Notice: file_put_contents(): Write of 12571 bytes failed with errno=28 No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94827 -
Telegram Group & Telegram Channel
" በ7 ወራት ውስጥ ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት ተፈጽሟል " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ባለፉት 7 ወራት፣ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ሰርቆት ተፈጽሞበታል።

በአዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት ለአገልግሎት መቋረጥ ምክንያት መሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።


የአገልግሎቱ ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ታዬ ለዶቸቨለ ሬድዮ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

የተቋማቸው ተግባር፣ የኤሌክትሪክ ሀይልን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች ማቅረብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሆኖም፣ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሀይል መሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትልቅ ተግዳሮት እየፈጠረ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡

ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውም ጉዳት እንደዚሁ እየከፋ መምጣቱንም አመልክተዋል፡፡

በተያዘው የበጀት አመት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት መፈፀሙን አስታውቋል፡፡

በዋና ከተማ አዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች፣ በትራንስፎርመር እና በሀይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል።

እነዚህ በውጭ ምንዛሪ የሚገቡ ሀብቶች በመሆናቸው የሚያስከትለው ጉዳት ትልቅ ነው ብለዋል፡፡

የሰርቆት ድርጊቱ በአገልግሎት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ እንዳለውም አመልክተዋል፡፡ 

"/በመሰረተልማቶች ላይ በሚደርሰው ጉዳት ምክንያት የሀይል አቅርቦት ሲቋረጥ፣ ተጎጅዎቹ ደንበኞች ብቻ አይደሉም ’ተቋሙም ከፍተኛ ጉዳት ያስተናግዳል " ያሉ ሲሆን " ይህ ድርጊት ከደንበኞች የምናገኘውን ገቢ ያሳጣናል፣ የወደሙትን መሰረተልማቶች መልሰን ለመጠገን የምናወጣው ወጪም ከፍተኛ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡

" የስርቆት ድርጊቱን ከመከላከል አኳያ፣ በአሁኑ ጊዜ መጠነኛ መሻሻል አለ " ያሉ ሲሆን ሆኖም አሳሳቢነቱ በመቀጠሉ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ይህን ችግር ለማስቆምና እነዚህን የሀገር ሀብቶች ከውድመት ለመታደግ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል።

 የኤለኤክትሪክ መሰረተልማቱ እየተሰረቀ ያለው ተቀባዮች ስላሉ ነው፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ‘ የሚሉት አቶ መላኩ፣ መንግስትም አጥፊዎችን ለህግ በማቅረቡ በኩል እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

#DW

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94827
Create:
Last Update:

" በ7 ወራት ውስጥ ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት ተፈጽሟል " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ባለፉት 7 ወራት፣ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ሰርቆት ተፈጽሞበታል።

በአዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት ለአገልግሎት መቋረጥ ምክንያት መሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።


የአገልግሎቱ ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ታዬ ለዶቸቨለ ሬድዮ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

የተቋማቸው ተግባር፣ የኤሌክትሪክ ሀይልን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች ማቅረብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሆኖም፣ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሀይል መሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትልቅ ተግዳሮት እየፈጠረ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡

ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውም ጉዳት እንደዚሁ እየከፋ መምጣቱንም አመልክተዋል፡፡

በተያዘው የበጀት አመት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት መፈፀሙን አስታውቋል፡፡

በዋና ከተማ አዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች፣ በትራንስፎርመር እና በሀይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል።

እነዚህ በውጭ ምንዛሪ የሚገቡ ሀብቶች በመሆናቸው የሚያስከትለው ጉዳት ትልቅ ነው ብለዋል፡፡

የሰርቆት ድርጊቱ በአገልግሎት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ እንዳለውም አመልክተዋል፡፡ 

"/በመሰረተልማቶች ላይ በሚደርሰው ጉዳት ምክንያት የሀይል አቅርቦት ሲቋረጥ፣ ተጎጅዎቹ ደንበኞች ብቻ አይደሉም ’ተቋሙም ከፍተኛ ጉዳት ያስተናግዳል " ያሉ ሲሆን " ይህ ድርጊት ከደንበኞች የምናገኘውን ገቢ ያሳጣናል፣ የወደሙትን መሰረተልማቶች መልሰን ለመጠገን የምናወጣው ወጪም ከፍተኛ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡

" የስርቆት ድርጊቱን ከመከላከል አኳያ፣ በአሁኑ ጊዜ መጠነኛ መሻሻል አለ " ያሉ ሲሆን ሆኖም አሳሳቢነቱ በመቀጠሉ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ይህን ችግር ለማስቆምና እነዚህን የሀገር ሀብቶች ከውድመት ለመታደግ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል።

 የኤለኤክትሪክ መሰረተልማቱ እየተሰረቀ ያለው ተቀባዮች ስላሉ ነው፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ‘ የሚሉት አቶ መላኩ፣ መንግስትም አጥፊዎችን ለህግ በማቅረቡ በኩል እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

#DW

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94827

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Despite Telegram's origins, its approach to users' security has privacy advocates worried. Russian President Vladimir Putin launched Russia's invasion of Ukraine in the early-morning hours of February 24, targeting several key cities with military strikes. Anastasia Vlasova/Getty Images "He has to start being more proactive and to find a real solution to this situation, not stay in standby without interfering. It's a very irresponsible position from the owner of Telegram," she said. Lastly, the web previews of t.me links have been given a new look, adding chat backgrounds and design elements from the fully-features Telegram Web client.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American