Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray : በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት የራሱን ምክር ቤት አቋቁሟል። " የሃላቀርነት እና ወንጀል ቡድን " ሲል የገለፀውን በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን የህወሓት ቡድን በፅኑ ለመታገል ቆርጦ እንደተነሳ ገልጿል። በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት እስከ ቀጣዩ 14ኛው የደርጅቱ መደበኛ ጉባኤ የሚቆዩ ሊቀመንበር እና ምክትል ያቀፈ 7 አባላት ባሉት አስተባባሪ ኮሚቴ የሚመራ ም/ቤት…
#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል።

ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል።

ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።

ምንም እንኳን ፓርቲው በስድስት ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ የሚለውን ግዴታ ያለተጨማሪ ማሳሰቢያ መፈፀም እንዳለበት የሚታመን ቢሆንም ቦርዱ ለፓርቲው ነሀሴ 3 ፣ ነሀሴ 20 /2016 ዓ/ም እንዲሁም ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በፃፋቸው ደብዳቤዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማከናዎን ጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ማስታወቁን አመልክቷል።

" ፓርቲው በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በመሆኑ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ ይጠበቃል " ያለው ምርጫ ቦርድ " ለዚሁ የጠቅላላ ጉባኤ ዝግጅት የሚያስፈልገውን የቅድመ ጉባኤ ዝግጅት የተመለከቱ ስራዎችን ቦርዱ መከታተል እንዲችል ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ከማድረጉ 21 ቀናት በፊት ጉባኤው የሚደረግበትን ቀን ለቦርድ እንዲያሳውቅ ይጠበቃል " ብሏል።

ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ፓርቲው ከተመዘገበ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚያስችለውን እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ቦርዱ እንደማያውቅ አመልክቷል።

ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚገባው ወቅት ሊገባደድ ከሁለት ወር ያነሰ ጊዜ የቀረው በመሆኑ ፖርቲው ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በቀረው አጭር ጊዜ የጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ቦርዱ በጥበቅ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም።

በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

ምንም እንኳን ምርጫ ቦርድ እውቅና እንደማይሰጥ ቢያሳውቅም በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ቡድን ጉባኤ አድርጎ አመራሮቹን መርጧል።

አቶ ጌታቸው ረዳን እና ሌሎች ከእሳቸው ጋር የነበሩ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮችን ከቦታቸውን አንስቷል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ቡድንም ለጉባኤው እውቅና የነፈገ ሲሆን ትክክለኛ ቅቡልነት ያለው ጉባኤ እንዲደረግ እየሰራ መሆኑን ማሳወቁ አይዘነጋም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93283
Create:
Last Update:

#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል።

ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል።

ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።

ምንም እንኳን ፓርቲው በስድስት ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ የሚለውን ግዴታ ያለተጨማሪ ማሳሰቢያ መፈፀም እንዳለበት የሚታመን ቢሆንም ቦርዱ ለፓርቲው ነሀሴ 3 ፣ ነሀሴ 20 /2016 ዓ/ም እንዲሁም ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በፃፋቸው ደብዳቤዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማከናዎን ጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ማስታወቁን አመልክቷል።

" ፓርቲው በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በመሆኑ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ ይጠበቃል " ያለው ምርጫ ቦርድ " ለዚሁ የጠቅላላ ጉባኤ ዝግጅት የሚያስፈልገውን የቅድመ ጉባኤ ዝግጅት የተመለከቱ ስራዎችን ቦርዱ መከታተል እንዲችል ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ከማድረጉ 21 ቀናት በፊት ጉባኤው የሚደረግበትን ቀን ለቦርድ እንዲያሳውቅ ይጠበቃል " ብሏል።

ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ፓርቲው ከተመዘገበ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚያስችለውን እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ቦርዱ እንደማያውቅ አመልክቷል።

ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚገባው ወቅት ሊገባደድ ከሁለት ወር ያነሰ ጊዜ የቀረው በመሆኑ ፖርቲው ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በቀረው አጭር ጊዜ የጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ቦርዱ በጥበቅ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም።

በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

ምንም እንኳን ምርጫ ቦርድ እውቅና እንደማይሰጥ ቢያሳውቅም በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ቡድን ጉባኤ አድርጎ አመራሮቹን መርጧል።

አቶ ጌታቸው ረዳን እና ሌሎች ከእሳቸው ጋር የነበሩ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮችን ከቦታቸውን አንስቷል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ቡድንም ለጉባኤው እውቅና የነፈገ ሲሆን ትክክለኛ ቅቡልነት ያለው ጉባኤ እንዲደረግ እየሰራ መሆኑን ማሳወቁ አይዘነጋም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93283

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

But Telegram says people want to keep their chat history when they get a new phone, and they like having a data backup that will sync their chats across multiple devices. And that is why they let people choose whether they want their messages to be encrypted or not. When not turned on, though, chats are stored on Telegram's services, which are scattered throughout the world. But it has "disclosed 0 bytes of user data to third parties, including governments," Telegram states on its website. "There is a significant risk of insider threat or hacking of Telegram systems that could expose all of these chats to the Russian government," said Eva Galperin with the Electronic Frontier Foundation, which has called for Telegram to improve its privacy practices. Again, in contrast to Facebook, Google and Twitter, Telegram's founder Pavel Durov runs his company in relative secrecy from Dubai. There was another possible development: Reuters also reported that Ukraine said that Belarus could soon join the invasion of Ukraine. However, the AFP, citing a Pentagon official, said the U.S. hasn’t yet seen evidence that Belarusian troops are in Ukraine. READ MORE
from tr


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American