Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ስድስት

ባሰበችው ቁጥርም ይሄ ንግግሩ ይገርማት ነበር። አሁን ግን ነገሮች እየተገለጡላት መጡ። "አፍቅሮኝ ነበር ማለት ነው" እራሷን ጠየቀች። ለዚህ ነው ወደ ንቅናቄው መግባቴን የተቃወመው? የመጨረሻውን ስብሰባ እንዳትካፈል ያላደረገው ጥረት እንዳልነበር ትዝ አላት። በተኩሱ መሀል መጥቶ ጎትቶ ሲወስዳት  ዐይኑ ላይ ይነበብ የነበረው ፍቅር ከየት እንደመጣ በዛን ጊዜ ለማወቅ ተቸግራ ነበር። ግን ለምን አልነገረኝም? እኮ ለምን? ልቧ በሀዘን ደምቷል።
      ታክሲው ካዛንቺስ ደርሶ ሲቆም ወረደች። የተባለው አድራሻ ጋ ለመድረስ ብዙ ሰአት አልወሰደባትም። አልአዛር ከተባለው ሰው የጥያቄዎቿን መልስ እንደምታገኝ ስለገመተች አድራሻው ላይ የሰፈረውን ቤት ለማግኘት ተቻኮለች። መለስተኛ ሆኖ የተደላደለ ኑሮ ሊኖርበት የሚችልበት ሰፊ ቤት አጠገብ ስትደርስ 'ይሄ መሆን አለበት' አለች በሆዷ። የበሩን መጥሪያ ተጫነችው። የሷን መምጣት በመጠባበቅ ላይ የነበሩ እስከሚመስላት ድረስ በሚያስደንቅ ፍጥነት የቤቱ በር ተከፈተ።
       ከፊት ለፊቷ የቆመውን ሰው ስታይ ደነገጠች።ቁርጥ እዮብን። ልቧ በድንጋጤ ምቷን ጨመረች። እንድትገባ በሩን ወለል አድርጎ ከፈተላት። ምንም ሳታመነታ ወደ ውስጥ ዘለቀች። ጊዜ ሳይፈጅ 'አልአዛር' ብሎ እጁን ለትውውቅ ዘረጋ። 'ብሌን' አለች ነገር ግን ራሷን ማስተዋወቅ አስፈላጊ መስሎ አልታያትም። ወጣቱ ካወቃት የቆየ ይመስላልና።
     አልአዛር ገና ብሌንን እንዳየ የወንድሙ እንደዛ በፍቅር መሰቃየት ተገለጠለት። ማንስ ቢሆን ከዚች ቆንጆ የፍቅር ወጥመድ ያመልጣል ሲል አሰበ። ሰውነቷ በድካምና በዱላ የተጎዳ ስለሚመስል ዛሬ ወንድሙ በአደራ ያስቀመጠውን ወረቀት ቢሰጣት ሊጎዳት ይችላል ብሎ ስለጠረጠረ ወረቀቱን ነገ ሊያሳያት ቀጠሮውን አራዘመ።
      ቤቱ የአንድ ወንድ መኖሪያ ብቻ አይመስልም። በፅዳት ተስተካክላ የተዘጋጀችው ሳሎን የሴት እጅ የግድ ያረፈባት መሆኑን ገመተች። እንደገባች ከፊቷ የነበረው ሶፋ ላይ ተዘረረች። ድካሙና ረሀቡ ተደራርበው አቅም አሳጥተዋታል። የልቧ ሀዘን ደግሞ ይበልጥ ሰውነቷን ጎዳው። "ወንድሙ  ነው?" እንዴት ወንድም እንዳለው ለማንም ሳይናገር ኖረ? ግራ ገብቷት ራሷን ጠየቀች።
      አልአዛር ፈጠን ብሎ የሚበላ አቀረበላት። ምግቡን ከፊት ለፊቷ ቀርቦ ስታየው የረሀብ ስሜቷ ተቀሰቀሰ። በልታ እንደጨረሰች ወጣቱ በአበላል ሁኔታዋ መገረሙ አይቀርም ብላ አሰበች። እሱ ግን የተረዳት ይመስላል።
       ራሷን በድንጋይ እንደተመታ ሰው ይፈልጣታል።መቋቋም እስኪያቅታት ድረስ ህመሙ እየጨመረ ሄደ። የራስ ምታት መድኃኒት ይኖርሃል? አለች ወጣቱን እያየች። ወደ መኝታ ክፍል ሄዶ ሁለት መድኃኒቶችን ይዞ መጣ። ይኸውና የራስ ምታት መድሀኒቱ ብሎ አንዱን ወደ እጇ አቀበላት። "ይሄ ደግሞ የእንቅልፍ ኪኒን ነው።" ብዙ እረፍት ያገኘሽ አትመስዪም አላት ፊቷን እያየ። ብሌን አላንገራገረችም ሁለቱንም መድኃኒቶች ዋጠቻቸው። የእንቅልፍ መድኃኒቱ ለመስራት ጊዜም አልወሰደበትም። ጭንቅላቷን ሶፋው ላይ አስደግፋ ለመተኛት ሞከረች። አልተመቻትም። ወጣቱ ሶፋው ላይ ሙሉ ለሙሉ ወጥታ እንድትተኛ ትራስና ወፍራም ጋቢ ከመኝታ ቤት አምጥቶ ሰጣት። መድኃኒቶቹን  መኝታ ቤት አስቀምጦ እስከሚመለስ እንቅልፍ ወስዷታል።
      ከሶፋው አጠገብ ቆሞ ሶፋው ላይ የተኛችሁን ብሌንን በአድናቆት ይመለከታታል። ሁለመናዋ ልብን ይማርካል። በብዙ ነገር ራሳቸውን አስጊጠው ከሚመለከታቸው ሴቶች ይልቅ በሷ ውስጥ ከጉስቁልናዋ በላይ ጎልቶ የሚታየው አፍዝዞታል። እጁን ዘርግቶ.......
✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/121
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ስድስት

ባሰበችው ቁጥርም ይሄ ንግግሩ ይገርማት ነበር። አሁን ግን ነገሮች እየተገለጡላት መጡ። "አፍቅሮኝ ነበር ማለት ነው" እራሷን ጠየቀች። ለዚህ ነው ወደ ንቅናቄው መግባቴን የተቃወመው? የመጨረሻውን ስብሰባ እንዳትካፈል ያላደረገው ጥረት እንዳልነበር ትዝ አላት። በተኩሱ መሀል መጥቶ ጎትቶ ሲወስዳት  ዐይኑ ላይ ይነበብ የነበረው ፍቅር ከየት እንደመጣ በዛን ጊዜ ለማወቅ ተቸግራ ነበር። ግን ለምን አልነገረኝም? እኮ ለምን? ልቧ በሀዘን ደምቷል።
      ታክሲው ካዛንቺስ ደርሶ ሲቆም ወረደች። የተባለው አድራሻ ጋ ለመድረስ ብዙ ሰአት አልወሰደባትም። አልአዛር ከተባለው ሰው የጥያቄዎቿን መልስ እንደምታገኝ ስለገመተች አድራሻው ላይ የሰፈረውን ቤት ለማግኘት ተቻኮለች። መለስተኛ ሆኖ የተደላደለ ኑሮ ሊኖርበት የሚችልበት ሰፊ ቤት አጠገብ ስትደርስ 'ይሄ መሆን አለበት' አለች በሆዷ። የበሩን መጥሪያ ተጫነችው። የሷን መምጣት በመጠባበቅ ላይ የነበሩ እስከሚመስላት ድረስ በሚያስደንቅ ፍጥነት የቤቱ በር ተከፈተ።
       ከፊት ለፊቷ የቆመውን ሰው ስታይ ደነገጠች።ቁርጥ እዮብን። ልቧ በድንጋጤ ምቷን ጨመረች። እንድትገባ በሩን ወለል አድርጎ ከፈተላት። ምንም ሳታመነታ ወደ ውስጥ ዘለቀች። ጊዜ ሳይፈጅ 'አልአዛር' ብሎ እጁን ለትውውቅ ዘረጋ። 'ብሌን' አለች ነገር ግን ራሷን ማስተዋወቅ አስፈላጊ መስሎ አልታያትም። ወጣቱ ካወቃት የቆየ ይመስላልና።
     አልአዛር ገና ብሌንን እንዳየ የወንድሙ እንደዛ በፍቅር መሰቃየት ተገለጠለት። ማንስ ቢሆን ከዚች ቆንጆ የፍቅር ወጥመድ ያመልጣል ሲል አሰበ። ሰውነቷ በድካምና በዱላ የተጎዳ ስለሚመስል ዛሬ ወንድሙ በአደራ ያስቀመጠውን ወረቀት ቢሰጣት ሊጎዳት ይችላል ብሎ ስለጠረጠረ ወረቀቱን ነገ ሊያሳያት ቀጠሮውን አራዘመ።
      ቤቱ የአንድ ወንድ መኖሪያ ብቻ አይመስልም። በፅዳት ተስተካክላ የተዘጋጀችው ሳሎን የሴት እጅ የግድ ያረፈባት መሆኑን ገመተች። እንደገባች ከፊቷ የነበረው ሶፋ ላይ ተዘረረች። ድካሙና ረሀቡ ተደራርበው አቅም አሳጥተዋታል። የልቧ ሀዘን ደግሞ ይበልጥ ሰውነቷን ጎዳው። "ወንድሙ  ነው?" እንዴት ወንድም እንዳለው ለማንም ሳይናገር ኖረ? ግራ ገብቷት ራሷን ጠየቀች።
      አልአዛር ፈጠን ብሎ የሚበላ አቀረበላት። ምግቡን ከፊት ለፊቷ ቀርቦ ስታየው የረሀብ ስሜቷ ተቀሰቀሰ። በልታ እንደጨረሰች ወጣቱ በአበላል ሁኔታዋ መገረሙ አይቀርም ብላ አሰበች። እሱ ግን የተረዳት ይመስላል።
       ራሷን በድንጋይ እንደተመታ ሰው ይፈልጣታል።መቋቋም እስኪያቅታት ድረስ ህመሙ እየጨመረ ሄደ። የራስ ምታት መድኃኒት ይኖርሃል? አለች ወጣቱን እያየች። ወደ መኝታ ክፍል ሄዶ ሁለት መድኃኒቶችን ይዞ መጣ። ይኸውና የራስ ምታት መድሀኒቱ ብሎ አንዱን ወደ እጇ አቀበላት። "ይሄ ደግሞ የእንቅልፍ ኪኒን ነው።" ብዙ እረፍት ያገኘሽ አትመስዪም አላት ፊቷን እያየ። ብሌን አላንገራገረችም ሁለቱንም መድኃኒቶች ዋጠቻቸው። የእንቅልፍ መድኃኒቱ ለመስራት ጊዜም አልወሰደበትም። ጭንቅላቷን ሶፋው ላይ አስደግፋ ለመተኛት ሞከረች። አልተመቻትም። ወጣቱ ሶፋው ላይ ሙሉ ለሙሉ ወጥታ እንድትተኛ ትራስና ወፍራም ጋቢ ከመኝታ ቤት አምጥቶ ሰጣት። መድኃኒቶቹን  መኝታ ቤት አስቀምጦ እስከሚመለስ እንቅልፍ ወስዷታል።
      ከሶፋው አጠገብ ቆሞ ሶፋው ላይ የተኛችሁን ብሌንን በአድናቆት ይመለከታታል። ሁለመናዋ ልብን ይማርካል። በብዙ ነገር ራሳቸውን አስጊጠው ከሚመለከታቸው ሴቶች ይልቅ በሷ ውስጥ ከጉስቁልናዋ በላይ ጎልቶ የሚታየው አፍዝዞታል። እጁን ዘርግቶ.......
✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/121

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Emerson Brooking, a disinformation expert at the Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, said: "Back in the Wild West period of content moderation, like 2014 or 2015, maybe they could have gotten away with it, but it stands in marked contrast with how other companies run themselves today." Either way, Durov says that he withdrew his resignation but that he was ousted from his company anyway. Subsequently, control of the company was reportedly handed to oligarchs Alisher Usmanov and Igor Sechin, both allegedly close associates of Russian leader Vladimir Putin. Update March 8, 2022: EFF has clarified that Channels and Groups are not fully encrypted, end-to-end, updated our post to link to Telegram’s FAQ for Cloud and Secret chats, updated to clarify that auto-delete is available for group and channel admins, and added some additional links. The regulator took order for the search and seizure operation from Judge Purushottam B Jadhav, Sebi Special Judge / Additional Sessions Judge. However, the perpetrators of such frauds are now adopting new methods and technologies to defraud the investors.
from tr


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American