Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ወደ ቀን መርሃግብር ተቀይረን እንድንማር ከመግባባት ላይ ተደርሷል " - ተማሪዎች

ሰሞኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) መረሃግብር በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በግል ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ አመልካቾች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት " ተመዝግበንና አስፈላጊውን ክፊያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ዉስጥ ባለንበት ዩኒቨርሲቲው ' አናስተምራችሁም ' ብሎናል " ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ዩኒቨርሲቲዉ በበኩሉ ጉዳዩን ከትምህርት ሚንስቴር ጋር በመነጋገር ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፆልን ነበር።

ቅሬታ አቅርበዉ የነበሩ ተማሪዎችና ወላጆች በዛሬው ዕለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳስታወቁት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርሃግብሩን ከእረፍት ቀናት ወደ መደበኛ መርሃግብር በማዘዋወር ተማሪዎቹን ለማስተማር መወሰኑን አረጋግጠዋል።

" ዛሬ ተጠርተን ዉል ተፈራርመናል " ያሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) አመልካቾች " በዉሉ ላይ የተቀመጡ ጉዳዮች የመረሃግብሩ ከዕረፍት ቀናት (weekend) ወደ መደበኛ መቀየር ፣ አመልካቾች በግል ከፍለዉ የሚማሩ ስለመሆናቸው የሚገልፅ፣ ስለ ክፍያ አፈፃፀምና በዩኒቨርሲቲው እና በተማሪዎቹ መካከል ስለሚኖረዉ መብትና ግዴታ የሚደነግግ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የተማሪ ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ከከፍተኛ ጭንቅ ነዉ የገላገላችሁን፣ ምን እንደምናደርግ ጨንቆን ነበር ትምህርት ሚንስቴር እና የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲም ላሳያችሁን በጎ ምላሽ እናመሰግናለን " ብለዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በግል ከፍሎ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለሚወስዱ ተማሪዎች ያዘጋጀዉን ዉል በዚህ መረጃ ላይ ያካተትን ሲሆን የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት  ዶ/ር አክበር ጩፎ ስለጉዳዩ ትክክለኛነት ከመግለፅ ባለፈ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94148
Create:
Last Update:

#Update

" ወደ ቀን መርሃግብር ተቀይረን እንድንማር ከመግባባት ላይ ተደርሷል " - ተማሪዎች

ሰሞኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) መረሃግብር በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በግል ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ አመልካቾች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት " ተመዝግበንና አስፈላጊውን ክፊያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ዉስጥ ባለንበት ዩኒቨርሲቲው ' አናስተምራችሁም ' ብሎናል " ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ዩኒቨርሲቲዉ በበኩሉ ጉዳዩን ከትምህርት ሚንስቴር ጋር በመነጋገር ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፆልን ነበር።

ቅሬታ አቅርበዉ የነበሩ ተማሪዎችና ወላጆች በዛሬው ዕለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳስታወቁት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርሃግብሩን ከእረፍት ቀናት ወደ መደበኛ መርሃግብር በማዘዋወር ተማሪዎቹን ለማስተማር መወሰኑን አረጋግጠዋል።

" ዛሬ ተጠርተን ዉል ተፈራርመናል " ያሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) አመልካቾች " በዉሉ ላይ የተቀመጡ ጉዳዮች የመረሃግብሩ ከዕረፍት ቀናት (weekend) ወደ መደበኛ መቀየር ፣ አመልካቾች በግል ከፍለዉ የሚማሩ ስለመሆናቸው የሚገልፅ፣ ስለ ክፍያ አፈፃፀምና በዩኒቨርሲቲው እና በተማሪዎቹ መካከል ስለሚኖረዉ መብትና ግዴታ የሚደነግግ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የተማሪ ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ከከፍተኛ ጭንቅ ነዉ የገላገላችሁን፣ ምን እንደምናደርግ ጨንቆን ነበር ትምህርት ሚንስቴር እና የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲም ላሳያችሁን በጎ ምላሽ እናመሰግናለን " ብለዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በግል ከፍሎ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለሚወስዱ ተማሪዎች ያዘጋጀዉን ዉል በዚህ መረጃ ላይ ያካተትን ሲሆን የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት  ዶ/ር አክበር ጩፎ ስለጉዳዩ ትክክለኛነት ከመግለፅ ባለፈ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94148

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The fake Zelenskiy account reached 20,000 followers on Telegram before it was shut down, a remedial action that experts say is all too rare. It is unclear who runs the account, although Russia's official Ministry of Foreign Affairs Twitter account promoted the Telegram channel on Saturday and claimed it was operated by "a group of experts & journalists." In 2014, Pavel Durov fled the country after allies of the Kremlin took control of the social networking site most know just as VK. Russia's intelligence agency had asked Durov to turn over the data of anti-Kremlin protesters. Durov refused to do so. Multiple pro-Kremlin media figures circulated the post's false claims, including prominent Russian journalist Vladimir Soloviev and the state-controlled Russian outlet RT, according to the DFR Lab's report. Following this, Sebi, in an order passed in January 2022, established that the administrators of a Telegram channel having a large subscriber base enticed the subscribers to act upon recommendations that were circulated by those administrators on the channel, leading to significant price and volume impact in various scrips.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American