Telegram Group & Telegram Channel
" ለቅሬታችን ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን ለርዕሰ መስተዳድሩ አቅርበናል " - የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መምህራን

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ክፍያ " አልተከፈለንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

በቁጥር ከአንድ መቶ በላይ የሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ የፃፉትንና የተፈራረሙበትን የቅሬታ ደብዳቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ሰራተኞቹ በሰጡት ቃልም " መንግስት ለኑሮ ዉድነት ማካካሻ በማለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1/2017ዓ/ም ጀምሮ ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም እስካሁን የማሻሻያዉ ልዩነት አልተከገለንም " ሲሉ ገልፀዋል።

" ስራ ሳናቆም ተደጋጋሚ ቅሬታ ስናቀርብ ቆይተናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ከዚህ ቀደም ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ አብዘኞቻችን የተሰጠንን የደረጃ ዕድገት ክፊያ ተግባራዊ አልተደረገም በዚያ ላይ ይህ ሲጨመርበት ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ " ብለዋል።

ኮሌጁ ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ?

የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጻድቁ ሳሙኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የደሞዝ ማሻሻያው አለመከፈሉ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።

" የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በክልሉ ያሉ የሁሉም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎችን መረጃ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በመሰብሰብና በማደረጃት ክፍያዉን እንደሚፈፅም ምላሽ ስለሰጠ እየተጠባበቅን እንገኛለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮን ምላሽም ጠይቋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቢዮት ደምሴ በቢሯቸዉና በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ እጅ ያለዉ የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ከ5 መቶ በላይ ሰዉ የቁጥር ልዩነት በማሳየቱ የማጣራቱ ስራ እስኪጠናቀቅ ክፍያው አለመፈፀሙን ተናግረዋል።

" አሁን ላይ ሁሉም ኮሌጆች መረጃዎችን አጠናቀዉ ወደ ፐብሊክ ሰርቪስ የመላኩ ስራ ስለተጠናቀቀ በአጭር ቀናት ዉስጥ ችግሩ ይፈታል " ሲቡ ያላቸዉን ሙሉ እምነት ገልፀዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክንክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ስር 35 ኮሌጆች መኖራቸዉን ከነዚህም ዉስጥ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ አረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ150 በላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94351
Create:
Last Update:

" ለቅሬታችን ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን ለርዕሰ መስተዳድሩ አቅርበናል " - የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መምህራን

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ክፍያ " አልተከፈለንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

በቁጥር ከአንድ መቶ በላይ የሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ የፃፉትንና የተፈራረሙበትን የቅሬታ ደብዳቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ሰራተኞቹ በሰጡት ቃልም " መንግስት ለኑሮ ዉድነት ማካካሻ በማለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1/2017ዓ/ም ጀምሮ ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም እስካሁን የማሻሻያዉ ልዩነት አልተከገለንም " ሲሉ ገልፀዋል።

" ስራ ሳናቆም ተደጋጋሚ ቅሬታ ስናቀርብ ቆይተናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ከዚህ ቀደም ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ አብዘኞቻችን የተሰጠንን የደረጃ ዕድገት ክፊያ ተግባራዊ አልተደረገም በዚያ ላይ ይህ ሲጨመርበት ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ " ብለዋል።

ኮሌጁ ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ?

የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጻድቁ ሳሙኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የደሞዝ ማሻሻያው አለመከፈሉ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።

" የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በክልሉ ያሉ የሁሉም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎችን መረጃ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በመሰብሰብና በማደረጃት ክፍያዉን እንደሚፈፅም ምላሽ ስለሰጠ እየተጠባበቅን እንገኛለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮን ምላሽም ጠይቋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቢዮት ደምሴ በቢሯቸዉና በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ እጅ ያለዉ የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ከ5 መቶ በላይ ሰዉ የቁጥር ልዩነት በማሳየቱ የማጣራቱ ስራ እስኪጠናቀቅ ክፍያው አለመፈፀሙን ተናግረዋል።

" አሁን ላይ ሁሉም ኮሌጆች መረጃዎችን አጠናቀዉ ወደ ፐብሊክ ሰርቪስ የመላኩ ስራ ስለተጠናቀቀ በአጭር ቀናት ዉስጥ ችግሩ ይፈታል " ሲቡ ያላቸዉን ሙሉ እምነት ገልፀዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክንክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ስር 35 ኮሌጆች መኖራቸዉን ከነዚህም ዉስጥ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ አረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ150 በላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA










Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94351

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Perpetrators of these scams will create a public group on Telegram to promote these investment packages that are usually accompanied by fake testimonies and sometimes advertised as being Shariah-compliant. Interested investors will be asked to directly message the representatives to begin investing in the various investment packages offered. Continuing its crackdown against entities allegedly involved in a front-running scam using messaging app Telegram, Sebi on Thursday carried out search and seizure operations at the premises of eight entities in multiple locations across the country. However, the perpetrators of such frauds are now adopting new methods and technologies to defraud the investors. Meanwhile, a completely redesigned attachment menu appears when sending multiple photos or vides. Users can tap "X selected" (X being the number of items) at the top of the panel to preview how the album will look in the chat when it's sent, as well as rearrange or remove selected media. Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more.
from tw


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American