Telegram Group Search
🚨#Alert

በትግራይ ክልል ላጋጠመ የደን ቃጠሎ የፌደራል መንግስት እገዛ ተጠየቀ። በሄሊኮፕተር የተደገፈ የውሃ ርጭት እገዛ እንዲደረግ ነው የተጠየቀው።

የትግራይ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ዛሬ ሰኔ 18/2017 ዓ.ም ለፌደራል የአደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽን በደብዳቤ እንዳስታወቀው ፤ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወረዳ ቃልአሚን ቀበሌ  ሓይለ-ቡሐለ ልዩ ቦታ በሚገኘው የዱስኣ ጥብቅ ደን የእሳት ቃጠሎ አጋጥሟል።

" በዓፋር ክልል ልዩ ቦታ ገረብ ዋሕለ የጀመረው ቃጠሎ በሃይለኛ ንፋስ እየተስፋፋ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ላይ ይገኛል " ብሏል።

" የአከባቢው ማህበረሰብ ቃጠሎው በባህላዊ መንገድ ለማጥፋት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል " ያለው ኮሚሽኑ " ባለው ደረቅ የአየር ሁኔታና ሃይለኛ ንፋስ እየተባባሰ የከፋ ጉዳት በማድረስ ላይ ነው " ሲል ገልጿል።

የተከሰተው የእሳት ቃጠሎ ከአከባቢው ማህበረሰብ አቅም በላይ በመሆኑ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደርና የፌደራል መንግስት እገዛ ተጠይቋል።

የእሳት ቃጠሎው በቁጥጥር ስር ለማዋል የፌደራል መንግስት በሄሊኮፕተር የተደገፈ የውሃ ርጭት እገዛ በአስቸኳይ እንዲያደርግ ኮሚሽኑ ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
#ሴጅ_ማሰልጠኛ

የሁለት ወር የልጆች የክረምት ስልጠና (25% ቅናሽ እስከ ቅዳሜ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም)
👉ስልጠናው ዕድሜያቸው ከ 5-18  ዓመት ላሉ ልጆች የሚሰጥ ነው።
👉 ልጆች ፕሮጀክቶች እየሰሩ የሚሰለጥኑበት
👉ስልጠናው ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
የስልጠናዎቹ ዓይነት፦
👉 Computer Programming and Website Development
👉 AI and Robotics
👉 Graphic Design, Video Editing and Animation
👉 Art (Film Acting, Writing and Modeling)
👉 Painting, Drawing and Sculpture
👉 Language and Basic Computer

0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram
Tiktok
Linkedin
" የጓደኞቼ ፉገራ ለተሻለ ስራ አነሳስቶኛል፤ አሁን ላይ በአንድ ማስታወቂያ በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ይከፈለኛል " - ወጣት ዳግማዊ

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሀዋሳ ከተማ በብስክሌት በላይ የሚደረግ ማስታወቂዎችን ማየት የተለመደ ሆኗል።

ወጣት ዳግም ታምራት ከአምስት ወራት በፊት ከቦታ ቦታ ለመንቀሳቀስ ይጠቀምባት በነበረው አንዲት ብስክሌት ላይ የተወሰኑ የፈጠራ ስራዎችን ጨምሮ የተንቀሳቃሽ የማስታወቂያ ስራ የጀመረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በቋሚነትና በጊዜያዊነት ለ7 ስራ አጥ ወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠር ችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ወጣት ዳግም ታምራትን በስራዉ ዙሪያ አነጋግሮታል።

" ስራዉን የጀመርኩት ለራሴ መንቀሳቀሻ እጠቀምበት በነበረዉ ብስክሌት ላይ ተቀጣይ ባለ ሁለት ጎማ ላሜራ በመስራት የራሴን ማስታወቂያ ሰዎች እንዲያነቡት በማድረግ ነበር ፤ ቀስ በቀስም የሰዎችን ትኩረት ማግኘት ሲጀምር ሌሎች ድርጅቶችንና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማስታወቂያ ለማሰራት ጥሪ ማቅረብ ጀመሩ " ሲል ገልጿል።

" በአሁኑ ወቅት የብስክሌቶችን ቁጥር ከፍ በማድረግ ለ3 ቋሚና 4 ተጠባባቂ ስራ አጥ ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጥሪያሁ " ያለን ወጣት ዳግም " በቀጣይም በዘርፉ የተለያዩ የማስታወቂያ ስራዎች ላይ ለመሰማራትና በLED ላይት የታገዘ ተንቀሳቃሽ የማስታወቂያ ስራ ለመጀመር ዕቅድ እንዳለዉ " ተናግሯል።

" በሞተር ሳይክል የሚንቀሳቀሱ ጓደኝቼ ' አንተ ምን አለብህ የነዳጅ ወጪ ሰልፍና ዋጋ አያስጨንቅህ፤ ለነገሩ ለጤናህም ስፖርት ነዉ ' እያሉ የሚቀልዱብኝ ቀልድና ፉገራ እንደዉም ለምን ይህን ብስክለት የገቢ ማመንጫ አላደርገዉም የሚል ቁጭት አሳድሮብኝ ብስክሌቴን ወደ ተሻለ ስራ አስገብቻለሁ አሁን ላይ በአንድ ማስታወቂያ በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ይከፈለኛል " ሲል ተናግሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
" የውጭ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች ማመልከቻቸውን ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ ይችላሉ " - ብሔራዊ ባንክ

ኢትዮጵያ የባንክ ዘርፉን ለውጪ ባንኮች ክፍት ማድረጓን በይፋ አስታወቀች።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ባንኮች ለመክፈት የሚያስችለውን መመሪያ አጽድቋል።

ባንኩ፥ መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ወይም "የባንክ ሥራ ፈቃድ፤ የእድሳት መስፈርቶች እና የውክልና ቢሮ መመሪያ " መጽደቁን ነው ያስታወቀው።

በዚህ መመሪያ መሰረትም ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባንኮችን ጨምሮ ሌሎች ስትራቴጂክ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ይፈቅዳል።

ብሔራዊ ባንክ ትላንት ባወጣው መግለጫ ፥ " የኢትዮጵያ የባንክ መስክ ለውጭ ኢንቨስተሮች ተከፍቷል፤ የውጭ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች ማመልከቻቸውን ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ ይችላሉ " ሲል አስታውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Big 5 Construct Ethiopia እና የEast Africa Infrastructure & Water Expo

🔥 የመጀመርያው ቀን እጅግ የተለየ ነበር —  2ተኛው ቀን በፍጹም እንዳያመልጥዎ!

የBig 5 Construct Ethiopia እና የEast Africa Infrastructure & Water Expo አጀማመሩ እጅግ ደማቅ ሆኗል!  በከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ሹማምንት ተመርቆ የተከፈተው ደማቅ የንግድ አውደ ርዕይ፣ ለንግድ፣ ለፈጠራ እና ለዓለም አቀፋዊ ትሥሥሮች ሁነኛ መድረክ መሆኑን አስመስክሯል።

በመጀመሪያው ቀን ካልተገኙ:
  ከ20+ ሀገራት የተውጣጡ 180+ የምርት መለያዎችና አገልግሎቶች
የምርት ሙከራዎች፣ አዳዲስ ምርቶች እና በሲፒዲ የተረጋጠላቸው ትምህርታዊ ውይይቶች አምልጠዎታል!

ነገር ግን አልረፈደም! አውደ ርዕዩ በነገው ዕለትም ይቀጥላል!

📍 በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ
🕙 ከጠዋቱ አራት ሰዓት ጀምሮ!
🎟 አሁኑኑ በነጻ ይመዝገቡ: [https://www.big5constructethiopia.com/Tikvah_Ethiopia]
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#DStvEthiopia

📣 ከእሁድ እስከ እሁድ አለንላችሁ!

❗️❗️ለአጭር ጊዜ የሚቆይ! ደንበኝነትዎን ከሰኔ 8 ጀምሮ ሲያራዝሙ ከፍ ወዳለው ፓኬጅ ከተጨማሪ ቻናሎች ጋር በስጦታ ያገኛሉ!!

አዲሱን እና የተሻሻለውን MyDStv መተግበሪያ ያውርዱ።
⬇️ https://mydstv.onelink.me/vGln/xepsjmo7

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው!

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
#EthPL🇪🇹

ክለቦች በየግል ሜዳቸው መጫወት ካቆሙ አመታት ያለፉት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2017 ዓ.ም ውድድር ተጠናቀቀ።

ኢትዮጵያ መድን በታሪኩ የመጀመሪያ ዋንጫውን አንስቷል።

በሱፐር ስፖርት ያለፉትን አመታት በአዲስ ቅርፅ የቀጥታ ሽፋን ያገኘው ሊጉ የአምስት አመት የቀጥታ ስርጭት ውል በይፋ ተጠናቋል።

ሱፐር ስፖርት ባለፉት አመታት 802 ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካቾቹ አድርሷል።

በቀጣይ አመት ሊጉ በአዲስ ቅርፅ ሊደርግ እንደሚችል የአክስዮን ማህበሩ ዋና ስራ አስኪጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ ፍንጭ ሰጥተዋል።

" አሁን እየተጫወትን ከምንገኝባቸው ሜዳዎች የሜዳ መጫወቻ ' Home ' አድርገው የፈለጉትን ከተማ እንዲመርጡ አስበናል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ውድድሩን አርብ ፣ ቅዳሜ እና እሁድ በየሳምንቱ ለማድረግ አስበናል " ሲሉ ገልጸዋል።

ካለፉት ዓመታት ወዲህ ውድድሩ በተመረጡ ከተሞች ባሉ ስታዲየሞች ሲደረግ የቆየ ሲሆን ክለቦች መላ የቡድን አባላቶቻቸው ይዘው አንድ ከተማ ላይ ለሳምንታት በመቆየት ነው ውድድሩን የሚያደርጉት።

የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የአመቱ ምርጥ እነማን ናቸው ?

➡️ የአመቱ ምርጥ ተጨዋች :- ሀይደር ሸረፋ ( ኢትዮጵያ መድን )

➡️ የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ :- ገብረመድህን ኃይሌ ( ኢትዮጵያ መድን )

➡️ የአመቱ ምርጥ ግብ ጠባቂ :- አቡበከር ኑራ ( ኢትዮጵያ መድን )

➡️ ወጣት ተጫዋች :- ይታገሱ ታሪኩ ( ኢትዮጵያ ቡና )

የአመቱ ምስጉን ዋና ዳኛ :- ማኑኤ ወልደፃዲቅ

➡️ የአመቱ ምስጉን ረዳት ዳኛ :- ሙስጠፋ መኪ  በመሆን ተመርጠዋል።

Via @tikvahethsport
2025/06/29 17:45:49
Back to Top
HTML Embed Code: