Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ሰባት

እጁን ዘርግቶ የተራቆተ እግሯን ሸፈነላት። ምን ነካኝ? አለ ራሱን ቆጣ ብሎ። የተገተረበትን ቦታ ለቆ ወደ መኝታ ቤቱ አመራና አልጋው ላይ ተወረወረ። ጎጃምን ለቆ ሲወጣ የሚያስታውሰው ነገር የለም። በዛን ጊዜ በጣም ልጅ ነበረ። ነገሮች ተረስተውታል። አንድ የማይረሳው ነገር ግን አለ። ታናሽ ወንድሙ እዮብ። በሁለት አመት ውስጥ አከታትላ የወለደቻቸው እናታቸው የ አራት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች እናት ናት። የእድሜ ልዩነታቸው ብዙም ስላይደለ እዮብና አልአዛር መንታ ይመስላሉ።

አባታቸው በእናታቸው ላይ የሚያደርሰውን ግፍ ማየት የሚችልበት ጥንካሬ ስላጣ አንድ ቀን ወንድሙ እዮብን ብቻ ተሰናብቶ ጎጃምን ለቀቀ። ለቀቀ የሚለው ቃል አልአዛር እዚህ ቦታ ለመድረስ ያየው መከራና ጊዜ ባይገልፀውም እንዲሁ ለቀቀ ይባል። የወሰደበት ጊዜ ረጅም ነው ምን አልባትም የእድሜውን እኩሌታ ያህላል።

እዮብ ወደእዚህ አገር ሲመጣ አልአዛር ትንሽ ሱቅ ከፍቶ በመነገድ ላይ ነበር። የስጋ ነገር ሆነና እንደገና ለመገናኘት ዝምድናቸውንም ለማደስ ጊዜ አልፈጀባቸውም። እዮብ አዲስ አበባ ሲመጣ እናታቸው ሆነ አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በወረርሽኝ አልቀው ነበር። ብቻውን የቀረው አንድ እዮብም የተመደበበት ወደነበረው ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ በጎጃም የቀረው አንድም ቤተሰብ የለም። ሁሉም አልቀዋል። ለዚህም ተጠያቂው በምንቸገረኝነት ከዳር ሆኖ ሲመለከት የነበረው መንግስት ለመሆኑ ደምድሟል።

ልቡ በቀልን እንዳረገዘ ዩኒቨርስቲውን ተቀላቀለ። ከአንድ ወር በኃላም በልጅነቱ የተለየውን ወንድሙን አገኘና የብቸኝነቱን ስቃይ መቋቋም ቻለ። የእዮብና የአልአዛር ገበያ ግንኙነት በሚስጥር እንዲሆን ሀሳብ ያቀረበው እዮብ ነበር። አልአዛር ከአገሩ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን ስም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። "አንተነህ" ምን አይነት አስቀያሚ ስም ነው ሲል አሰበ። ገና አዲስ አበባ እንደገባ ወደ አልአዛር ቀየረ። ወንድማማቾቹ በእረፍት ቀናቸው በድብቅ ተገናኝተው ይወያያሉ። በመካከላቸው የነበረው ፍቅር ጠንካራ ነው። አልአዛር ወሩንና ቀኑን ባያስታውሰውም ብቻ የሆነ ቀን ወንድሙ እዮብ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ወደ እሱ ሲሮጥ ተመለከተ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጉቶ ስለነበር የእዮብ ትንፋሽ መለስ እስኪል ራሱ አልጠበቀም። ምን እንደሆነ ለማወቅ በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር።

ፍቅር ይዞኛል! አለው ከእሱ መፍትሔ ያገኝ ይመስል። ታዲያ ምን ችግር አለው? አለ አልአዛር በፍቅር መያዝ እንዲህ ወንድሙን ያስጨነቀበት ምክንያት አልገባሁም። ባክህ አድምጠኝ አለ እዮብ የወንድሙ ቸልታ ቅር አሰኝቶት። የተማሪዎች ህብረት አባል ነኝ። ልጅቷም እንዲሁ አለ እዮብ ከወንድሙ የደበቀውን ሚስጥር ማጋለጡ እያስፈራው።

አልአዛር ስጋቱ እውን ሆኖ ሲያየው የሚያደርገውን አሳጣው። ድሮውኑ የወንድሙን ቆራጥነት ያውቀዋል። የህብረቱ አባል መሆን ማለት ራስን በሸምቀቆ ወደተዘጋጀ ገመድ ማስገባት ማለት ነው። የእዮብን ግትር ውሳኔ ማስቀረት ፍፁም እንደማይቻለው ስለተገነዘበ በሀዘን አንገቱን አቀርቅሮ ዝምታን መረጠ።

አሊ አንድ ነገር በል እንጂ! አለ እዮብ የወንድሙን ዝምታ ጠልቶ። ምን ልበልህ? ራስህን ለሞት አሳልፈህ ስትሰጥ ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ ምን አይነት ምርጫ አለኝ? አለ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ። ከተል አድርጎም ነግረአታል? አለ አልአዛር ንግግሩ ህይወት አልባ ነበር። አልነገርኳትም ልነግራትም አልፈልግም። የህብረቱ አባል እንዳትሆን ያላዴግኩት ጥረት አልነበረም ሊሳካልኝ አልቻለም እንጂ።

ህብረታችን በቅርቡ በመንግስት ሀይል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት አድርጓል። በዚህ ነገር ላይ እንዳትሳተፍ ብፈልግም ቁርጠኛ ሀሳቧን ማስቀየር የማይቻል ነገር ነው። ይህንን ለወንድሙ መንገሩ እፎይታን ሰጥቶታል። አልአዛር ግራ ተጋብቶ ወንድሙ ላይ አሁንም እንዳፈጠጠ ነው። እርዳታ ሲያሻት ወደ አንተ ትመጣለች። ለእኔ ስትል እንዳታሳፍራት። አለ ታላቅ ወንድሙን እያየ። ብሌንን አደራ መስጠቱ አርክቶታል። ፍቅሩ በአስተማማኝ እጆች ላይ ትሆናለች። ይህ ደግሞ ለእሱ ትልቅ ረፍት ነው። የልቡን አውጥቶ መንገር አለመፈለጉ የብሌንን እሺታን አልያም እምቢታን ማወቅ የለመፈለጉ ምክንያት ለአልአዛር አልተገለጠለትም።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/122
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ሰባት

እጁን ዘርግቶ የተራቆተ እግሯን ሸፈነላት። ምን ነካኝ? አለ ራሱን ቆጣ ብሎ። የተገተረበትን ቦታ ለቆ ወደ መኝታ ቤቱ አመራና አልጋው ላይ ተወረወረ። ጎጃምን ለቆ ሲወጣ የሚያስታውሰው ነገር የለም። በዛን ጊዜ በጣም ልጅ ነበረ። ነገሮች ተረስተውታል። አንድ የማይረሳው ነገር ግን አለ። ታናሽ ወንድሙ እዮብ። በሁለት አመት ውስጥ አከታትላ የወለደቻቸው እናታቸው የ አራት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች እናት ናት። የእድሜ ልዩነታቸው ብዙም ስላይደለ እዮብና አልአዛር መንታ ይመስላሉ።

አባታቸው በእናታቸው ላይ የሚያደርሰውን ግፍ ማየት የሚችልበት ጥንካሬ ስላጣ አንድ ቀን ወንድሙ እዮብን ብቻ ተሰናብቶ ጎጃምን ለቀቀ። ለቀቀ የሚለው ቃል አልአዛር እዚህ ቦታ ለመድረስ ያየው መከራና ጊዜ ባይገልፀውም እንዲሁ ለቀቀ ይባል። የወሰደበት ጊዜ ረጅም ነው ምን አልባትም የእድሜውን እኩሌታ ያህላል።

እዮብ ወደእዚህ አገር ሲመጣ አልአዛር ትንሽ ሱቅ ከፍቶ በመነገድ ላይ ነበር። የስጋ ነገር ሆነና እንደገና ለመገናኘት ዝምድናቸውንም ለማደስ ጊዜ አልፈጀባቸውም። እዮብ አዲስ አበባ ሲመጣ እናታቸው ሆነ አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በወረርሽኝ አልቀው ነበር። ብቻውን የቀረው አንድ እዮብም የተመደበበት ወደነበረው ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ በጎጃም የቀረው አንድም ቤተሰብ የለም። ሁሉም አልቀዋል። ለዚህም ተጠያቂው በምንቸገረኝነት ከዳር ሆኖ ሲመለከት የነበረው መንግስት ለመሆኑ ደምድሟል።

ልቡ በቀልን እንዳረገዘ ዩኒቨርስቲውን ተቀላቀለ። ከአንድ ወር በኃላም በልጅነቱ የተለየውን ወንድሙን አገኘና የብቸኝነቱን ስቃይ መቋቋም ቻለ። የእዮብና የአልአዛር ገበያ ግንኙነት በሚስጥር እንዲሆን ሀሳብ ያቀረበው እዮብ ነበር። አልአዛር ከአገሩ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን ስም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። "አንተነህ" ምን አይነት አስቀያሚ ስም ነው ሲል አሰበ። ገና አዲስ አበባ እንደገባ ወደ አልአዛር ቀየረ። ወንድማማቾቹ በእረፍት ቀናቸው በድብቅ ተገናኝተው ይወያያሉ። በመካከላቸው የነበረው ፍቅር ጠንካራ ነው። አልአዛር ወሩንና ቀኑን ባያስታውሰውም ብቻ የሆነ ቀን ወንድሙ እዮብ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ወደ እሱ ሲሮጥ ተመለከተ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጉቶ ስለነበር የእዮብ ትንፋሽ መለስ እስኪል ራሱ አልጠበቀም። ምን እንደሆነ ለማወቅ በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር።

ፍቅር ይዞኛል! አለው ከእሱ መፍትሔ ያገኝ ይመስል። ታዲያ ምን ችግር አለው? አለ አልአዛር በፍቅር መያዝ እንዲህ ወንድሙን ያስጨነቀበት ምክንያት አልገባሁም። ባክህ አድምጠኝ አለ እዮብ የወንድሙ ቸልታ ቅር አሰኝቶት። የተማሪዎች ህብረት አባል ነኝ። ልጅቷም እንዲሁ አለ እዮብ ከወንድሙ የደበቀውን ሚስጥር ማጋለጡ እያስፈራው።

አልአዛር ስጋቱ እውን ሆኖ ሲያየው የሚያደርገውን አሳጣው። ድሮውኑ የወንድሙን ቆራጥነት ያውቀዋል። የህብረቱ አባል መሆን ማለት ራስን በሸምቀቆ ወደተዘጋጀ ገመድ ማስገባት ማለት ነው። የእዮብን ግትር ውሳኔ ማስቀረት ፍፁም እንደማይቻለው ስለተገነዘበ በሀዘን አንገቱን አቀርቅሮ ዝምታን መረጠ።

አሊ አንድ ነገር በል እንጂ! አለ እዮብ የወንድሙን ዝምታ ጠልቶ። ምን ልበልህ? ራስህን ለሞት አሳልፈህ ስትሰጥ ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ ምን አይነት ምርጫ አለኝ? አለ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ። ከተል አድርጎም ነግረአታል? አለ አልአዛር ንግግሩ ህይወት አልባ ነበር። አልነገርኳትም ልነግራትም አልፈልግም። የህብረቱ አባል እንዳትሆን ያላዴግኩት ጥረት አልነበረም ሊሳካልኝ አልቻለም እንጂ።

ህብረታችን በቅርቡ በመንግስት ሀይል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት አድርጓል። በዚህ ነገር ላይ እንዳትሳተፍ ብፈልግም ቁርጠኛ ሀሳቧን ማስቀየር የማይቻል ነገር ነው። ይህንን ለወንድሙ መንገሩ እፎይታን ሰጥቶታል። አልአዛር ግራ ተጋብቶ ወንድሙ ላይ አሁንም እንዳፈጠጠ ነው። እርዳታ ሲያሻት ወደ አንተ ትመጣለች። ለእኔ ስትል እንዳታሳፍራት። አለ ታላቅ ወንድሙን እያየ። ብሌንን አደራ መስጠቱ አርክቶታል። ፍቅሩ በአስተማማኝ እጆች ላይ ትሆናለች። ይህ ደግሞ ለእሱ ትልቅ ረፍት ነው። የልቡን አውጥቶ መንገር አለመፈለጉ የብሌንን እሺታን አልያም እምቢታን ማወቅ የለመፈለጉ ምክንያት ለአልአዛር አልተገለጠለትም።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/122

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Continuing its crackdown against entities allegedly involved in a front-running scam using messaging app Telegram, Sebi on Thursday carried out search and seizure operations at the premises of eight entities in multiple locations across the country. The regulator took order for the search and seizure operation from Judge Purushottam B Jadhav, Sebi Special Judge / Additional Sessions Judge. Since January 2022, the SC has received a total of 47 complaints and enquiries on illegal investment schemes promoted through Telegram. These fraudulent schemes offer non-existent investment opportunities, promising very attractive and risk-free returns within a short span of time. They commonly offer unrealistic returns of as high as 1,000% within 24 hours or even within a few hours. Messages are not fully encrypted by default. That means the company could, in theory, access the content of the messages, or be forced to hand over the data at the request of a government. Official government accounts have also spread fake fact checks. An official Twitter account for the Russia diplomatic mission in Geneva shared a fake debunking video claiming without evidence that "Western and Ukrainian media are creating thousands of fake news on Russia every day." The video, which has amassed almost 30,000 views, offered a "how-to" spot misinformation.
from sg


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American