TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ከኢሶዴፓ 9 የስራ አስፈፃሚ አባላት 6ቱ ተሰብስበው፣ ምክትል ሊቀመንበሯን ዶ/ር ራሔልን እና ነባሩን ማህተም አግደዋል "- የኢሶዴፓ ጊዜያዊ ሊቀመንበር ነኝ ያሉት አቶ አጫሞ ቦቄ
የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ/ሶዴፓ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባለፈው ሳምንት ማለትም ሰኔ 8/2017 ዓ.ም የፓርቲውን ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ራሔል ባፌን ማገዱን የሚያትት መግለጫ ተሰራጭቶ ነበር፡፡
የፓርቲው መሪ ዶ/ር ራሔል ባፌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል መግለጫው ቀደም ሲል በማዕከላዊ ኮሚቴ በታገዱ 4 የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት የተፃፈና በህገወጥ ማህተም የተዘጋጀ ነው ብለውታል፡፡
የእግድ መግለጫውን አዘጋጅተዋል ከተባሉት ሰዎች መካከል የሆኑትና በዚሁ መግለጫ ላይ በጊዜያዊ ሊቀመንበርነት መሾማቸው የተገለፀ አንድ አባል በበኩላቸው የዶ/ር ራሔል የመታገድ ውሳኔ በፓርቲው ህገደንብ መሰረት በስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ አባላት በአብላጫ ድምፅ መተላለፉን ተናግረዋል፡፡
የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ መሆናቸውን የተናገሩት አቶ አጫሞ ቦቄ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ዶ/ር ራሔል ከተሰጣቸው ሐላፊነት ውጭ እየተንቀሳቀሱ በመሆናቸውና ማህተሙንም ላልተገባ ተግባር እየተጠቀሙበት ስለሆነ " ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የእግድ ውሳኔውን አሳልፏል፣ አዲስ ማህተምም አስቀርፆዋል " ሲሉም ተናግረዋል፡፡
አቶ አጫሞ ቦቄ በዝርዝር ምን አሉ ?
" እኔ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ/ሶዴፓ የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ ነኝ፡፡ ቢያንስ 30 አመታት ለሚሆን ጊዜ ከፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ጋር በፓርቲው ውስጥ ሰርቻለሁ፡፡
ፓርቲውን ከብሔር ፓርቲነት ወደ ሀገርአቀፍ ፓርቲነት በማሸጋገሩ ሒደት ሚናዬን ተወጥቻለሁ፡፡ አንድ ፓርቲ የሚመራው በህገደንቡ መሰረት ነው፡፡ አደረጃጀቱንና ውሳኔ አሰጣጡን የሚወስነው ህገደንቡ ነው፡፡ እኛም የምንመራውና የምንሰራው በዚሁ ህገደንብ መሰረት ነው፡፡
የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት አሁን 9 ብቻ ነን፡፡ የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከማለፋቸው በፊትም 10 ነው የነበርነው፡፡ የአባላቱ ቁጥር 11 እንዲሆኑ ዶ/ር አወል አለማየሁ የሚባል ሰው ነሐሴ 20/ 2015 በተደረገ ጠቅላላ ጉባኤ ተመርጦ ነበር፡፡ ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች አልተቀላቀለንም፡፡
ፕሮፌሰር በየነ በሞት ከተለዩንም በኋላ መንግስቱ እና ወንድሙ የሚባሉ ሁለት ሰዎች እንዲቀላቀሉን ተጠቁመው ነበር፡፡ ነገር ግን ሁለቱ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች አልተቀላቀሉንም፡፡ ስለዚህ፣ ፕሮፌሰር እያሉ 10 ነበርን ከዛ በኋላ ግን እስከዛሬ ድረስ በፓርቲው 9 ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ነን ያለነው፡፡
መስከረም 28/2017 ዘጠኛችንም ዶ/ር ራሔል ሊቀመንበር እንድትሆን ተስማምተን ቃለጉባኤ ፈርመን ለምርጫ ቦርድ ልከናል፡፡ ነገር ግን ምርጫ ቦርድ አልተቀበለውም ውሳኔያችንን፡፡ ሽግሽግ አይቻልም አለን፡፡ በማዕከላዊ ምክር ቤት ምርጫ አድርጋችሁ ነው ሊቀመንበር የምትመርጡት አለን፡፡ ከዛ በኋላ በቃ በምክትል ሊቀመንበርነት ፓርቲውን ምሪ ብለን ተስማማን፡፡
9ኙ የስራ አስፈፃሚ አባላት ከፕሮፌሰር ህልፈት በኋላ አንዴ ብቻ ነው የተሰበሰብነው፡፡ ከዛ በኋላ ዶ/ር ራሔል ልትሰበስበን አልፈለገችም፡፡ ነገር ግን ስራ አስፈፃሚውን ሳትሰበስብ የተናጠል ውሳኔ ማሳለፍ ጀመረች፡፡ ለምሳሌ የስራ አስፈፃሚው ሳይነጋገር ፣ በጀት ሳያፀድቅ አጀንዳ ሳይዝ፣ የስብሰባ ቦታም ሳይመርጥ፣ በራሷ ውሳኔ ወላይታ ሶዶ ከተማ ላይ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ጠራች፡፡
በህገደንቡ መሰረት ግን ስራ አስፈፃሚው ስለስብሰባው ተወያይቶ መወሰን ነበረበት፡፡ ህገደንቡ ተጥሶ ስብሰባ ተጠርቷል ብለን አቤቱታ አቀረብን ለምርጫ ቦርድ፡፡
ከዘጠኝ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ስድስታችን ነን አቤቱታ ያቀረብነው፡፡ ሁለቱ አባላት በሀሳቡ ያልተስማሙ ናቸው የተባለው ትክክል አይደለም፡፡ ሁለቱ ሰዎች ራሳቸው መፈረማቸውን ለምርጫ ቦርድ አረጋግጠዋል፡፡ በህይወት ያሉ ናቸው ሊጠየቁ ይችላሉ፡፡ ከራሳቸው አንደበትም መስማት ይቻላል፡፡ ከሀሰት ፊርማ ጋር ተያይዞ በፖሊስ ሲፈለግ የነበረም ሆነ የተደበቀ ሰው የለም፡፡ እኔንም ያሳደደኝ ፖሊስ የለም፡፡
ምርጫ ቦርድ በበኩሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ማገድ አልችልም በማለቱ ስብሰባው ተጠራ፡፡ እኛም ወደ ስብሰባው ገብተን፣ ህገወጥ እንደሆነ ገልፀን ፖሊስ ጠርተን አስበተነው፡፡ ከተበተነ በኋላ ስድስት ሽማግሌዎች ተመርጠው አነጋገሩን፣ ስብሰባው ሌላ ቀን ይሁን ብለን ተስማምተን ወደቤታችን ገባን፡፡
ከዛ ዶ/ር ራሔል የተወሰኑትን አባላት አግባብታ በመሰብሰብ ማታ ላይ ቃለጉባኤ እንዲዘጋጅ አደረገች፡፡ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ በአራቱ ሰዎች ላይ እግድ አስተላልፏል ብላ የእገዳ ደብዳቤ ሰጠችን፡፡ ይህ ትክክል አልነበረም፡፡ማዕከላዊ ኮሚቴ የስራ አስፈፃሚ አባላትን የሚያግድባቸው በህገደንቡ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎች አሉ፡፡ እነሱን ያሟላ አይደለም እግዱ፡፡ እኛ የሰራነው ስህተት የለም፣ የአካሔድ ክፍተት ተፈጥሯል፣ የህገደንብ ጥሰት ተፈፅሟል ነው ያልነው፡፡
ከታገድን በኋላ ደግሞ አሁንም ስድስታችን ለሁለተኛ ጊዜ ለምርጫ ቦርድ አመለከትን፣ የተጣለብን እግድ ህገወጥ ነው ብለን ማለት ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ሚያዝያ 6/2017 ዓ.ም ውሳኔ ሰጠ፡፡
ወላይታ ሶዶ ላይ የተደረገው ስብሰባ ህገደንቡን የተከተለ አይደለም፣ የአባላት እግዱም ህገወጥ ነው ብሎ አነሳው፡፡ በፓርቲው አሰራር መሰረት ሁሉም ነገር ወደነበረበት ይመለስ አለ፡፡ ችግራችሁን በስራ አስፈፃሚ ውይይት ፍቱ አለን፡፡ እኛ ደግሞ ሰብስቢን ብለን ጠየቅን ዶ/ር ራሔልን፡፡ አሁንም ፈቃደኛ አልሆችም፡፡
ዶ/ር ራሔል ባፌ ከፓርቲው ህገደንብ በላይ ስላልሆነች ሰኔ 8/2017 ዓ.ም ከዘጠኙ ስራ አስፈፃሚ አባላት ስድስቱ ተሰብስበን የእግድ ውሳኔውን አሳልፈናል፡፡ ወደፊት ማዕከላዊ ኮሚቴው ተሰብስቦ በህገደንቡ መሰረት ሊቀመንበሩን እስኪመርጥ ድረስ እኔን ጊዜያዊ ሊቀመንበር አድርጎ መርጦኛል ስራ አስፈፃሚው፡፡ በስድስቱም ስራ አስስፃሚ አባላት ተመርጫለሁ፡፡
ማህተሙንም ዶ/ር ራሔል ለህገወጥ ተግባር ስትጠቀምበት ስለነበረ ቀይረነዋል፡፡ ነባሩን ማህተም በመጠቀም የተላለፉ ውሳኔዎች አሉ ወደፊት በህግ የሚያስጠይቁ ናቸው፡፡ ዶ/ር ራሔል ከታገደች በኋላ የፓርቲው ህልውና መቀጠል ስላለበት ስራ አስፈፃሚው አዲስ ማህተም እንዲቀረፅ አድርጓል፡፡
ይህን የእግድ ውሳኔ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳውቀናል፡፡ ለሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም አሳውቀናል፡፡ ምርጫ ቦርድ፣ የመተዳደሪያ ደንባችንን መርምሮና ፈትሾ ውሳኔያችንን ይቀበላል ብለን እንጠብቃለን፡፡ ቦርዱ የሚሰጠን ውሳኔ የማያረካ ከሆነ የመተዳደሪያ ደንባችንንና ሰነዶቻችንን ሰብስበን ወደ ፍርድ ቤት እንሔዳለን፡፡
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሐላፊዎችን የማገድ፣ የመሾምና የመሻር ስልጣን አልተሰጠውም የሚለው ትክክል አይደለም፡፡ በህገደንቡ አንቀፅ 14/6 ላይ ይህ ስልጣን በግልፅ ተቀምጧል። በዚህ አንቀፅ መሰረት ስራ አስፈፃሚው ሐላፊዎችን ማገድ ይችላል፡፡
ከዚህ በፊት የውስጥ ችግራችንን በውይይት ለመፍታት ሞክረናል በዶ/ር ራሔል እምቢተኝነት ሁሉም ጥረቶች አልተሳኩም፡፡ አሁንም ጉዳዩን በውይይት ለመፍታት ጥረት ማድረጋችንን እንቀጥላለን፣ ግን ደግሞ የሚሳኩ አይመስለኝም፡፡ ወደ ውይይት የምንመጣ ከሆነ ግን መጀመሪያ እኛንም፣ ሽማግሌዎችንም ይቅርታ መጠየቅ ይኖርባታል፣ ዶ/ር ራሔል ባፌ "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ/ሶዴፓ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባለፈው ሳምንት ማለትም ሰኔ 8/2017 ዓ.ም የፓርቲውን ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ራሔል ባፌን ማገዱን የሚያትት መግለጫ ተሰራጭቶ ነበር፡፡
የፓርቲው መሪ ዶ/ር ራሔል ባፌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል መግለጫው ቀደም ሲል በማዕከላዊ ኮሚቴ በታገዱ 4 የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት የተፃፈና በህገወጥ ማህተም የተዘጋጀ ነው ብለውታል፡፡
የእግድ መግለጫውን አዘጋጅተዋል ከተባሉት ሰዎች መካከል የሆኑትና በዚሁ መግለጫ ላይ በጊዜያዊ ሊቀመንበርነት መሾማቸው የተገለፀ አንድ አባል በበኩላቸው የዶ/ር ራሔል የመታገድ ውሳኔ በፓርቲው ህገደንብ መሰረት በስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ አባላት በአብላጫ ድምፅ መተላለፉን ተናግረዋል፡፡
የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ መሆናቸውን የተናገሩት አቶ አጫሞ ቦቄ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ዶ/ር ራሔል ከተሰጣቸው ሐላፊነት ውጭ እየተንቀሳቀሱ በመሆናቸውና ማህተሙንም ላልተገባ ተግባር እየተጠቀሙበት ስለሆነ " ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የእግድ ውሳኔውን አሳልፏል፣ አዲስ ማህተምም አስቀርፆዋል " ሲሉም ተናግረዋል፡፡
አቶ አጫሞ ቦቄ በዝርዝር ምን አሉ ?
" እኔ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ/ሶዴፓ የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ ነኝ፡፡ ቢያንስ 30 አመታት ለሚሆን ጊዜ ከፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ጋር በፓርቲው ውስጥ ሰርቻለሁ፡፡
ፓርቲውን ከብሔር ፓርቲነት ወደ ሀገርአቀፍ ፓርቲነት በማሸጋገሩ ሒደት ሚናዬን ተወጥቻለሁ፡፡ አንድ ፓርቲ የሚመራው በህገደንቡ መሰረት ነው፡፡ አደረጃጀቱንና ውሳኔ አሰጣጡን የሚወስነው ህገደንቡ ነው፡፡ እኛም የምንመራውና የምንሰራው በዚሁ ህገደንብ መሰረት ነው፡፡
የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት አሁን 9 ብቻ ነን፡፡ የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከማለፋቸው በፊትም 10 ነው የነበርነው፡፡ የአባላቱ ቁጥር 11 እንዲሆኑ ዶ/ር አወል አለማየሁ የሚባል ሰው ነሐሴ 20/ 2015 በተደረገ ጠቅላላ ጉባኤ ተመርጦ ነበር፡፡ ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች አልተቀላቀለንም፡፡
ፕሮፌሰር በየነ በሞት ከተለዩንም በኋላ መንግስቱ እና ወንድሙ የሚባሉ ሁለት ሰዎች እንዲቀላቀሉን ተጠቁመው ነበር፡፡ ነገር ግን ሁለቱ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች አልተቀላቀሉንም፡፡ ስለዚህ፣ ፕሮፌሰር እያሉ 10 ነበርን ከዛ በኋላ ግን እስከዛሬ ድረስ በፓርቲው 9 ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ነን ያለነው፡፡
መስከረም 28/2017 ዘጠኛችንም ዶ/ር ራሔል ሊቀመንበር እንድትሆን ተስማምተን ቃለጉባኤ ፈርመን ለምርጫ ቦርድ ልከናል፡፡ ነገር ግን ምርጫ ቦርድ አልተቀበለውም ውሳኔያችንን፡፡ ሽግሽግ አይቻልም አለን፡፡ በማዕከላዊ ምክር ቤት ምርጫ አድርጋችሁ ነው ሊቀመንበር የምትመርጡት አለን፡፡ ከዛ በኋላ በቃ በምክትል ሊቀመንበርነት ፓርቲውን ምሪ ብለን ተስማማን፡፡
9ኙ የስራ አስፈፃሚ አባላት ከፕሮፌሰር ህልፈት በኋላ አንዴ ብቻ ነው የተሰበሰብነው፡፡ ከዛ በኋላ ዶ/ር ራሔል ልትሰበስበን አልፈለገችም፡፡ ነገር ግን ስራ አስፈፃሚውን ሳትሰበስብ የተናጠል ውሳኔ ማሳለፍ ጀመረች፡፡ ለምሳሌ የስራ አስፈፃሚው ሳይነጋገር ፣ በጀት ሳያፀድቅ አጀንዳ ሳይዝ፣ የስብሰባ ቦታም ሳይመርጥ፣ በራሷ ውሳኔ ወላይታ ሶዶ ከተማ ላይ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ጠራች፡፡
በህገደንቡ መሰረት ግን ስራ አስፈፃሚው ስለስብሰባው ተወያይቶ መወሰን ነበረበት፡፡ ህገደንቡ ተጥሶ ስብሰባ ተጠርቷል ብለን አቤቱታ አቀረብን ለምርጫ ቦርድ፡፡
ከዘጠኝ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ስድስታችን ነን አቤቱታ ያቀረብነው፡፡ ሁለቱ አባላት በሀሳቡ ያልተስማሙ ናቸው የተባለው ትክክል አይደለም፡፡ ሁለቱ ሰዎች ራሳቸው መፈረማቸውን ለምርጫ ቦርድ አረጋግጠዋል፡፡ በህይወት ያሉ ናቸው ሊጠየቁ ይችላሉ፡፡ ከራሳቸው አንደበትም መስማት ይቻላል፡፡ ከሀሰት ፊርማ ጋር ተያይዞ በፖሊስ ሲፈለግ የነበረም ሆነ የተደበቀ ሰው የለም፡፡ እኔንም ያሳደደኝ ፖሊስ የለም፡፡
ምርጫ ቦርድ በበኩሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ማገድ አልችልም በማለቱ ስብሰባው ተጠራ፡፡ እኛም ወደ ስብሰባው ገብተን፣ ህገወጥ እንደሆነ ገልፀን ፖሊስ ጠርተን አስበተነው፡፡ ከተበተነ በኋላ ስድስት ሽማግሌዎች ተመርጠው አነጋገሩን፣ ስብሰባው ሌላ ቀን ይሁን ብለን ተስማምተን ወደቤታችን ገባን፡፡
ከዛ ዶ/ር ራሔል የተወሰኑትን አባላት አግባብታ በመሰብሰብ ማታ ላይ ቃለጉባኤ እንዲዘጋጅ አደረገች፡፡ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ በአራቱ ሰዎች ላይ እግድ አስተላልፏል ብላ የእገዳ ደብዳቤ ሰጠችን፡፡ ይህ ትክክል አልነበረም፡፡ማዕከላዊ ኮሚቴ የስራ አስፈፃሚ አባላትን የሚያግድባቸው በህገደንቡ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎች አሉ፡፡ እነሱን ያሟላ አይደለም እግዱ፡፡ እኛ የሰራነው ስህተት የለም፣ የአካሔድ ክፍተት ተፈጥሯል፣ የህገደንብ ጥሰት ተፈፅሟል ነው ያልነው፡፡
ከታገድን በኋላ ደግሞ አሁንም ስድስታችን ለሁለተኛ ጊዜ ለምርጫ ቦርድ አመለከትን፣ የተጣለብን እግድ ህገወጥ ነው ብለን ማለት ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ሚያዝያ 6/2017 ዓ.ም ውሳኔ ሰጠ፡፡
ወላይታ ሶዶ ላይ የተደረገው ስብሰባ ህገደንቡን የተከተለ አይደለም፣ የአባላት እግዱም ህገወጥ ነው ብሎ አነሳው፡፡ በፓርቲው አሰራር መሰረት ሁሉም ነገር ወደነበረበት ይመለስ አለ፡፡ ችግራችሁን በስራ አስፈፃሚ ውይይት ፍቱ አለን፡፡ እኛ ደግሞ ሰብስቢን ብለን ጠየቅን ዶ/ር ራሔልን፡፡ አሁንም ፈቃደኛ አልሆችም፡፡
ዶ/ር ራሔል ባፌ ከፓርቲው ህገደንብ በላይ ስላልሆነች ሰኔ 8/2017 ዓ.ም ከዘጠኙ ስራ አስፈፃሚ አባላት ስድስቱ ተሰብስበን የእግድ ውሳኔውን አሳልፈናል፡፡ ወደፊት ማዕከላዊ ኮሚቴው ተሰብስቦ በህገደንቡ መሰረት ሊቀመንበሩን እስኪመርጥ ድረስ እኔን ጊዜያዊ ሊቀመንበር አድርጎ መርጦኛል ስራ አስፈፃሚው፡፡ በስድስቱም ስራ አስስፃሚ አባላት ተመርጫለሁ፡፡
ማህተሙንም ዶ/ር ራሔል ለህገወጥ ተግባር ስትጠቀምበት ስለነበረ ቀይረነዋል፡፡ ነባሩን ማህተም በመጠቀም የተላለፉ ውሳኔዎች አሉ ወደፊት በህግ የሚያስጠይቁ ናቸው፡፡ ዶ/ር ራሔል ከታገደች በኋላ የፓርቲው ህልውና መቀጠል ስላለበት ስራ አስፈፃሚው አዲስ ማህተም እንዲቀረፅ አድርጓል፡፡
ይህን የእግድ ውሳኔ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳውቀናል፡፡ ለሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም አሳውቀናል፡፡ ምርጫ ቦርድ፣ የመተዳደሪያ ደንባችንን መርምሮና ፈትሾ ውሳኔያችንን ይቀበላል ብለን እንጠብቃለን፡፡ ቦርዱ የሚሰጠን ውሳኔ የማያረካ ከሆነ የመተዳደሪያ ደንባችንንና ሰነዶቻችንን ሰብስበን ወደ ፍርድ ቤት እንሔዳለን፡፡
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሐላፊዎችን የማገድ፣ የመሾምና የመሻር ስልጣን አልተሰጠውም የሚለው ትክክል አይደለም፡፡ በህገደንቡ አንቀፅ 14/6 ላይ ይህ ስልጣን በግልፅ ተቀምጧል። በዚህ አንቀፅ መሰረት ስራ አስፈፃሚው ሐላፊዎችን ማገድ ይችላል፡፡
ከዚህ በፊት የውስጥ ችግራችንን በውይይት ለመፍታት ሞክረናል በዶ/ር ራሔል እምቢተኝነት ሁሉም ጥረቶች አልተሳኩም፡፡ አሁንም ጉዳዩን በውይይት ለመፍታት ጥረት ማድረጋችንን እንቀጥላለን፣ ግን ደግሞ የሚሳኩ አይመስለኝም፡፡ ወደ ውይይት የምንመጣ ከሆነ ግን መጀመሪያ እኛንም፣ ሽማግሌዎችንም ይቅርታ መጠየቅ ይኖርባታል፣ ዶ/ር ራሔል ባፌ "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" አንድ አባት በታጣቂዎች ተገድለዋል። ቤታቸውንም አቃጥለውታል። ሁለቱ ይገደሉ ይኖሩ ገና አልታወቀም " - ዝቋላ አንድነት ገዳም በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን የሚገኘው ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም የ " ኦነግ ሸኔ ሠራዊት" ያላቸው ታጣቂዎች፤ " ገዳሙን እናጠፋለን " በሚል እቅድ በተደጋጋሚ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ። አርብ ምሽት ተከፈተ ባለው ጥቃት፣…
“ የተገደሉት አባት ለ12 ዓመት በብትውና የኖሩ ነበሩ። ቀብራቸው ተፈጽሟል። ጥቃት በተከፈተበት ዋሻ አካባቢ የነበሩ ሰባት አባቶችን ወደ ገዳሙ አምጥተናል ” - ደብረ ከዋክብት ዝቋላ ገዳም
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎም፤ “ ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ ግን በርካታ አባቶች ተገደሉ፤ ታግተው ተወሰዱ ” የሚል መረጃ በማህበራዊ ሚዲያው በሰፊው የተዘዋወረ ሲሆን በርካቶችን አሳዝኗል አስቆጥቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ በሰሞንኛው የታጣቂዎች ጥቃት የተገደሉት ምን ያህል አባቶች ናቸው ? ታግተው የተወሰዱስ አሉ እንዴ ? “ ይገደሉ ይኖሩ ገና አልታወቀም ” የተባለላቸው አባቶች ጉዳይስ ከምን ደረሰ ? ሲል ዛሬ ገደሙን ጠይቋል።
" 'ሁለት አባቶች ተገድለዋል' የሚል መረጃ ተሰራጭቶ ነበር፤ ይህን ያሉን አባቶች አንዱን አባት ከዋሻው ሲገድላቸው ሲያዩ ተደብቀው ቆይተው ሸኔዎቹ ሲሄዱላቸው ተኩስ ወደ ከተከፈተበት ዋሻ ሲመለሱ አንዱን አባት ሞተው አገኟቸው፤ ወደ ሁለተኛው አባት ዋሻ ሲሄዱ ግን አጧቸውና በተከታታይ ጥይት ተተኩሶ ስለነበር እሳቸውንም ገድለዋቸዋል በሚል 'ሁለት አባቶች ሞተዋል' ብለው ነገሩን " ሲል መልሷል።
" ነገር ግን ትላንት ዋሻው ድረስ ሂደን አይተን ስናረጋግጥ የሞቱት አንድ አባት ብቻ ናቸው። ሌላኛው 'ተገደሉ ተብለው የነበሩት አባት ደግሞ ሸኔዎቹን ሲያዩ ከዋሻቸው ወጥተው ተሰውረው ስለነበር በፍለጋ አግኝተናቸዋል" ሲል ገዳሙ ገልጷል።
የጥቃት ቀጠና በነበሩት የገዳሙ ዋሻዎች የነበሩ ሌሎች ሰባት አባቶችን ወደ ዋናው ገዳም አምጥተው ቦታ እንደሰጧቸው፣ የሞቱት አባት ደግሞ አምና ከተገደሉት አራት አባቶች አጠገብ የቀብር ሥርዓታቸው እንደፈጸመ ገዳሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
ሟቹ ባህታዊ አባ ኃይለሚካኤል በመጀመሪያ ገዳማቸው ማኀበረ ስላሴ፣ ዲሙ የሚባል በርሃ፣ ደብረ ሊባኖስ ገዳም እንዳገለገሉ፣ በኋላም በዝቋላ ገዳም ብዙ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተው ወደ ዋሻ ሂደው 12 ዓመት በብትህውና እንደኖሩ፣ ሰኔ 13 ቀን 2017 ዓ/ም በጥቃቱ ሰማዕትነት እንደተቀበሉ ተመላክቷል።
" የታገቱ አባቶች አሉ " ለሚለው መረጃስ እውነተኛ ነው ? ለሚለው ጥያቄ፣ " ታግተዋል ተብሎ የነበረው በአቅራቢያቸው የነበሩ አባቶች ከተኩስ በኋላ በዋሻቸው ሲያጧቸው ጊዜ የተናገሩት እንጂ የታገተ ሰው የለም " ሲል ገዳሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥቷል።
ሆኖም ግን አሁንም በዋሻ ያሉ አባቶችን፣ ታጣቂዎቹ፣ " 'እዚህ ሸኔ መጥቷል ብላችሁ ብትናገሩ ሙሉ ለሙሉ እንጨርሳችኋለን' በሚል ዝተውቸዋል" ብሎ፣ መንግስትና ህዝቡ ከለላ እንዲያደርግለት ዝቋላ ገዳም በአጽንኦት ጠይቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎም፤ “ ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ ግን በርካታ አባቶች ተገደሉ፤ ታግተው ተወሰዱ ” የሚል መረጃ በማህበራዊ ሚዲያው በሰፊው የተዘዋወረ ሲሆን በርካቶችን አሳዝኗል አስቆጥቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ በሰሞንኛው የታጣቂዎች ጥቃት የተገደሉት ምን ያህል አባቶች ናቸው ? ታግተው የተወሰዱስ አሉ እንዴ ? “ ይገደሉ ይኖሩ ገና አልታወቀም ” የተባለላቸው አባቶች ጉዳይስ ከምን ደረሰ ? ሲል ዛሬ ገደሙን ጠይቋል።
" 'ሁለት አባቶች ተገድለዋል' የሚል መረጃ ተሰራጭቶ ነበር፤ ይህን ያሉን አባቶች አንዱን አባት ከዋሻው ሲገድላቸው ሲያዩ ተደብቀው ቆይተው ሸኔዎቹ ሲሄዱላቸው ተኩስ ወደ ከተከፈተበት ዋሻ ሲመለሱ አንዱን አባት ሞተው አገኟቸው፤ ወደ ሁለተኛው አባት ዋሻ ሲሄዱ ግን አጧቸውና በተከታታይ ጥይት ተተኩሶ ስለነበር እሳቸውንም ገድለዋቸዋል በሚል 'ሁለት አባቶች ሞተዋል' ብለው ነገሩን " ሲል መልሷል።
" ነገር ግን ትላንት ዋሻው ድረስ ሂደን አይተን ስናረጋግጥ የሞቱት አንድ አባት ብቻ ናቸው። ሌላኛው 'ተገደሉ ተብለው የነበሩት አባት ደግሞ ሸኔዎቹን ሲያዩ ከዋሻቸው ወጥተው ተሰውረው ስለነበር በፍለጋ አግኝተናቸዋል" ሲል ገዳሙ ገልጷል።
የጥቃት ቀጠና በነበሩት የገዳሙ ዋሻዎች የነበሩ ሌሎች ሰባት አባቶችን ወደ ዋናው ገዳም አምጥተው ቦታ እንደሰጧቸው፣ የሞቱት አባት ደግሞ አምና ከተገደሉት አራት አባቶች አጠገብ የቀብር ሥርዓታቸው እንደፈጸመ ገዳሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
ሟቹ ባህታዊ አባ ኃይለሚካኤል በመጀመሪያ ገዳማቸው ማኀበረ ስላሴ፣ ዲሙ የሚባል በርሃ፣ ደብረ ሊባኖስ ገዳም እንዳገለገሉ፣ በኋላም በዝቋላ ገዳም ብዙ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተው ወደ ዋሻ ሂደው 12 ዓመት በብትህውና እንደኖሩ፣ ሰኔ 13 ቀን 2017 ዓ/ም በጥቃቱ ሰማዕትነት እንደተቀበሉ ተመላክቷል።
" የታገቱ አባቶች አሉ " ለሚለው መረጃስ እውነተኛ ነው ? ለሚለው ጥያቄ፣ " ታግተዋል ተብሎ የነበረው በአቅራቢያቸው የነበሩ አባቶች ከተኩስ በኋላ በዋሻቸው ሲያጧቸው ጊዜ የተናገሩት እንጂ የታገተ ሰው የለም " ሲል ገዳሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥቷል።
ሆኖም ግን አሁንም በዋሻ ያሉ አባቶችን፣ ታጣቂዎቹ፣ " 'እዚህ ሸኔ መጥቷል ብላችሁ ብትናገሩ ሙሉ ለሙሉ እንጨርሳችኋለን' በሚል ዝተውቸዋል" ብሎ፣ መንግስትና ህዝቡ ከለላ እንዲያደርግለት ዝቋላ ገዳም በአጽንኦት ጠይቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ከሟቾቹ አንዱ የሊስትሮ ስራ የሚሰራ ታዳጊ ነው " - ፖሊስ
በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ዛሬ ከቀኑ 7 ሰዓት አከባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 3 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ በ3 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሀብታሙ አስፋዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋዉ የደረሰዉ በሶዶ ከተማ በተለምዶ አጂፕ ከሚባል አከባቢ የተነሳዉ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ - 3 - 63419 ኢት የሆነ የፍሳሽ ማስወገጃ ተሽከርካሪ ከቁጥጥር ዉጪ በመሆን እስከ ማርያም ቤተክርስቲያን አጥር ድረስ በፍጥነት በመምጣት በመንገድ ላይ በነበሩ እግረኞች፣ በስራ ላይ የነበረ ሊስትሮ እንዲሁም ከቆሙ ተሽከርካሪዎች ጋር በመጋጨቱ ነው ብለዋል።
በአደጋዉ አንድ የሃይላክስ ሚኒባስ ረዳት፣ አንድ እግረኛ እና መንገድ ዳር ሊስትሮ ይሰራ የነበረ ወጣት በአጠቃላይ 3 ሰዎች ወዲያዉኑ ሕይወታቸዉ ሲያልፍ 3 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዉ በጤና ተቋም የህክምና ክትትል እየተደረገላቸዉ መሆኑን ተናግርዋል።
የተሽከርካሪዉ የቴክንክ ብልሽት የአደጋዉ መንስኤ ሊሆን እንደሚችል የገለፁት ፖሊስ አዛዡ አሽከርካሪውም ጉዳት ከደረሰባቸዉ 3 ሰዎች አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ዛሬ ከቀኑ 7 ሰዓት አከባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 3 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ በ3 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሀብታሙ አስፋዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋዉ የደረሰዉ በሶዶ ከተማ በተለምዶ አጂፕ ከሚባል አከባቢ የተነሳዉ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ - 3 - 63419 ኢት የሆነ የፍሳሽ ማስወገጃ ተሽከርካሪ ከቁጥጥር ዉጪ በመሆን እስከ ማርያም ቤተክርስቲያን አጥር ድረስ በፍጥነት በመምጣት በመንገድ ላይ በነበሩ እግረኞች፣ በስራ ላይ የነበረ ሊስትሮ እንዲሁም ከቆሙ ተሽከርካሪዎች ጋር በመጋጨቱ ነው ብለዋል።
በአደጋዉ አንድ የሃይላክስ ሚኒባስ ረዳት፣ አንድ እግረኛ እና መንገድ ዳር ሊስትሮ ይሰራ የነበረ ወጣት በአጠቃላይ 3 ሰዎች ወዲያዉኑ ሕይወታቸዉ ሲያልፍ 3 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዉ በጤና ተቋም የህክምና ክትትል እየተደረገላቸዉ መሆኑን ተናግርዋል።
የተሽከርካሪዉ የቴክንክ ብልሽት የአደጋዉ መንስኤ ሊሆን እንደሚችል የገለፁት ፖሊስ አዛዡ አሽከርካሪውም ጉዳት ከደረሰባቸዉ 3 ሰዎች አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
🚨 የጥበቃ ጊዜው አብቅቷል — Big 5 Construct Ethiopia እና የEast Africa Infrastructure and Water Expo የንግድ ትርዒት ነገ ይከፈታል!
በኢትዮጵያ ትልቁ በሆነውና ከሰኔ 19–21፣ 2017 ዓ.ም ድረስ በሚሊኒየም አዳራሽ፣ አዲስ አበባ በሚከናወነው የኮንስትራክሽን እና የመሠረተ ልማት የንግድ ትርዒት ላይ ተሳታፊ ይሁኑ።
ከ10,000+ ባለሙያዎች እና ልምድ ያላቸው ተቋማት
✅ ከ20 በላይ ሀገራት የተውጣጡ ከ180+ ተሳታፊ ኩባንያዎች
✅ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዕይታ የሚቀርቡ አዳዲስ ምርቶች
✅ 20+ የCPD ማረጋገጫ ያላቸው ትምህርታዊ ቆይታዎች በኮንስትራክሽን፣ መሠረተ ልማት እና ውኃ ጉዳዮች ላይ
✅ አስደሳች እና አሳታፊ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች
ያስታውሱ! ይህ ዓውደ ርዕይ፣ ለኮንስትራክሽን እና ለመሠረተ ልማት ባለሙያዎች የቀረበ ልዩ ዕድል ነው!
አሁኑኑ #በነፃ ይመዝገቡ፦
👉 https://www.big5constructethiopia.com/Tikvah_Ethiopia
📅 ሰኔ 19–21፣ 2017 ዓ.ም
📍 ሚሊኒየም አዳራሽ፣ አዲስ አበባ
በኢትዮጵያ ትልቁ በሆነውና ከሰኔ 19–21፣ 2017 ዓ.ም ድረስ በሚሊኒየም አዳራሽ፣ አዲስ አበባ በሚከናወነው የኮንስትራክሽን እና የመሠረተ ልማት የንግድ ትርዒት ላይ ተሳታፊ ይሁኑ።
ከ10,000+ ባለሙያዎች እና ልምድ ያላቸው ተቋማት
✅ ከ20 በላይ ሀገራት የተውጣጡ ከ180+ ተሳታፊ ኩባንያዎች
✅ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዕይታ የሚቀርቡ አዳዲስ ምርቶች
✅ 20+ የCPD ማረጋገጫ ያላቸው ትምህርታዊ ቆይታዎች በኮንስትራክሽን፣ መሠረተ ልማት እና ውኃ ጉዳዮች ላይ
✅ አስደሳች እና አሳታፊ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች
ያስታውሱ! ይህ ዓውደ ርዕይ፣ ለኮንስትራክሽን እና ለመሠረተ ልማት ባለሙያዎች የቀረበ ልዩ ዕድል ነው!
አሁኑኑ #በነፃ ይመዝገቡ፦
👉 https://www.big5constructethiopia.com/Tikvah_Ethiopia
📅 ሰኔ 19–21፣ 2017 ዓ.ም
📍 ሚሊኒየም አዳራሽ፣ አዲስ አበባ
ዋሪት ፈርኒቸር !
ክቡራን ደንበኞቻችን ምቾታቸውን እና ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶቻችንን እንደሁልጊዜው እርሶን ይጠብቃሉ ይምጡና ይሸምቱ!
ለእያንዳንዱ የሕይወት ምዕራፍ ምቾት የሚሰጡ
🚼የሕፃናት ትራሶች
🤰🏽የእርግዝና ትራስ
ቢን ባግ
🌊የውሃ ማጣሪያዎች
ወደ ማሳያ ክፍሎቻችንን በመምጣት ይጎብኙን !
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል * ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት * ፒያሳ- ፍርዱ ኮሜርሻል
*ወሎ ሰፈር- Ethiolife life real estate
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: ☎️ 0911210706 / 07
ክቡራን ደንበኞቻችን ምቾታቸውን እና ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶቻችንን እንደሁልጊዜው እርሶን ይጠብቃሉ ይምጡና ይሸምቱ!
ለእያንዳንዱ የሕይወት ምዕራፍ ምቾት የሚሰጡ
🚼የሕፃናት ትራሶች
🤰🏽የእርግዝና ትራስ
ቢን ባግ
🌊የውሃ ማጣሪያዎች
ወደ ማሳያ ክፍሎቻችንን በመምጣት ይጎብኙን !
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል * ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት * ፒያሳ- ፍርዱ ኮሜርሻል
*ወሎ ሰፈር- Ethiolife life real estate
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: ☎️ 0911210706 / 07
#ኢትዮጵያ🇪🇹
ኢትዮጵያ የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት የአባልነት ማረጋገጫ ተቀበለች።
ኢትዮጵያ 105 አገራትን ባቀፈው የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት (PKD) አባል መሆኗን የሚያረጋግጥ ሰርተፍኬት ከተቋሙ ዋና መቀመጫ ከሆነችው ካናዳ ሞንትሪያል ከሚገኘዉ አለም አቀፉ የሲቪል አቬሽን ተቋም ተቀብላለች።
ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ አባል መሆኗ የኢትዮጵያን ፓስፖርት የያዙ ዜጎች በአባል አገራቱ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ያለምንም እንግልት እንዲጓጓዙ የሚያስችል ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በየብስም ሆነ በአየር በተጭበረበረ የጉዞ ሰነድ ለመምጣት የሚሞክሩ አካላትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳና በአገር ላይ ሊቃጣ የሚችል የደህንነት ስጋትን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያግዝ ነው።
ኢትዮጵያ ወደዚህ ማዕቀፍ በይፋ መቀላቀሏን ተከትሎ የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት አባል አገራት ተወካዮችና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አካላት በተገኙበት አገሪቱ ያላትን ሁለንተናዊ አቅም የሚያስተዋውቅ መድረክ ተዘጋጅቷል።
በዚህ ወቅትም የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ገፅታ፣ የኢሚግሬሽን ስርዓትና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም የኢትዮጵያን የቱሪዝምና የቢዝነስ አቅሞች የሚያስተዋውቁ ገለፃዎች ተደርገዋል።
በስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት " ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ (PKD) አባል መሆኗ ዜጎች በሚሄዱበት አገር ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረጉ ባሻገር የአገርን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ይጫወታል " ብለዋል።
" ኢትዮጵያ ጠንካራ በሆነው የአለም አቀፍ አቪዬሽን ትብብር ስርዓት ውስጥ የላቀ ቴክኖሎጂን መጠቀሟ ድንበሯን ከመጠበቅ ባለፈ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የጋራ ደኅንነት መጠበቅ ያላትን ቁርጠኝነትም የሚያሳይ ውሳኔ ነው " ሱሉ ጠቁመዋል።
የካናዳ ትራንስፖርት ሚኒስትር ምክትል ሚኒስትር ኒኮላስ ሮብሰን " ኢትዮጵያ ወደዚህ ስርዓት በይፋ መቀላቀሏ በአቪዬሽን መስክ የምትሰራውን ስራ በዓለም የታመነ እንዲሆን ያደርጋል " ብለዋል።
" በተለይም በርካታ ዜጎችን ወደ ተለያዩ ክፍለ-ዓለማት የሚያጓጉዝ የግዙፍ አየር መንገድ ባለቤት በመሆኗ ይህን ማዕቀፍ መቀላቀሏ የሚደነቅ ውሳኔ ነው " ሲሉ ጠቁመዋል።
የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ፕሬዝዳንት ሳልቫቶሬ ሻኪታኖ ኢትዮጵያ ወደ ማዕቀፉ በመግባት የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ተቋማቸው የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
መረጃው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት የአባልነት ማረጋገጫ ተቀበለች።
ኢትዮጵያ 105 አገራትን ባቀፈው የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት (PKD) አባል መሆኗን የሚያረጋግጥ ሰርተፍኬት ከተቋሙ ዋና መቀመጫ ከሆነችው ካናዳ ሞንትሪያል ከሚገኘዉ አለም አቀፉ የሲቪል አቬሽን ተቋም ተቀብላለች።
ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ አባል መሆኗ የኢትዮጵያን ፓስፖርት የያዙ ዜጎች በአባል አገራቱ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ያለምንም እንግልት እንዲጓጓዙ የሚያስችል ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በየብስም ሆነ በአየር በተጭበረበረ የጉዞ ሰነድ ለመምጣት የሚሞክሩ አካላትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳና በአገር ላይ ሊቃጣ የሚችል የደህንነት ስጋትን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያግዝ ነው።
ኢትዮጵያ ወደዚህ ማዕቀፍ በይፋ መቀላቀሏን ተከትሎ የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት አባል አገራት ተወካዮችና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አካላት በተገኙበት አገሪቱ ያላትን ሁለንተናዊ አቅም የሚያስተዋውቅ መድረክ ተዘጋጅቷል።
በዚህ ወቅትም የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ገፅታ፣ የኢሚግሬሽን ስርዓትና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም የኢትዮጵያን የቱሪዝምና የቢዝነስ አቅሞች የሚያስተዋውቁ ገለፃዎች ተደርገዋል።
በስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት " ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ (PKD) አባል መሆኗ ዜጎች በሚሄዱበት አገር ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረጉ ባሻገር የአገርን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ይጫወታል " ብለዋል።
" ኢትዮጵያ ጠንካራ በሆነው የአለም አቀፍ አቪዬሽን ትብብር ስርዓት ውስጥ የላቀ ቴክኖሎጂን መጠቀሟ ድንበሯን ከመጠበቅ ባለፈ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የጋራ ደኅንነት መጠበቅ ያላትን ቁርጠኝነትም የሚያሳይ ውሳኔ ነው " ሱሉ ጠቁመዋል።
የካናዳ ትራንስፖርት ሚኒስትር ምክትል ሚኒስትር ኒኮላስ ሮብሰን " ኢትዮጵያ ወደዚህ ስርዓት በይፋ መቀላቀሏ በአቪዬሽን መስክ የምትሰራውን ስራ በዓለም የታመነ እንዲሆን ያደርጋል " ብለዋል።
" በተለይም በርካታ ዜጎችን ወደ ተለያዩ ክፍለ-ዓለማት የሚያጓጉዝ የግዙፍ አየር መንገድ ባለቤት በመሆኗ ይህን ማዕቀፍ መቀላቀሏ የሚደነቅ ውሳኔ ነው " ሲሉ ጠቁመዋል።
የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ፕሬዝዳንት ሳልቫቶሬ ሻኪታኖ ኢትዮጵያ ወደ ማዕቀፉ በመግባት የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ተቋማቸው የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
መረጃው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
" የአስራ ሁለት አመት ልጄን ነው በወባ በሽታ ያጣሁት " - አቶ ኦስማ አባመረሀባ በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ቆንዳላ ወረዳ ውስጥ ሁለት ህፃናትና አንድ አዋቂ በቱዋምቢ፣ ዲቾ እና ሹራ የተባሉ የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ በወባ በሽታ ህይወታቸው ማለፉን ነዋሪዎች እና የቤተሰብ አባላት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል። የቱዋምቢ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት አቶ ኦስማን አባመረሀባ የ12 ዓመት ልጃቸውን በወባ በሽታ…
" ሶስቱ ልጆቼ በወባ በሽታ ተይዘው በመንግስት የህክምና ተቋም መድሃኒት ማግኘት አልቻሉም " - አንድ የአካባቢው ነዋሪዎች
" መንግስት በነፃ መድሃኒቶችን አቅርቧል ህብረተሰቡ እጥረት አለ ካለ መጠቆም ይችላል " የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ
በኦሮሚያ ክልል በሶስት ዞኖች የወባ በሽታ ስርጭት መጨመሩን የኦሮምያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ተስፋዬ ከበበው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ዶክተር ተስፋዬ ከበበው ምን አሉ ?
የክረምቱን መግባት ተከትሎ በጅማ፣ ምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች ስርጭቱ በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል።
ሥርጭቱ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል የሞት ቁጥር ግን ቀንሷል።
በአሁን ወቅት በሳምንት ውስጥ በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከ1000 እስከ 2000 ሲሆን የሞት ቁጥር ደግሞ 1 ወይም ሁለት ነው። ይህ ቁጥር በክልል ደረጃ የተመዘገበ ነው።
የወባ በሽታ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያቀረቡት ቅሬታ ፦
" በቂ የመድሃኒት አቅርቦት በመንግስት የጤና ተቋም የለም " ሲሉ ነዋሪዎቹ ቅሬታ ያነሳሉ።
በምዕራብ ወለጋ ዞን የቆንዳላ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘሮ ጎልጃ ገርባ ሦስቱ ልጆቻቸው በወባ በሽታ ተይዘው በአካባቢው ባለው የመንግስት የህክምና ተቋም ቢሄዱም መድኃኃኒት እንዳላገኙ ተናግረዋል።
በተመሳሳይ የቄለም ወለጋ ዞን ዳሌ ዋበራ ወረዳ ነዋሪ አቶ ተወከል ከማል በወረዳው ገጠራማ ቀበሌዎች ውስጥ የሚኖሩ በርካታ ነዋሪዎች ለወባ በሽታ ተጋልጠዋል፤ ቀድሞ በመንግስት ተቋማት በነፃ ይሰጥ የነበረው የወባ መድሃኒት ከግል ተቋም በውድ ዋጋ ለመግዛት መገደዳቸውን ገልፀዋል።
ወደ ሌላ ቦታ ሂዶ ለመታከምም በአካባቢው ባለው ግጭት ምክንያት መንቀሳቀስ አለመቻሉን አክለዋል።
ነዋሪዎች ባቀረቡት ቅሬታ ዙሪያ የምክትል ቢሮ ኃላፊው ምን ምላሽ ሰጡ ?
በቂ የመድሃኒት አቅርቦት ለሁሉም ወረዳዎች ቀድመን ልከናል እስካሁን የመድሃኒት እጥረት መከሰቱን ሪፖርት ያደረገ ዞንም ወረዳም የለም።
የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች በየ ቀበሌው ካሉ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ጋር እንዲሰሩ ሶስት ሶስት የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ሰልጥነው አገልግሎት እየሰጡ ነው።
ህብረተሰቡ መንግስት በነፃ ያቀረበውን መድሃኒት ማግኘት ካልቻለ ለቢሮው ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ምክትል ጤና ቢሮ ኃላፊው ዶ/ር ተስፋዬ ክበበው ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
በሽታው እንዳይባባስ ቢሮው ምን እየሰራ ነው ?
የበሽታው ስርጭት ጎልቶ በታየባቸው አካባቢዎች 600 ሺህ የአልጋ አጎበር የተሰራጨ ሲሆን በተለይ በምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች 12 ወረዳዎች እና በኢሉ አባቦር 3 ወረዳዎች ውስጥ ለ400 ሽህ ቤቶች የኬሚካል ርጭት ስራዎች በቅርቡ እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamliyNekemte
@tikvahethiopia
" መንግስት በነፃ መድሃኒቶችን አቅርቧል ህብረተሰቡ እጥረት አለ ካለ መጠቆም ይችላል " የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ
በኦሮሚያ ክልል በሶስት ዞኖች የወባ በሽታ ስርጭት መጨመሩን የኦሮምያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ተስፋዬ ከበበው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ዶክተር ተስፋዬ ከበበው ምን አሉ ?
የክረምቱን መግባት ተከትሎ በጅማ፣ ምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች ስርጭቱ በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል።
ሥርጭቱ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል የሞት ቁጥር ግን ቀንሷል።
በአሁን ወቅት በሳምንት ውስጥ በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከ1000 እስከ 2000 ሲሆን የሞት ቁጥር ደግሞ 1 ወይም ሁለት ነው። ይህ ቁጥር በክልል ደረጃ የተመዘገበ ነው።
የወባ በሽታ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያቀረቡት ቅሬታ ፦
" በቂ የመድሃኒት አቅርቦት በመንግስት የጤና ተቋም የለም " ሲሉ ነዋሪዎቹ ቅሬታ ያነሳሉ።
በምዕራብ ወለጋ ዞን የቆንዳላ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘሮ ጎልጃ ገርባ ሦስቱ ልጆቻቸው በወባ በሽታ ተይዘው በአካባቢው ባለው የመንግስት የህክምና ተቋም ቢሄዱም መድኃኃኒት እንዳላገኙ ተናግረዋል።
በተመሳሳይ የቄለም ወለጋ ዞን ዳሌ ዋበራ ወረዳ ነዋሪ አቶ ተወከል ከማል በወረዳው ገጠራማ ቀበሌዎች ውስጥ የሚኖሩ በርካታ ነዋሪዎች ለወባ በሽታ ተጋልጠዋል፤ ቀድሞ በመንግስት ተቋማት በነፃ ይሰጥ የነበረው የወባ መድሃኒት ከግል ተቋም በውድ ዋጋ ለመግዛት መገደዳቸውን ገልፀዋል።
ወደ ሌላ ቦታ ሂዶ ለመታከምም በአካባቢው ባለው ግጭት ምክንያት መንቀሳቀስ አለመቻሉን አክለዋል።
ነዋሪዎች ባቀረቡት ቅሬታ ዙሪያ የምክትል ቢሮ ኃላፊው ምን ምላሽ ሰጡ ?
በቂ የመድሃኒት አቅርቦት ለሁሉም ወረዳዎች ቀድመን ልከናል እስካሁን የመድሃኒት እጥረት መከሰቱን ሪፖርት ያደረገ ዞንም ወረዳም የለም።
የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች በየ ቀበሌው ካሉ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ጋር እንዲሰሩ ሶስት ሶስት የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ሰልጥነው አገልግሎት እየሰጡ ነው።
ህብረተሰቡ መንግስት በነፃ ያቀረበውን መድሃኒት ማግኘት ካልቻለ ለቢሮው ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ምክትል ጤና ቢሮ ኃላፊው ዶ/ር ተስፋዬ ክበበው ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
በሽታው እንዳይባባስ ቢሮው ምን እየሰራ ነው ?
የበሽታው ስርጭት ጎልቶ በታየባቸው አካባቢዎች 600 ሺህ የአልጋ አጎበር የተሰራጨ ሲሆን በተለይ በምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች 12 ወረዳዎች እና በኢሉ አባቦር 3 ወረዳዎች ውስጥ ለ400 ሽህ ቤቶች የኬሚካል ርጭት ስራዎች በቅርቡ እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamliyNekemte
@tikvahethiopia
#ኦዲት
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ለቋሚ የሥራ ቅጥር መደቦች የቀን ሠራተኞችን በመቅጠር ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ መፈጸማቸው ተገለጸ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የመንግሥት ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት የበጀት ኦዲት አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርብ ነው የተገለጸው፡፡
ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በሪፖርቱ እንደጠቀሰው 12 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሳይፈቀድላቸው ለቋሚ የሥራ መደቦች ላይ የቀን ሠራተኞችን ቀጥረው ተገኝተዋል ብሏል።
ተቋማቱ በጠቅላላው 61,882,081 ብር ለቀን ሠራተኞች ክፍያ እንደፈጸሙ የገለጸው የፌዴራል ዋና ኦዲተር ፦
➡️ ጅማ ዩኒቨርሲቲ 25,310,211 ብር፣
➡️ አምቦ ዩኒቨርሲቲ 10,938,834 ብር፣
➡️ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 7,888,374 ብር፣
➡️ ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ 5,170,600 ብርና ዲላ ዩኒቨርሲቲ 4,414,974 ብር በመክፈል ዋነኞቹ እንደሆኑ በሪፖርቱ ተጠቅሰዋል፡፡
እንዲሁም 17 የመንግሥት ተቋማት በጡረታ፣ በሞትና በሌሎች ምክንያት ከሥራ ለለቀቁ ሠራተኞች 408,462 ብር ያላግባብ ደመወዝ መክፈለቸው በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ በስተቀር የሠራተኞች ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገትና ዝውውር እንዳይፈጸም ቢከለክልም በስምንት መሥሪያ ቤቶችና በአንድ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በጠቅላላው 24,073,003 ብር የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ ለቋሚ የሥራ መደቦች ሠራተኞችን በኮንትራት በመቅጠር ክፍያ ፈጽመዋል ተብሏል፡፡
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ የኮንትራት ቅጥር ከፈጸሙት ተቋማት መካከል ፦
- የቅደስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣
- ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ፣
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋነኞቹ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ በ2015 በጀት ዓመትና ከዚያ በፊት በተከናወኑ የኦዲት ሪፖርቶች መሠረት ዕርምጃ የተወሰደ መሆኑን ለማጣራት ኦዲት ሲደረግ በአጠቃላይ እንዲመለስ አስተያየት ከተሰጠበት 20.5 ቢሊዮን ብርና 23,230 ዶላር ውስጥ፣ የተመለሰው ሦስት ቢሊዮን ብርገደማ ብቻ መሆኑን የፌዴራል ዋና ኦዲተር አስታውቋል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች አገልግሎትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በአጠቃላይ 37,304,100 ብር የአገልግሎት ገቢ ተመናቸውና በሚመለከተው አካል ሳያፀድቁ ገቢ መሰብሰባቸውም ተገልጿል፡፡
እንዲሁም 28 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶችና ሰባት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች የፈጸሙት 348 ሚሊዮን ብር ክፍያ የተሟላ የወጪ ማስረጃ አልቀረበበትም ተብሏል።
የተሟላ የወጪ ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ ከተመዘገቡት መሥሪያ ቤቶች መካከል የጤና ሚኒስቴር፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና የቤተ መንግሥት አስተዳደር ዋነኞቹ ናቸው።
በ70 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶችና በሰባት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ከ404 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግሥትን የግዥ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ግዥ ተፈጽሞ መገኘቱን ዋና ኦዲተር ገልጿል።
- ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣
- የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣
- የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽንና አርሲ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ከሕግ ውጪ ግዥ ከፈጸሙ ተቋማት መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
ስምንት ተቋማት ደግሞ በጠቅላላው ከ6.5 ሚሊዮን በላይ ብር ዋጋ ያላቸውና ተገዝተዋል የተባሉ ንብረቶች እስካሁን ገቢ እንዳላደረጉ ሲገለጽ የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ የቤተ መንግሥት አስተዳደርና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ግዥውን ፈጽመው ዕቃዎቹን ገቢ ያላደረጉ
እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት 20 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶች ከተመደበላቸው ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ ሳይጠቀሙበት ወደ መንግሥት ካዝና ተመላሽ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የዚህ መረጃ ባለቤት ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ለቋሚ የሥራ ቅጥር መደቦች የቀን ሠራተኞችን በመቅጠር ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ መፈጸማቸው ተገለጸ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የመንግሥት ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት የበጀት ኦዲት አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርብ ነው የተገለጸው፡፡
ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በሪፖርቱ እንደጠቀሰው 12 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሳይፈቀድላቸው ለቋሚ የሥራ መደቦች ላይ የቀን ሠራተኞችን ቀጥረው ተገኝተዋል ብሏል።
ተቋማቱ በጠቅላላው 61,882,081 ብር ለቀን ሠራተኞች ክፍያ እንደፈጸሙ የገለጸው የፌዴራል ዋና ኦዲተር ፦
➡️ ጅማ ዩኒቨርሲቲ 25,310,211 ብር፣
➡️ አምቦ ዩኒቨርሲቲ 10,938,834 ብር፣
➡️ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 7,888,374 ብር፣
➡️ ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ 5,170,600 ብርና ዲላ ዩኒቨርሲቲ 4,414,974 ብር በመክፈል ዋነኞቹ እንደሆኑ በሪፖርቱ ተጠቅሰዋል፡፡
እንዲሁም 17 የመንግሥት ተቋማት በጡረታ፣ በሞትና በሌሎች ምክንያት ከሥራ ለለቀቁ ሠራተኞች 408,462 ብር ያላግባብ ደመወዝ መክፈለቸው በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ በስተቀር የሠራተኞች ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገትና ዝውውር እንዳይፈጸም ቢከለክልም በስምንት መሥሪያ ቤቶችና በአንድ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በጠቅላላው 24,073,003 ብር የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ ለቋሚ የሥራ መደቦች ሠራተኞችን በኮንትራት በመቅጠር ክፍያ ፈጽመዋል ተብሏል፡፡
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ የኮንትራት ቅጥር ከፈጸሙት ተቋማት መካከል ፦
- የቅደስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣
- ሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ፣
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋነኞቹ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ በ2015 በጀት ዓመትና ከዚያ በፊት በተከናወኑ የኦዲት ሪፖርቶች መሠረት ዕርምጃ የተወሰደ መሆኑን ለማጣራት ኦዲት ሲደረግ በአጠቃላይ እንዲመለስ አስተያየት ከተሰጠበት 20.5 ቢሊዮን ብርና 23,230 ዶላር ውስጥ፣ የተመለሰው ሦስት ቢሊዮን ብርገደማ ብቻ መሆኑን የፌዴራል ዋና ኦዲተር አስታውቋል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች አገልግሎትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በአጠቃላይ 37,304,100 ብር የአገልግሎት ገቢ ተመናቸውና በሚመለከተው አካል ሳያፀድቁ ገቢ መሰብሰባቸውም ተገልጿል፡፡
እንዲሁም 28 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶችና ሰባት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች የፈጸሙት 348 ሚሊዮን ብር ክፍያ የተሟላ የወጪ ማስረጃ አልቀረበበትም ተብሏል።
የተሟላ የወጪ ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ ከተመዘገቡት መሥሪያ ቤቶች መካከል የጤና ሚኒስቴር፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና የቤተ መንግሥት አስተዳደር ዋነኞቹ ናቸው።
በ70 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶችና በሰባት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ከ404 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግሥትን የግዥ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ግዥ ተፈጽሞ መገኘቱን ዋና ኦዲተር ገልጿል።
- ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣
- የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣
- የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽንና አርሲ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ከሕግ ውጪ ግዥ ከፈጸሙ ተቋማት መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
ስምንት ተቋማት ደግሞ በጠቅላላው ከ6.5 ሚሊዮን በላይ ብር ዋጋ ያላቸውና ተገዝተዋል የተባሉ ንብረቶች እስካሁን ገቢ እንዳላደረጉ ሲገለጽ የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ የቤተ መንግሥት አስተዳደርና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ግዥውን ፈጽመው ዕቃዎቹን ገቢ ያላደረጉ
እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት 20 የፌዴራል መሥሪያ ቤቶች ከተመደበላቸው ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ ሳይጠቀሙበት ወደ መንግሥት ካዝና ተመላሽ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የዚህ መረጃ ባለቤት ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia