Telegram Group & Telegram Channel
አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት  ዕጩ ሆነው ቀረቡ።

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም  ፓርላማ ቀርበዋል።

ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

አቶ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት ሲሆን የመጨረሻ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ነበር።

ከኃላፊነታቸው የተነሱት " በቀረበባቸው ቅሬታ " መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ ከ10 ዓመታት በፊት ዘግቧል።

" ከሠራተኞች እና ከተቋሙ ደንበኞች ቅሬታዎች ይቀርቡባቸው እንደነበር " ጋዜጣው በወቅቱ ዘግቧል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ ብርሃኑን ከዚህ ኃላፊነት ማንሳታቸውም የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል።

አቶ ብርሃኑ የአዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬከተር ሆነው ከመሾማቸው በፊት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም. ለ6 ዓመታት አገልግለዋል።

በሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ መሠረት አቶ ብርሃኑ ከዚህ ኃላፊነታቸው የተነሱትም በቀረበባቸው ቅሬታ ምክንያት ነው።

ከተወለዱበት ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች አዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በአቶ ብርሃኑ ላይ የተፈራረሙትን ቅሬታ በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማቅረባቸውን የሪፖርተር ዘገባ ያስታውሳል።

ይህን ተከትሎ " በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ባቀረበባቸው ሪፖርት ከካቢኔ ጉዳይ ሚኒስትርነታቸው እና ከኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲነሱ " መደረጉን ሪፖርተር ከ10 ዓመታት በፊት በሠራው ዘገባ ጠቅሷል።

አቶ ብርሃኑ በመንግሥታዊ ተቋማት ከነበራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ አወዛጋውን የ1997 ምርጫ ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ።

የትምህርት ሁኔታቸው ምን ይመስላል ?

ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው። በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ከሕንድ አገር የማስተርስ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል።

የስራ ህይወታቸው ምን ይመስላል ?

- ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲ አስተምረዋል።

- በዞን ፋይናንስ መምሪያ የህግ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።

- የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ባገኙበት የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የህግ ፋካልቲ ለ3 ዓመታት አስተምረዋል።

- በቀድሞው ደቡብ ክልል የፍትህ ቢሮ ኃላፊነት ላይ ሰርተዋል። ከዛ በመቀጠልም በቀረበባቸው ቅሬታዎች ከስልጣን ወደተነሱባቸው የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት አቅንተዋል።

- ከመንግስታዊ የሥራ ኃላፊ ከተነሱ በኋላ ላለፉት 10 ዓመታት በጥብቅና እና በህግ ማማከር ስራ ላይ መሰማራታቸውን ለፓርላማ አባላት የቀረበው የስራ ልምድ ያሳያል።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94129
Create:
Last Update:

አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት  ዕጩ ሆነው ቀረቡ።

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም  ፓርላማ ቀርበዋል።

ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

አቶ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት ሲሆን የመጨረሻ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ነበር።

ከኃላፊነታቸው የተነሱት " በቀረበባቸው ቅሬታ " መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ ከ10 ዓመታት በፊት ዘግቧል።

" ከሠራተኞች እና ከተቋሙ ደንበኞች ቅሬታዎች ይቀርቡባቸው እንደነበር " ጋዜጣው በወቅቱ ዘግቧል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ ብርሃኑን ከዚህ ኃላፊነት ማንሳታቸውም የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል።

አቶ ብርሃኑ የአዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬከተር ሆነው ከመሾማቸው በፊት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም. ለ6 ዓመታት አገልግለዋል።

በሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ መሠረት አቶ ብርሃኑ ከዚህ ኃላፊነታቸው የተነሱትም በቀረበባቸው ቅሬታ ምክንያት ነው።

ከተወለዱበት ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች አዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በአቶ ብርሃኑ ላይ የተፈራረሙትን ቅሬታ በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማቅረባቸውን የሪፖርተር ዘገባ ያስታውሳል።

ይህን ተከትሎ " በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ባቀረበባቸው ሪፖርት ከካቢኔ ጉዳይ ሚኒስትርነታቸው እና ከኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲነሱ " መደረጉን ሪፖርተር ከ10 ዓመታት በፊት በሠራው ዘገባ ጠቅሷል።

አቶ ብርሃኑ በመንግሥታዊ ተቋማት ከነበራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ አወዛጋውን የ1997 ምርጫ ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ።

የትምህርት ሁኔታቸው ምን ይመስላል ?

ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው። በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ከሕንድ አገር የማስተርስ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል።

የስራ ህይወታቸው ምን ይመስላል ?

- ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲ አስተምረዋል።

- በዞን ፋይናንስ መምሪያ የህግ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።

- የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ባገኙበት የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የህግ ፋካልቲ ለ3 ዓመታት አስተምረዋል።

- በቀድሞው ደቡብ ክልል የፍትህ ቢሮ ኃላፊነት ላይ ሰርተዋል። ከዛ በመቀጠልም በቀረበባቸው ቅሬታዎች ከስልጣን ወደተነሱባቸው የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት አቅንተዋል።

- ከመንግስታዊ የሥራ ኃላፊ ከተነሱ በኋላ ላለፉት 10 ዓመታት በጥብቅና እና በህግ ማማከር ስራ ላይ መሰማራታቸውን ለፓርላማ አባላት የቀረበው የስራ ልምድ ያሳያል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94129

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

However, the perpetrators of such frauds are now adopting new methods and technologies to defraud the investors. At this point, however, Durov had already been working on Telegram with his brother, and further planned a mobile-first social network with an explicit focus on anti-censorship. Later in April, he told TechCrunch that he had left Russia and had “no plans to go back,” saying that the nation was currently “incompatible with internet business at the moment.” He added later that he was looking for a country that matched his libertarian ideals to base his next startup. The Securities and Exchange Board of India (Sebi) had carried out a similar exercise in 2017 in a matter related to circulation of messages through WhatsApp. This ability to mix the public and the private, as well as the ability to use bots to engage with users has proved to be problematic. In early 2021, a database selling phone numbers pulled from Facebook was selling numbers for $20 per lookup. Similarly, security researchers found a network of deepfake bots on the platform that were generating images of people submitted by users to create non-consensual imagery, some of which involved children. Anastasia Vlasova/Getty Images
from tw


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American