂው መስፋፋት እየታየ በአንዴ ሳይሆን በሒደት መተግበር ያለበት ነገር ነው የሚመስለኝ፡፡ እንደዛ ካልሆነ ግን ገበሬው መልሶ የደላሎች መጫወቻ ሊሆን ነው፡፡ በእኔ ሞባይል ላስገባልህ ይህን ያህል ክፈለኝ ይላል ደላላው፡፡ በኮሚሽን ማለት ነው፡፡ ሌላ የማጭበርበሪያ መንገድም ሊሆን ይችላል፡፡ ስሜታዊ ሆነህ ከገጠር እስከ ከተማ ከመሀል እስከ ጫፍ በአንዴ ላስፈፅም ብትል አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፡፡ "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የገንዘብ ሚኒስቴር በግብይት ወቅት ከ 10,000 ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም የሚከለክል ህግ ሊያወጣ እንደሆነ ተሰምቷል፡፡
በሒደት ላይ የሚገኘው የገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅ ሲፀድቅ ከ10,000 ብር በላይ ግብይትን በጥሬ ገንዘብ መፈፀምም እንደሚያስቀጣ ተዘግቧል።
በረቂቅ አዋጁ ላይ ከባለሙያዎች ጋር ውይይት እንደተደረገና አዋጁ ያስፈለገው በጥሬ ገንዘብ የሚፈፀም ግብይትን ለመገደብ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው አንድ ከፍተኛ የባንክ ባለሙያ አሰራሩ ተገቢና ከረዥመም ጊዜ በፊት ጀምሮ ሲነሳ የነበረ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ሆኖም ግን ይህን አቅጣጫ የመስጠት ስልጣን የብሔራዊ ባንክ ነው ትግበራውም በአንዴ ሳይሆን ጊዜ ይፈልጋል ሲሉ ስሜ እንዳይጠቀስ ያሉት ባለሙያ ገልፀዋል፡፡
ባለሙያው በዝርዝር ምን አሉ ?
" የዚህ ዓይነቱ አሰራር እንዲተገበር ምክረ ሀሳብ የቀረበው የዛሬ አስራ አምስት አመት ነበር፡፡ ከያኔው ጀምሮ ከወረቀት/ ከብር ኖት ጋር የማይያያዝ/ፔፐርለስ አገልግሎት መስጠት አለብን የሚል ሀሳብ ሲቀርብ ነበር፡፡
ህዝቡ ብር በጆንያ እና በአይሱዙ እያጓጓዘ መኖር የለበትም፡፡ እንዲህ ዓይነት አሰራር በሌላውም አለም በአውሮፓም በአሜሪካም የተለመደ ነው፡፡ ለግብይት በጥሬ ገንዘብ ይዘህ የምትንቀሳቀሰው መጠን ገደብ አለው፡፡
በጀርመን ከሁለት ሺህ ዩሮ/ማርክ በላይ ይዘህ መንቀሳቀስ አትችልም ከያዝክ ደግሞ ይወረሳል፡፡ ይህ ደግሞ ጥቅም አለው፡፡
በዚህ አይነቱ አሰራር ህዝብረተሰቡን ወደ ዲጂታላዊ የፋይናንስ አገልግሎት ታመጣዋለህ፡፡
ሌላው ደግሞ ለብር ማተሚያ የሚወጣ ለማጓጓዣና የተበላሸ ብር/Mutilated currency (የተቀደደ፣ የተጣጠፈ፣ የተጎዳ) ብር ለማስወገድ የምታወጣውን በቢሊዮን የሚገመትን ወጪ ታድናለህ፡፡
መንግስት በዚህ አሰራር የሚያድነውን ወጪ ለህዝቡ ትራክተርና ማዳበሪያ ሊገዛለት፣ ትምህርት ቤትና ሆስፒታል ሊገነባለት ይችላል፡፡
ህዝቡ ጥሬ ገንዘብ ይዞ ሲዘዋወር ወይም እቤቱ በማስቀመጥ የሚገጥመውን የዘረፋ ወንጀልም ትቀንሳለህ፡፡ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ትቆጣጠራለህ፡፡
ይህ አሰራር ግን በአንድ ሌሊት ይተግበር መባል የለበትም፡፡ የቴሌኮም ኔትወርክ ካደገ በኋላ ፣ የባንክ አገልግሎት ተስፋፍቶ፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ሲጠናከርና ብሔራዊ ባንክም ተዘጋጅቶበት፣ ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ትምህርት ሰጥቶ ነው እንዲህ ዓይነት ውሳኔ መተላለፍ ያለበት፡፡ ብሔራዊ ባንክ አቅጣጫ አስቀምጦ ነው መደረግ ያለበት፡፡
አሁን በገንዘብ ሚኒስቴር የተቀመጠውን አቅጣጫ ብሔራዊ ባንክ ተቀብሎታል ወይ ? ነው፡፡ ይህን አቅጣጫ ማስቀመጥ ያለበት እሱ ነው ገንዘብ ሚኒስቴር አይደለም፡፡
የገንዘብ ማስተላለፍን ስርዓት የሚወስነው ብሄራዊ ባንክ ነው ገንዘቡን የሚያትመው እሱ ስለሆነ፡፡ ስለ ገንዘብ ዝውውርና ልውውጥ ገደብ ማውጣት ያለበት እሱ ነው፡፡
ለአምጪው እንዲከፈል ህግ ያስገድዳል የሚለውን የባንኩን ህግ ጥሰህ በዲጂታል ካልሆነ በቀር ብርን አልቀበልም ማለት እንዴት ይቻላል ? የብሩ ባለቤት እኮ ብሔራዊ ባንክ ነው፡፡ አሁን ይህን አቅጣጫ ሲቀይሱ ብሔራዊ ባንክን አማክረዋል ወይ ? የሚለው ሊታይ ይገባል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ትንሽ ቆዩ መጀመሪያ ህዝቡን ላስተምር ሊላቸው ይችላል፡፡
ገንዘብ ነክ ጉዳይ ሁሉ በብሔራዊ ባንክ ነው የሚከናወነው፡፡ የገንዘብ ዝውውርን፣ ፍሰትን፣ ልውውጥን የሚመለከቱ መመሪያዎች፣ ህጎችና ደንቦች በዚህ ነፃ ተቋም ነው መውጣትና መመራት ያለባቸው፡፡
ዲጂታላይዜሽን መጣ ሲባል የክፍያ ሁኔታም እንደዚሁ ዲጂታላይዝ እንደሚደረግ ስለሚታወቅ ይህን አሰራር ማስተዋወቅ የሚገባው ብሔራዊ ባነክ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክስ ምን ይላል ?
ሌላው ደግሞ እንዲህ አይነት አቅጣጫ ስታስቀምጥ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት፣ የቴሌኮም አገልግሎት መስፋፋትን፣ የሞባይል ስልክ ስርጭትን፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ማደግን ማየት አለብህ፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ አለ ወይ ? ብለን መጠየቅ ይገባል፡፡
አብዛኛው የገጠሩ ህብረተሰብ የባንክ ተጠቃሚ አይደለም የባንክ ሒሳብ የለውም ፣ ስልክ አይጠቀምም፣ ሞባይል ስልክም የለውም፡፡ በሬውን ሲሸጥ እንዴት ነው ገንዘቡን የምትሰጠው፡፡ ነጋዴውስ እንዴት ነው ከገበሬው ለገዛው ሸቀጥ ክፍያ የሚፈፅመው፡፡ ገበሬው በዚህ ምክንያት ሸቀጥ መሸጥ ቢያቆም በከተማም እኮ የሸቀጥ እጥረት ሊፈጠር ይችላል፡፡
ስለዚህ አሰራሩን በየደረጃው የሚተገብሩት ነው የሚመስለኝ፡፡ እንደ ቦታው ርቀትና እንደ ቴክኖሎጂው መስፋፋት እየታየ በአንዴ ሳይሆን በሒደት መተግበር ያለበት ነገር ነው የሚመስለኝ፡፡ እንደዛ ካልሆነ ግን ገበሬው መልሶ የደላሎች መጫወቻ ሊሆን ነው፡፡ በእኔ ሞባይል ላስገባልህ ይህን ያህል ክፈለኝ ይላል ደላላው፡፡ በኮሚሽን ማለት ነው፡፡ ሌላ የማጭበርበሪያ መንገድም ሊሆን ይችላል፡፡ ስሜታዊ ሆነህ ከገጠር እስከ ከተማ ከመሀል እስከ ጫፍ በአንዴ ላስፈፅም ብትል አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፡፡ "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የአቶ ዓለማየሁ ጢሞቴዎስ ያለመከሰስ መብት ተነሳ። " በሕገወጥ የጦር መሳሪያ ዝዉዉር እና በከፍተኛ የኮንትሮባንድ እና አደንዛዥ ዕፆች ንግድ ተሰማተዋል " የተባሉት ባለስልጣን በቁጥጥር ስር ውለው ያለመከሰስ መብታቸው ተነሳ። የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛ ዙር 4ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓለማየሁ ጢሞቴዎስን ያለመከሰስ…
" አቶ አለማየው ጢሞቴዎስ ለ2 ዓመታት በጥብቅ ዲሲፕሊን ተገምግመው በማስጠንቀቂያ እና በሂስ እንዲታለፉ ተደርገዋል " - በሲዳማ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት
ያለ መከሰስ መብታቸው የተነሳው የቀድሞው የሲዳማ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየው ጢሞቴዎስ በህግ ቁጥጥር ስር ይገኛሉ።
በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ዛሬ ባሰራጨው መረጃ ፥ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በተከታታይ 2 ዓመታት በጥብቅ ዲሲፕሊን ተገምግመው በማስጠንቀቂያ እና በሂስ እንዲታለፉ መደረጋቸውን ጠቁሟል።
በዚህም በራሳቸው ላይ ማሻሻሎችን በማምጣት በፀጥታ ተቋማት ላይ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማድረግ መቻላቸው ፤ ከጥፋታቸው ተምረው እና ታርመው እየሰሩ እንደነበርም ገልጿል።
ይህ ባለበት ሁኔታ ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፓርቲ መርህ ባፈነገጠ መልኩ የክልሉ መንግስት ላይ በተቃራኒው ሲሰሩ እና ከህገወጥ አካላት ጋር ሲገናኙ እንደነበር ጠቁሟል።
በዚህም ምክንያትና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ከነበራቸው የስልጣን ገደብ በላይ በመጠቀማቸው ፓርቲው የእርምት እርምጃን በመውሰዱ ምክንያት ከስራ ገበታቸው ላይ በመቅረት ፓርቲው በስም በግልጽ ጠቅሶ ካልጠራቸውና " የሽብር አካላት " ካላቸው አካላት ጋር ግኑኝነት ሲያካሂዱ እንደተደረሰባቸው አመልክቷል።
በዚህም የተነሳ ሲመሩት የቆየው ተቋም መጥራት ስላለበት በፓርቲ ማዕከል ሰነድ ተዘጋጅቶ ከፀጥታ አመራሮች ጋር በመነጋጋር ሰፊ ወንጅሎች ሲፈፅሙ እንደቆዩ ማወቅ እንደተቻለ ፤ በቀጣይም የማጥራት ሂደቱ በፓርቲው የአሰራር መሰረት እየተካሄደ የሚዘልቅ እንደሆነ ገልጿል።
አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ምንም እንኳን ምክር እና ተግሳፅ ቢሰጣቸውም የግል ጥቅማቸውን ለማግኘት ሲሉ ፦
- በኮንትሮባንድ ንግድ፣
- በህገወጥ መሣሪያ ዝውውር፣
- ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም፣
- የስርዓት ግልበጣና በሌሎች መሠል ወንጀሎች በመጠርጠራቸው ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ አሳውቋል።
ቀጣይ ሂደቱ የፍርድ ቤት እንደሆነም ጠቁሟል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
ያለ መከሰስ መብታቸው የተነሳው የቀድሞው የሲዳማ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየው ጢሞቴዎስ በህግ ቁጥጥር ስር ይገኛሉ።
በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ዛሬ ባሰራጨው መረጃ ፥ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በተከታታይ 2 ዓመታት በጥብቅ ዲሲፕሊን ተገምግመው በማስጠንቀቂያ እና በሂስ እንዲታለፉ መደረጋቸውን ጠቁሟል።
በዚህም በራሳቸው ላይ ማሻሻሎችን በማምጣት በፀጥታ ተቋማት ላይ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማድረግ መቻላቸው ፤ ከጥፋታቸው ተምረው እና ታርመው እየሰሩ እንደነበርም ገልጿል።
ይህ ባለበት ሁኔታ ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፓርቲ መርህ ባፈነገጠ መልኩ የክልሉ መንግስት ላይ በተቃራኒው ሲሰሩ እና ከህገወጥ አካላት ጋር ሲገናኙ እንደነበር ጠቁሟል።
በዚህም ምክንያትና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ከነበራቸው የስልጣን ገደብ በላይ በመጠቀማቸው ፓርቲው የእርምት እርምጃን በመውሰዱ ምክንያት ከስራ ገበታቸው ላይ በመቅረት ፓርቲው በስም በግልጽ ጠቅሶ ካልጠራቸውና " የሽብር አካላት " ካላቸው አካላት ጋር ግኑኝነት ሲያካሂዱ እንደተደረሰባቸው አመልክቷል።
በዚህም የተነሳ ሲመሩት የቆየው ተቋም መጥራት ስላለበት በፓርቲ ማዕከል ሰነድ ተዘጋጅቶ ከፀጥታ አመራሮች ጋር በመነጋጋር ሰፊ ወንጅሎች ሲፈፅሙ እንደቆዩ ማወቅ እንደተቻለ ፤ በቀጣይም የማጥራት ሂደቱ በፓርቲው የአሰራር መሰረት እየተካሄደ የሚዘልቅ እንደሆነ ገልጿል።
አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ምንም እንኳን ምክር እና ተግሳፅ ቢሰጣቸውም የግል ጥቅማቸውን ለማግኘት ሲሉ ፦
- በኮንትሮባንድ ንግድ፣
- በህገወጥ መሣሪያ ዝውውር፣
- ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም፣
- የስርዓት ግልበጣና በሌሎች መሠል ወንጀሎች በመጠርጠራቸው ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ አሳውቋል።
ቀጣይ ሂደቱ የፍርድ ቤት እንደሆነም ጠቁሟል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
የ2026 - 2027 የሁበርት ኤች. ሀምፍሬይ ፌሎሺፕ ፕሮግራም ክፍት ተደርጓል ፤ እርሶም ያመልክቱ።
በአሜሪካ መንግሥት ፈንድ የሚደረገው ይኸው ፕሮግራም በመካከለኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችን (እድሜያቸው ከ32- 46) የሚመለከት ሲሆን አሜሪካ ውስጥ በተለያዩ ዘርፎች ለአንድ የአካዳሚክ አመት (በnon-degree program) ብቃትን ለማሳደግ እድል የሚሰጥ ነው።
ማነው ማመልከት የሚችለው ?
- እድሜያቸው ከ32 እስከ 45 ዓመት
- በምትሰሩበት የስራ ዘርፍ በትንሹ 5 ዓመት የሙሉ ሰዓት ስራ ልምድ ካላችሁ
- የመጀመሪያ ዲግሪ ካላችሁ
- ጥሩ የእንግሊዝኛ ተናጋሪ ከሆናችሁ (የTOFEL ፈተና ሊኖር ይችላል)
- የኢትዮጵያ ዜግነት ያላችሁ ወይም በቋሚነት በህጋዊ መልኩ በኢትዮጵያ የምትኖሩና ፓስፖርት ማግኘት የምትችሉ
- ፕሮግራሙ በሚሰጥበት ጊዜ ከመ/ቤቱ የስራ እረፍት ሊያፅፍ የሚችል
መስኮቹ ምን ምን ናቸው ?
1. ሂማውን ኤንድ ኢንስቲቱሽናል ካፓሲቲ
ለምሳሌ ፦
° ኢኮኖሚክ ፖሊሲ ኤንድ ፋይናንስ፣
° ፐብሊክ ፖሊሲ አናለሲስ ኤንድ አድሚኒስትሬሽን፣
° ቴክኖሎጂ ፖሊሲ ኤንድ ማኔጅመንት፣
2. ራይትስ ኤንድ ፍሪደም
ለምሳሌ ፦
° ጆርናሊዝም/ጋዜጠኝነት ኤንድ ኮሚኒኬሽን፣
° ሂውማን ራይትስ ኤንድ ሎው/ህግ
3. ሰስቲነብል ላንድስ
ለምሳሌ ፦
° አግሪካልቸር/ግብርና ኤንድ ሩላር ዴቨሎፕመንት፣
° ኢንቫይሮመንታል ፖሊስ እና ናቹራል ሪሶርስ ፣ አርባን ኤንድ ሪጅናል ፕላኒንግ
4. ትራቪንግ ኮሚዩኒቲስ
ለምሳሌ ፦
° ፐብሊክ ሄልዝ ኤንድ ፖሊሲ ኤንድ ማኔጅመንት
° ሰብስታንስ አብዩዝ ኢዱኬሽን ኤንድ ፖሊሲ
° ኢዱኬሽን አድሚኒስቴርሽን፣ ፕላኒንግ ኤንድ ፖሊሲ
ለማመልከት ምን ያስፈልጋል ?
➡ CV
➡ የፕሮግራም ፕላን (ለማሳካት ተስፋ የምታደርጉት)
➡ 2 የድጋፍ ደብዳቤ (አንዱ ከአሁን አሰሪ)
➡ ኮፒ ትራንስክሪፕት (አመልክታችሁ ለኢንተርቪው ካለፋችሁ ኦሪጅናል ትራንስክሪፕት ያስፈልጋል)
ማመልከቻችሁን በኦንላይን በዚህ ድረገጽ ብቻ፦ https://apply.iie.org/huberthhumphrey አስገቡ።
ከጁላይ 31,2025 በፊት ብቻ ነው ማመልከቻ ማስገባት የሚቻለው።
ስታመለክቱ ግልጽ ያልሆነላችሁ ጥያቄ ካለ በ [email protected] ላይ በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲን ማነጋገር ይቻላል።
NB. በፕሮግራሙ ወቅት ማንኛውም የቤተሰብ አባል አብሮ መሄድ አይችልም።
(ተጨማሪ ዝርዝር ማብራሪያዎች ከላይ በሁለት ገጽ ተያይዟል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
የ2026 - 2027 የሁበርት ኤች. ሀምፍሬይ ፌሎሺፕ ፕሮግራም ክፍት ተደርጓል ፤ እርሶም ያመልክቱ።
በአሜሪካ መንግሥት ፈንድ የሚደረገው ይኸው ፕሮግራም በመካከለኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችን (እድሜያቸው ከ32- 46) የሚመለከት ሲሆን አሜሪካ ውስጥ በተለያዩ ዘርፎች ለአንድ የአካዳሚክ አመት (በnon-degree program) ብቃትን ለማሳደግ እድል የሚሰጥ ነው።
ማነው ማመልከት የሚችለው ?
- እድሜያቸው ከ32 እስከ 45 ዓመት
- በምትሰሩበት የስራ ዘርፍ በትንሹ 5 ዓመት የሙሉ ሰዓት ስራ ልምድ ካላችሁ
- የመጀመሪያ ዲግሪ ካላችሁ
- ጥሩ የእንግሊዝኛ ተናጋሪ ከሆናችሁ (የTOFEL ፈተና ሊኖር ይችላል)
- የኢትዮጵያ ዜግነት ያላችሁ ወይም በቋሚነት በህጋዊ መልኩ በኢትዮጵያ የምትኖሩና ፓስፖርት ማግኘት የምትችሉ
- ፕሮግራሙ በሚሰጥበት ጊዜ ከመ/ቤቱ የስራ እረፍት ሊያፅፍ የሚችል
መስኮቹ ምን ምን ናቸው ?
1. ሂማውን ኤንድ ኢንስቲቱሽናል ካፓሲቲ
ለምሳሌ ፦
° ኢኮኖሚክ ፖሊሲ ኤንድ ፋይናንስ፣
° ፐብሊክ ፖሊሲ አናለሲስ ኤንድ አድሚኒስትሬሽን፣
° ቴክኖሎጂ ፖሊሲ ኤንድ ማኔጅመንት፣
2. ራይትስ ኤንድ ፍሪደም
ለምሳሌ ፦
° ጆርናሊዝም/ጋዜጠኝነት ኤንድ ኮሚኒኬሽን፣
° ሂውማን ራይትስ ኤንድ ሎው/ህግ
3. ሰስቲነብል ላንድስ
ለምሳሌ ፦
° አግሪካልቸር/ግብርና ኤንድ ሩላር ዴቨሎፕመንት፣
° ኢንቫይሮመንታል ፖሊስ እና ናቹራል ሪሶርስ ፣ አርባን ኤንድ ሪጅናል ፕላኒንግ
4. ትራቪንግ ኮሚዩኒቲስ
ለምሳሌ ፦
° ፐብሊክ ሄልዝ ኤንድ ፖሊሲ ኤንድ ማኔጅመንት
° ሰብስታንስ አብዩዝ ኢዱኬሽን ኤንድ ፖሊሲ
° ኢዱኬሽን አድሚኒስቴርሽን፣ ፕላኒንግ ኤንድ ፖሊሲ
ለማመልከት ምን ያስፈልጋል ?
➡ CV
➡ የፕሮግራም ፕላን (ለማሳካት ተስፋ የምታደርጉት)
➡ 2 የድጋፍ ደብዳቤ (አንዱ ከአሁን አሰሪ)
➡ ኮፒ ትራንስክሪፕት (አመልክታችሁ ለኢንተርቪው ካለፋችሁ ኦሪጅናል ትራንስክሪፕት ያስፈልጋል)
ማመልከቻችሁን በኦንላይን በዚህ ድረገጽ ብቻ፦ https://apply.iie.org/huberthhumphrey አስገቡ።
ከጁላይ 31,2025 በፊት ብቻ ነው ማመልከቻ ማስገባት የሚቻለው።
ስታመለክቱ ግልጽ ያልሆነላችሁ ጥያቄ ካለ በ [email protected] ላይ በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲን ማነጋገር ይቻላል።
NB. በፕሮግራሙ ወቅት ማንኛውም የቤተሰብ አባል አብሮ መሄድ አይችልም።
(ተጨማሪ ዝርዝር ማብራሪያዎች ከላይ በሁለት ገጽ ተያይዟል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
ዛሬ 50ሺህ ብር ሊሸለሙ ነው!
ሰኔ 29 የሚወጣው ቶምቦላ ሎተሪ ገበያ ላይ ነው!
ዛሬ ከታች ባለው ሊንክ የቶምቦላ ሎተሪ ለሚቆርጡ 5 እድለኞች ለእያንዳንዳቸው የ10ሺህ ብር ሽልማት ተዘጋጅቷል.
የቶምቦላን ሎተሪን https://www.ethiolottery.et/am?affiliate=684c3f42ba9392adbfc0f689 እዚህ ባለው ሊንክ በመጫን ተመዝግበው ይቁረጡ!
በ1ኛ እና በ2ኛ ዕጣ ባለሶስት እንዲሁም ባለሁለት መኝታ መኖሪያ የቤት ባለቤት ይሆናሉ፡፡
ከቤቶቹ በተጨማሪ የገንዘብ ሽልማት ያገኛሉ!
በ3ኛ እና በ4ኛ ዕጣ ደግሞ SUV ID-6 ጨምሮ ዘመናዊ የኤሌትሪክ የመኪና ባለቤት ይሆናሉ፡፡
ከመኪናዎቹ በተጨማሪ የገንዘብ ሽልማት ያገኛሉ!
ከወዳጅዎ ጋር ይጋሩ! ቶምቦላን ስጦታ ይላኩ!
ለተጨማሪ መረጃ በ +251977717272 ይደውሉ!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
ዛሬ 50ሺህ ብር ሊሸለሙ ነው!
ሰኔ 29 የሚወጣው ቶምቦላ ሎተሪ ገበያ ላይ ነው!
ዛሬ ከታች ባለው ሊንክ የቶምቦላ ሎተሪ ለሚቆርጡ 5 እድለኞች ለእያንዳንዳቸው የ10ሺህ ብር ሽልማት ተዘጋጅቷል.
የቶምቦላን ሎተሪን https://www.ethiolottery.et/am?affiliate=684c3f42ba9392adbfc0f689 እዚህ ባለው ሊንክ በመጫን ተመዝግበው ይቁረጡ!
በ1ኛ እና በ2ኛ ዕጣ ባለሶስት እንዲሁም ባለሁለት መኝታ መኖሪያ የቤት ባለቤት ይሆናሉ፡፡
ከቤቶቹ በተጨማሪ የገንዘብ ሽልማት ያገኛሉ!
በ3ኛ እና በ4ኛ ዕጣ ደግሞ SUV ID-6 ጨምሮ ዘመናዊ የኤሌትሪክ የመኪና ባለቤት ይሆናሉ፡፡
ከመኪናዎቹ በተጨማሪ የገንዘብ ሽልማት ያገኛሉ!
ከወዳጅዎ ጋር ይጋሩ! ቶምቦላን ስጦታ ይላኩ!
ለተጨማሪ መረጃ በ +251977717272 ይደውሉ!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
ሴጅ ማሰልጠኛ !
የሁለት ወር የክረምት ስልጠና (25% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም)
የጥናታዊ ጽሑፍ አሰራር እና አቀራረብ (Research Methods and Analysis) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን።
👉 Stata, SPSS, E-View, R, Atlas እና Nivivo ሶፍትዌሮችን በመጠቀም Quantitative እና Qualitaitive ሪሰርቾችን መስራትን በአንድ ላይ አካቶ የሚሰለጥኑበት
👉 ከፕሮፖሳል ቀረፃ ጀምሮ ሪሰርች አሰራር ቴክኒኮችን አካቶ እስከ ሪሰርች ሪፖርት አቀራረብ ያለውን አሰራር የሚሰለጥኑበት
👉በታላላቅ የአገራችን የጥናታዊ ፅሑፍ ባለሙያዎች የሚሰጥ ስልጠና
👉 ስልጠናው ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://www.group-telegram.com/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
የሁለት ወር የክረምት ስልጠና (25% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም)
የጥናታዊ ጽሑፍ አሰራር እና አቀራረብ (Research Methods and Analysis) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን።
👉 Stata, SPSS, E-View, R, Atlas እና Nivivo ሶፍትዌሮችን በመጠቀም Quantitative እና Qualitaitive ሪሰርቾችን መስራትን በአንድ ላይ አካቶ የሚሰለጥኑበት
👉 ከፕሮፖሳል ቀረፃ ጀምሮ ሪሰርች አሰራር ቴክኒኮችን አካቶ እስከ ሪሰርች ሪፖርት አቀራረብ ያለውን አሰራር የሚሰለጥኑበት
👉በታላላቅ የአገራችን የጥናታዊ ፅሑፍ ባለሙያዎች የሚሰጥ ስልጠና
👉 ስልጠናው ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://www.group-telegram.com/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
" በተደጋጋሚ ቀጠሮዎች ለአላስፈላጊ ወጪና ለጤና ችግሮች እየተዳረግን ነዉ " - ቅሬታ አቅራቢዎች
➡️ " ሴቶችን ጨምሮ ከሌሎች አከባቢዎች የሚመጡ ተገልጋዮች መንገድ ላይ የሚያድሩበት አጋጣሚ ብዙ ነዉ ! "
በኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሀዋሳ ቅርንጫፍ ፓስፖርት ለመዉሰድ ፣ አሻራ ለመስጠትና ሌሎችም ከፓስፖርት ጋር ለተያያዙ አገልግሎቶች በተሰጣቸዉ ቀጠሮ መሰረት ወደ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ መጥተዉ በተቋሙ በሚስተዋሉ ፍትሐዊ ባልሆኑ አሰራሮች ለአላስፈላጊ ወጪ፣ ለእንግልት እና የጤና ችግሮች እየተዳረጉ መሆኑን ዜጎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አሻራ ለመስጠት ሚያዚያ 5/2017 ዓ/ም በተሰጠን ቀጠሮ መሰረት መጥተን ለሁለት ቀናት ከተጉላላን በኋላ ሰኔ 4/2017 ዓ/ም ተመለሱ ተብለን ከግቢዉ እንድንወጣ ተደርገናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎች " በተቋሙ አቅራቢያ እንኳን እንዳንሆን ' ከፌዴራል ለጉብኝት እንግዶች ስለሚመጡ ' በሚል ከመንገድ ላይም በፖሊስ እንድንባረር ተደርገናል" ብለዋል።
በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታቸው ያሰሙ አንድ አባት እንደገለፁት " ከጥበቃ አንስቶ ተቋሙ ዉስጥ ያሉ ሰራተኞች ያልተገባ ስነምግባር የሚታይባቸዉና እጅ መንሻ ገንዘብ የማይሰጥና አገልግሎቱን በህጋዊ መንገድ ለማግኘት የሚሞክሩ ተገልጋዮችን እስከ መምታት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስዱ " መመልከታቸዉን አስረድተዋል።
ከግቢ ዉጪ ሆነዉ አዳዲስ የሚመጡ ተገልጋዮችን የገንዘብ አቅም በማጥናት " እኔ ላስጨርስልህ " በሚል ያልተገባ ገንዘብ እየተቀበሉ ዉስጥ ካሉ ሸሪኮቻቸዉ ጋር በመሆን ያለወረፋ የሚያስተናግዱ ደላሎችም ስለመኖራቸዉ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ተናግረዋል።
" በዚህ ምክንያት በህጋዊ መንገድ አገልግሎት ማግኘት የሚገባቸዉ ሰዎች ለተደጋጋሚ ቀጠሮዎች ስለሚዳረጉ ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዲሁም በተቋሙ ዉስጥ ባለዉ የሰዉ ብዛት በሚኖረዉ መተፋፈግና መነካካት ለጤና ችግሮች እየተጋለጡ ነው " ሲሉ አብራርተዋል።
አልፎ አልፎ የገንዘብ አቅም ችግር ያላቸዉ ተገልጋዮች እና ወረፋ ለመያዝ የሚፈልጉ ተገልጋዮች ሴቶችን ጨምሮ በተቋሙ በር ላይ የማደር ሁኔታዎች እንደሚስተዋሉም ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘትና ማጣሪያዎችን ለማድረግ ባደረገዉ ጥረት ምሽት 3 ሰዓት ገደማ በር ላይ ለማደር የተሰበሰቡ ሰዎችን ፓትሮል ፖሊስ ለመበተን ሲሞክር ተመልክቷል።
በተገልጋዮቹ ቅሬታ ዙሪያ ከቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ምላሽና ማብራሪያ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ " ከዋናዉ መስሪያ ቤት አዎንታ ሲያገኙ ብቻ ለሚዲያ ምላሽ እንደሚሰጡ " በመግለፃቸዉ ሳይሳካ ቀርቷል።
ምላሽና ማብራሪያ እንዳገኘን የምናካትት ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ትግራይ
የደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ላፕቶፕ ኮምፒተርን " ሰርቀዋል " ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ ቢወስንም አልተተገበረም።
6 የVIP የጥበቃ አባላት የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚከካኤል (ዶ/ር) ላፕቶፕ ኮምፒተርን " ሰርቀዋል " በመባል ተከሰዋል።
የመቐለ ዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤት ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሊቀመንበሩ ላፕቶፕ ኮምፒተር ስርቆት የተጠረጠሩት ግለሰቦች በዋስ እንዲፈቱ ወስኗል።
ስድስቱ ተጠርጣሪዎች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ በሰጠው ውሳኔ መሰረት ቤተሰቦቻቸው ብር ቢያስይዙም " ከላይ የመጣ ትእዛዝ " በሚል ከእስር አልተለቀቁም ብለዋል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ምንጮች።
ባለፈው የግንቦት ወር 2017 ዓ.ም ሳምንት መጨረሻ የሊቀ-መንበሩ ላፕቶፕ ኮምፒተር " በጠባቂዎቻቸው ተዘርፏል " የሚል መረጃ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በስፋት ቢሰራጭም ደጋፊዎቻቸው " መረጃው የፈጠራ ወሬ ነው " በማለት ሲያጣጥሉ ቆይተዋል።
ሊቀ-መንበሩም በቅርቡ ከደጋፊዎቻቸው ጋር በነበራቸው ስብሰባ " አልተሰረቅኩም " የሚል እንደምታ ያለው በሚያሰመስል ሁኔታ ላፕቶፕ ኮምፒዩተር ይዘው ታይተው ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ላፕቶፕ ኮምፒተርን " ሰርቀዋል " ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ ቢወስንም አልተተገበረም።
6 የVIP የጥበቃ አባላት የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚከካኤል (ዶ/ር) ላፕቶፕ ኮምፒተርን " ሰርቀዋል " በመባል ተከሰዋል።
የመቐለ ዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤት ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሊቀመንበሩ ላፕቶፕ ኮምፒተር ስርቆት የተጠረጠሩት ግለሰቦች በዋስ እንዲፈቱ ወስኗል።
ስድስቱ ተጠርጣሪዎች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ በሰጠው ውሳኔ መሰረት ቤተሰቦቻቸው ብር ቢያስይዙም " ከላይ የመጣ ትእዛዝ " በሚል ከእስር አልተለቀቁም ብለዋል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ምንጮች።
ባለፈው የግንቦት ወር 2017 ዓ.ም ሳምንት መጨረሻ የሊቀ-መንበሩ ላፕቶፕ ኮምፒተር " በጠባቂዎቻቸው ተዘርፏል " የሚል መረጃ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በስፋት ቢሰራጭም ደጋፊዎቻቸው " መረጃው የፈጠራ ወሬ ነው " በማለት ሲያጣጥሉ ቆይተዋል።
ሊቀ-መንበሩም በቅርቡ ከደጋፊዎቻቸው ጋር በነበራቸው ስብሰባ " አልተሰረቅኩም " የሚል እንደምታ ያለው በሚያሰመስል ሁኔታ ላፕቶፕ ኮምፒዩተር ይዘው ታይተው ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኦሮሚያ
“ በMpox በአጠቃላይ ኦሮሚያ ክልል ዘጠኝ ኬዞች ደርሰዋል። ሁለት ኬዞች በነቀምት ተገኝተዋል ” - የክልሉ ጤና ቢሮ
በዝንጀሮ ፈንጣጣ /Mpox በሽታ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ዘጠኝ መድረሱን፣ በነቀምት ከተማ ሁለት ኬዞች መገኘታቸውን የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ተስፋዬ ክበበው (ዶ/ር) በሰጡን ቃል፣ “ በክልሉ Mpox ከግንቦት 17/2017 ዓ/ም ጀምሮ እየሰራንበት ያለው ኬዝ ነው። በአጠቃላይ በኦሮሚያ ዘጠኝ ኬዞች ደርሰዋል ” ብለዋል።
ከዘጠኙ ኬዞች፣ አምስቱ ሞያሌ፣ ሁለቱ ጅማ፣ ቀሪ ሁለቱ በነቀምት ከተማ የተገኙ መሆናቸውን፣ ከተያዙት ሰዎች መካከል አገግመው የተመለሱ ፤ በክትትል ላይ ያሉ እንዳሉም ተናግረዋል።
“ ክትትል ላይ ያሉት ታመውም ሳይሆን ቆዳ ላይ የሚታይ ምልክቶች አላቸው። ግን ከዛ በዘለለ ሲስተም የሚያስቸግሩ ምልክቶች የሏቸውም ” ያሉት ዶ/ር ተስፋዬ ወደ ሌሎች እንዳያስተላለፉ ለብቻቸው ሆነው ህክምናና ትምህርት እየተሰጣቸው ስለመሆኑ አብራርተዋል።
በክልሉ ለምርመራ ከ100 በላይ ናሙናዎች ከጅማ፣ ከነቀምት፣ ከሸዋ፣ ከምዕራብ ሸዋ፣ ሀረርጌ እንደመጡ ገልጸው፣ “ ብዙዎቹ ተመርምረው ነጌቲቭ ናቸው። ከትላንት በስቲያ ብቻ ወደ 28 ምርመራ ከተደረገው ናሽናሊ ከአንድ ኬዝ ውጪ ኔጌቲቭ ናቸው ” ብለዋል።
ለበሽታው ህክምና ምን መደረግ እንዳለበት በብዛት ስለማይታወቅ በክልል ደረጃ የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቶ 300 የሚሆኑ ጤና ባለሙያዎች ወደ ዞን፣ ከተማ፣ ሆስፒታል መመለሳቸውን አስረድተዋል።
ጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መሠረት በአጠቃላይ በMpox በሽታ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 19 ደርሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
ፎቶ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
“ በMpox በአጠቃላይ ኦሮሚያ ክልል ዘጠኝ ኬዞች ደርሰዋል። ሁለት ኬዞች በነቀምት ተገኝተዋል ” - የክልሉ ጤና ቢሮ
በዝንጀሮ ፈንጣጣ /Mpox በሽታ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ዘጠኝ መድረሱን፣ በነቀምት ከተማ ሁለት ኬዞች መገኘታቸውን የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ተስፋዬ ክበበው (ዶ/ር) በሰጡን ቃል፣ “ በክልሉ Mpox ከግንቦት 17/2017 ዓ/ም ጀምሮ እየሰራንበት ያለው ኬዝ ነው። በአጠቃላይ በኦሮሚያ ዘጠኝ ኬዞች ደርሰዋል ” ብለዋል።
ከዘጠኙ ኬዞች፣ አምስቱ ሞያሌ፣ ሁለቱ ጅማ፣ ቀሪ ሁለቱ በነቀምት ከተማ የተገኙ መሆናቸውን፣ ከተያዙት ሰዎች መካከል አገግመው የተመለሱ ፤ በክትትል ላይ ያሉ እንዳሉም ተናግረዋል።
“ ክትትል ላይ ያሉት ታመውም ሳይሆን ቆዳ ላይ የሚታይ ምልክቶች አላቸው። ግን ከዛ በዘለለ ሲስተም የሚያስቸግሩ ምልክቶች የሏቸውም ” ያሉት ዶ/ር ተስፋዬ ወደ ሌሎች እንዳያስተላለፉ ለብቻቸው ሆነው ህክምናና ትምህርት እየተሰጣቸው ስለመሆኑ አብራርተዋል።
በክልሉ ለምርመራ ከ100 በላይ ናሙናዎች ከጅማ፣ ከነቀምት፣ ከሸዋ፣ ከምዕራብ ሸዋ፣ ሀረርጌ እንደመጡ ገልጸው፣ “ ብዙዎቹ ተመርምረው ነጌቲቭ ናቸው። ከትላንት በስቲያ ብቻ ወደ 28 ምርመራ ከተደረገው ናሽናሊ ከአንድ ኬዝ ውጪ ኔጌቲቭ ናቸው ” ብለዋል።
ለበሽታው ህክምና ምን መደረግ እንዳለበት በብዛት ስለማይታወቅ በክልል ደረጃ የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቶ 300 የሚሆኑ ጤና ባለሙያዎች ወደ ዞን፣ ከተማ፣ ሆስፒታል መመለሳቸውን አስረድተዋል።
ጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መሠረት በአጠቃላይ በMpox በሽታ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 19 ደርሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
ፎቶ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ጨመረ። እስራኤል ኢራን ላይ ከፍተኛ የአየር ጥቃት ከሰነዘረች በኋላ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 13 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ከ2020 በኋላ በቀን ውስጥ በዚህ ደረጃ ሲጨምር ከፍተኛው ነው ተብሏል። የአንድ በርሜል የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 78 ዶላር ገብቷል። አሁን ያለው ውጥረት በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ መቆራረጥ እንዳይፈጥር ተሰግቷል። ተንታኞች ውጥረቱ…
እስራኤል የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ ኢራን አጸፋዊ ሚሳኤሎችን ያስወነጨፈችበት የሁለቱ አገራት ፍጥጫ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል።
- እስራኤል በድጋሚ አርብ ምሽት በፈጸመችው ጥቃት በርካታ ኢላማዎች መምታቷን አስታውቃለች። በቴህራን የመኖሪያ ህንጻ ላይ በተፈጸመ ጥቃት 20 ህጻናትን ጨምሮ 60 ሰዎች መሞታቸውን የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ ዘግቧል።
- በኢራን አጸፋዊ የሚሳኤል ጥቃቶች ሶስት ሰዎች ሲገደሉ በርካቶች መቁሰላቸውን ባለስልጣናት ተናግረዋል።
- አሜሪካ ወደ ግጭቱ እንድትገባ ከተደረገች ሁኔታዎች በበለጠ ሊያገረሹ ይችላሉ ተብሏል።
- ኢራን ሚሳኤሎችን የምታስወነጭፍ ከሆነ መዲናዋ " ቴህራን ትቃጠላለች " ሲሉ የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ አስጠንቅዋል።
- የእስራኤል መከላከያ ኃይል ዘጠኝ የኢራን የኒውክሌር ሳይንቲስቶችን እና ባለሙያዎችን ገድያለሁ ብሏል። ጦሩ ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ በፈጸመው ተከታታይ ጥቃት የገደላቸው የኒውክሌር ሳይንቲስቶች ስድስት ናቸው ብሎ ነበር።
- ኢራን በእስራኤል ላይ እየወሰደች ያለችውን አጸፋዊ እርምጃ ለማስቆም አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ዩናይትድ ኪንግደም እስራኤልን የሚያግዙ ከሆነ በቀጣናው የሚገኙ የጦር ሰፈሮቻቸውን ኢላማ እንደምታደርግ ማስጠንቀቋን የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ ዘግቧል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ ሲሆን ቪድዮው ከተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
ቪድዮ ፦ የኢራን እና እስራኤል ጦርነት ተባብሶ ቀጥሏል።
ኢራን በእስራኤል ላይ የድሮንና የሚሳኤል ጥቃት ስትፈጽም በዋነኛነት ሃይፋ እንዲሁም ቴላቪቭ ኢላማ ተደርገዋል።
እስራኤል በበኩሏ በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን የሚገኙ ኢላማዎች ላይ ጥቃት እየሰነዘረች መሆኑ ተገልጿል።
በቴህራን የነዳጅ ማከማቻ ኢላማ ያደረገ ጥቃት ተደጽሞ ከፍተኛ እሳት በስፍራው መነሳቱ ተዘግቧል።
በሌላ በኩል ኢራን በዓለም ትልቁ የጋዝ ማምረቻ በእስራኤል ጥቃት ምክንያት በከፊል ስራ መቆሙን ገልጻለች።
ቪድዮ ፦ ሶሻል ሚዲያ
More🖥 @tikvahethmagazine @thiqaheth
ኢራን በእስራኤል ላይ የድሮንና የሚሳኤል ጥቃት ስትፈጽም በዋነኛነት ሃይፋ እንዲሁም ቴላቪቭ ኢላማ ተደርገዋል።
እስራኤል በበኩሏ በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን የሚገኙ ኢላማዎች ላይ ጥቃት እየሰነዘረች መሆኑ ተገልጿል።
በቴህራን የነዳጅ ማከማቻ ኢላማ ያደረገ ጥቃት ተደጽሞ ከፍተኛ እሳት በስፍራው መነሳቱ ተዘግቧል።
በሌላ በኩል ኢራን በዓለም ትልቁ የጋዝ ማምረቻ በእስራኤል ጥቃት ምክንያት በከፊል ስራ መቆሙን ገልጻለች።
ቪድዮ ፦ ሶሻል ሚዲያ
More
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM