Telegram Group & Telegram Channel
" እግዚአብሔር ያለዉ ይሆናል ብዬ አይዞ ! አይዞ ! እያልኩ ነበር ወደ ወንዝ ዉስጥ የገባነዉ፤ በፈጣሪ እርዳታ ነው እንጂ በህይወት መትረፍ የማይታሰብ ነበር " - ከአደገኛ የመኪና አደጋ በህይወት የተረፈው ረዳት

በቅርቡ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ዙሪያ ወረዳ ገላና ድልድይ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ከባድ የትራፊክ አደጋ ተከስቶ የ71 ሰዎችን ሕይወት ቀጥፎ እንደነበር አይዘነጋም።

በትናንትናው ዕለት ምሽት ይኸው ቦታ ሌላ የትራፊክ አደጋ አስተናግዷል።

የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ- 3 - 85774 ኢት የሆነ ሲኖትራክ መኪና በትናንትናው ዕለት ምሽት 5:30 ገደማ ዶንጎራ ተብሎ ከሚጠራው አከባቢ የግንባታ አሸዋ ጭኖ ወደ በንሳ ወረዳ እየሄደ በነበረበት ወቅት ቦና ዙሪያ ወረዳ ገላና ወንዝ ሲደርስ ከሳምንታት በፊት የ71 ሰዎችን ሕይወት በቀጠፈዉ ቦታ አደጋ ደርሶበታል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ደህንነትና የትራፊክ አደጋዎች መከላከል ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ዋና ኢ/ር ዳንኤል ሹንኩራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በመኪናዉ ዉስጥ ሹፌሩ እና ረዳቱ ብቻ ነበሩ።

" ከቦታዉ አደገኝነትና ከጫነዉ ሙሉ አሸዋ ክብደት አንፃር በሕይወት ይተርፋሉ ተብሎ ባይታሰብም በፈጣሪ እርዳታ መኪናዉ ተገልብጦ በአራቱም ጎማ ዉሃ ዉስጥ ማረፉን ተከትሎ በሕይወት መትረፋቸዉን " ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲኖትራክ ሹፌሩን አቶ ቴዎድሮስ ተስፋዬን እና ረዳቱን ወጣት ሲሳይ አንዴቦ በስልክ አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።

" ምሽት 5:30 ገላና ወንዘ አከባቢ ስንደርስ ፍሬን እምቢ አለኝ " ያለው ሹፌሩ " አሸዋ ጭነን ስለነበር በድንጋጤ ዘለህ ዉረድ...እያልኩ ረዳቱን ብማፀንም ግራ በተጋባንበት ሁኔታ እያየኝ መኪናዉ ከቁጥጥሬ ዉጪ ሆኖ ወደ ገደል ገባ " ሲል ስለሁኔታው አስረድቷል።

ረዳቱ ወጣት ሲሳይ አንዴቦ በበኩሉ " ከቦታዉ ቁልቁለታማነት እና መኪናዉ ከነበረበት ፍጥነት አንፃር እሱ ' ዝለል ' እያለኝ የነበረ ቢሆንም መዝለሉ የባሰ አደጋ ስለነበረዉ እግዚአብሔር ያለዉ ይሆናል ብዬ አይዞ ! አይዞ ! እያልኩ ነበር ወደ ወንዝ ዉስጥ የገባነዉ " ሲል ስለሁኔታው አክሏል።

" በፈጣሪ እርዳታ እንጂ ከቦታዉ አደገኝነት አንፃር በሕይወት መትረፍ የማይታሰብ ነዉ " የሚሉት ሹፌርና ረዳቱ " ሰዎች እየደወሉ ' ሞልታችኋል ተብሎ በየፌስቡኩ እየተሰራጬ አይደል!? ' እያሉ ይጠይቁናል " ብለዋል።

" በወቅቱ መኪናዉ ወደታች ሲወድቅ በጎማ ዉሃ ዉስጥ በማረፉ በኛ ላይ የከፋ አደጋ አልደረሰም " ያሉን ሲሆን " በአካባቢዉ ሰዎች እርዳታ ወዲያዉኑ ወደ ቦና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተወስደን መጠነኛ ሕክምና ከተደረገልን በኋላ በትራንስፖርት መኪና ተሳፍረን ወደ ሀዋሳ መጥተናል " ብለዋል።

በሌላ በኩል ይህ ቦታ ካስከተለዉና እያስከተለ ካለዉ አደጋ አንፃር ምን ታስቦበታል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመንገድ ደህንነት ዘርፍ ኃላፊ ኮለኔል ሮዳሞ ኪአ ጥያቄ አቅርቧል እሳቸውም ጉዳዩን ለፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ማቅረባቸውንና ዘላቂ መፍትሔ እንዲበጅለት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94115
Create:
Last Update:

" እግዚአብሔር ያለዉ ይሆናል ብዬ አይዞ ! አይዞ ! እያልኩ ነበር ወደ ወንዝ ዉስጥ የገባነዉ፤ በፈጣሪ እርዳታ ነው እንጂ በህይወት መትረፍ የማይታሰብ ነበር " - ከአደገኛ የመኪና አደጋ በህይወት የተረፈው ረዳት

በቅርቡ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ዙሪያ ወረዳ ገላና ድልድይ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ከባድ የትራፊክ አደጋ ተከስቶ የ71 ሰዎችን ሕይወት ቀጥፎ እንደነበር አይዘነጋም።

በትናንትናው ዕለት ምሽት ይኸው ቦታ ሌላ የትራፊክ አደጋ አስተናግዷል።

የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ- 3 - 85774 ኢት የሆነ ሲኖትራክ መኪና በትናንትናው ዕለት ምሽት 5:30 ገደማ ዶንጎራ ተብሎ ከሚጠራው አከባቢ የግንባታ አሸዋ ጭኖ ወደ በንሳ ወረዳ እየሄደ በነበረበት ወቅት ቦና ዙሪያ ወረዳ ገላና ወንዝ ሲደርስ ከሳምንታት በፊት የ71 ሰዎችን ሕይወት በቀጠፈዉ ቦታ አደጋ ደርሶበታል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ደህንነትና የትራፊክ አደጋዎች መከላከል ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ዋና ኢ/ር ዳንኤል ሹንኩራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በመኪናዉ ዉስጥ ሹፌሩ እና ረዳቱ ብቻ ነበሩ።

" ከቦታዉ አደገኝነትና ከጫነዉ ሙሉ አሸዋ ክብደት አንፃር በሕይወት ይተርፋሉ ተብሎ ባይታሰብም በፈጣሪ እርዳታ መኪናዉ ተገልብጦ በአራቱም ጎማ ዉሃ ዉስጥ ማረፉን ተከትሎ በሕይወት መትረፋቸዉን " ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲኖትራክ ሹፌሩን አቶ ቴዎድሮስ ተስፋዬን እና ረዳቱን ወጣት ሲሳይ አንዴቦ በስልክ አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።

" ምሽት 5:30 ገላና ወንዘ አከባቢ ስንደርስ ፍሬን እምቢ አለኝ " ያለው ሹፌሩ " አሸዋ ጭነን ስለነበር በድንጋጤ ዘለህ ዉረድ...እያልኩ ረዳቱን ብማፀንም ግራ በተጋባንበት ሁኔታ እያየኝ መኪናዉ ከቁጥጥሬ ዉጪ ሆኖ ወደ ገደል ገባ " ሲል ስለሁኔታው አስረድቷል።

ረዳቱ ወጣት ሲሳይ አንዴቦ በበኩሉ " ከቦታዉ ቁልቁለታማነት እና መኪናዉ ከነበረበት ፍጥነት አንፃር እሱ ' ዝለል ' እያለኝ የነበረ ቢሆንም መዝለሉ የባሰ አደጋ ስለነበረዉ እግዚአብሔር ያለዉ ይሆናል ብዬ አይዞ ! አይዞ ! እያልኩ ነበር ወደ ወንዝ ዉስጥ የገባነዉ " ሲል ስለሁኔታው አክሏል።

" በፈጣሪ እርዳታ እንጂ ከቦታዉ አደገኝነት አንፃር በሕይወት መትረፍ የማይታሰብ ነዉ " የሚሉት ሹፌርና ረዳቱ " ሰዎች እየደወሉ ' ሞልታችኋል ተብሎ በየፌስቡኩ እየተሰራጬ አይደል!? ' እያሉ ይጠይቁናል " ብለዋል።

" በወቅቱ መኪናዉ ወደታች ሲወድቅ በጎማ ዉሃ ዉስጥ በማረፉ በኛ ላይ የከፋ አደጋ አልደረሰም " ያሉን ሲሆን " በአካባቢዉ ሰዎች እርዳታ ወዲያዉኑ ወደ ቦና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተወስደን መጠነኛ ሕክምና ከተደረገልን በኋላ በትራንስፖርት መኪና ተሳፍረን ወደ ሀዋሳ መጥተናል " ብለዋል።

በሌላ በኩል ይህ ቦታ ካስከተለዉና እያስከተለ ካለዉ አደጋ አንፃር ምን ታስቦበታል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመንገድ ደህንነት ዘርፍ ኃላፊ ኮለኔል ሮዳሞ ኪአ ጥያቄ አቅርቧል እሳቸውም ጉዳዩን ለፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ማቅረባቸውንና ዘላቂ መፍትሔ እንዲበጅለት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94115

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

"He has kind of an old-school cyber-libertarian world view where technology is there to set you free," Maréchal said. "This time we received the coordinates of enemy vehicles marked 'V' in Kyiv region," it added. "There are a lot of things that Telegram could have been doing this whole time. And they know exactly what they are and they've chosen not to do them. That's why I don't trust them," she said. So, uh, whenever I hear about Telegram, it’s always in relation to something bad. What gives? Sebi said data, emails and other documents are being retrieved from the seized devices and detailed investigation is in progress.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American