Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94094-94095-94096-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94096 -
Telegram Group & Telegram Channel
" ' ብር (ጉቦ) ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ " - ቅሬታ አቅራቢዎች

በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ሳይት 3 የብሎክ 734 እና 735 ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገቡት የቆጣሪ እዳ ውዝግብ ምክንያት ሃይል ከተቋረጠባቸው 1 ወር ከ 5 ቀን መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጠቀሱት ብሎኮች ሃይል ያቋረጠው " በሦስት ቆጣሪዎች ያልተከፈለኝ ከ160 ሺ ብር በላይ እዳ አለ " በማለቱ ምክንያት ነው።

ቆጣሪዎቹ የተተከሉት ሳይቶቹ በግንባታ ላይ በነበሩበት ወቅት የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገባው ውል ሲሆን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት ደግሞ ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ውል በገባው እና ግንባታዎቹን ባከናወነው የስራ ተቋራጭ (ኮንትራክተር) ስም ነው።

" ይህ በሆነበት ሁኔታ ቆጣሪዎቹን ባልተረከብንበት እና ከእነዚህም ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለን ባልተጠቀምንበት ሁኔታ እዳውን ክፈሉ ተብለናል " ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተዋል።

" የመኖሪያ መንደሩ በግንባታ ላይ በነበረበት ወቅት የስራ ተቋራጩ (ኮንትራክተሩ) የተጠቀማቸው እና ግንባታቸው ተጠናቆ ከገባን በኋላም እንዲነሱ ባልተደረጉ ቆጣሪዎች ምክንያት የቆጣሪዎቹን የተጠራቀመ የክፍያ እዳ ክፈሉ ተብለናል ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆናችንም ምክንያት ላለፈው አንድ ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ ሃይል ታቋርጦብናል" ነው ያሉት።

በሁለቱ ብሎኮች ከ60 በላይ ነዋሪዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛኛዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ በሚገኙ የልማት ሥራዎች ምክንያት የተነሱ እና ከሁለት ዓመት እስከ ሁለት ወር ለሚሆን ጊዜ ገብተው መኖር የጀመሩ ናቸው።

ነዋሪዎቹ ቅሬታቸውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ያሳወቁ ሲሆን ጽ/ቤቶቹም ሃይል እንዲመለስላቸው የሚጠይቅ ደብዳቤ በተናጠል ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽፈዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው እና በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ኢ/ር በላይ ሞቱማ ተፈርሞ በ07/05/17 ዓም የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ብሎኮቹን የገነባው ኮንትራክተር ቆጣሪዎቹን ከኮርፖሬሽኑ መረከቡን ከግንባታው በኋላም እነዚህን ቆጣሪዎች ከኮንትራክተሩ በመረከብ ለነዋሪዎች አለመተላለፉን እና አሁንም በኮንትራክተሩ የተመዘገበ መሆኑን ይገልጻል።

በዚህም ምክንያት ከቆጣሪው ጋር ተያይዞ የሚመጣ እዳ ሁሉ ኮንትራክተሩን እንጂ ነዋሪዎችን እንደማይመለከት በማስረዳት አስፈላጊውን ህጋዊ ድጋፍ ይደረግላቸው ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጠይቋል።

የለሚኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በበኩሉ በ 09/05/17 ዓም በጻፈው ደብዳቤ  የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የጻፈውን ደብዳቤ በመጥቀስ ለነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ እንዲደርግ እንገልጻለን ብሏል።

ሁለቱም ጽ/ቤቶች በተናጠል በጻፉት ደብዳቤ ሃይል የተቋረጠባቸው ነዋሪዎች  የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ቢጠይቁም አገልግሎቱ ሃይሉን ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ላለፉት አንድ ወር በላይ በጨለማ ለመቀመጥ መገደዳቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ነዋሪዎች በዝርዝር ባቀረቡት ቅሬታ ምን አሉ ?

" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጠራቀመውን እዳ ኮንትራክተሩን ፈልጋቹ አስከፍሉ ወይም የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እዳውን እንዲከፍል አድርጉ እያለን ነው እነሱ በተዋዋሉት እኛ የምንጠየቀው ለምንድነው ?

መንገድ ላይ ያሉ ቆጣሪዎች እንዲነሱ ማህበረሰቡ ከአመት በፊት ጀምሮ አቤቱታ እያቀረበ ነው ያለው አልተሰማንም ቆጣሪዎቹ ሃይል አልተቋረጠባቸውም፣ አላነሳቸውም እኛ ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል አልቀጠልንም።

በዚህም ምክንያት ተዋውለን ለብሎካችን ያስገባነውን ስሪ ፌዝ ቆጣሪ ሃይል አቋረጡብን ለምን ? ስንል የዛኛውን ቆጣሪ እዳ ካልከፈላቹ ተባልን ባልገባነው ውል ባልተጠቀምንበት ሃይል ክፈሉ ተብለን ለምን እንገደዳለን ? እዳው የተመዘገበው በኮንትራክተሩ ነው እኛ ለምንድነው የምንከፍለው።

ምግብ ለማብሰል እንጨት እና ከሰል ነው እየተጠቀምን ያለነው ተማሪዎች አሉ የሚመገቡትን ትተን ፈተና የሚፈተኑበት ጊዜ እንደመሆኑ ያጥኑ እንኳን ቢባል በምን ? ለተጨማሪ እና አላስፈላጊ ለሆነ ወጪ ነው የተዳረግነው።

ፊዩዝ በተደጋጋሚ እያመጡ እየነቀሉ እያዋጣን መክፈል ሥራ ሆነብን ሲበዛብን ከወር በፊት ሊነቅል የመጣውን ሰራተኛ ለማስቆም ሞከርን ለምን ታስቆሙታላቹ በሚል አጠፉብን በዚህ ምክንያት እየተበቀሉን ነው እስካሁን መብራት የለንም።

እያዋጣን ጉቦ መክፈል ሰልችቶናል ' ብር ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ ይሄንን እና ሌሎች ነገሮች ስላሳወቅንባቸው ሌሎች ተመሳሳይ የሆኑ ቆጣሪ ያለባቸው ሳይቶች ላይ እንደዚህ አይነት እርምጃ ሳይወሰድ እኛ ላይ የተደረገው ለብቀላ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፣የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እና የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በጉዳዩ ላይ የሰጡት ምላሽ በቀጣይ ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94096
Create:
Last Update:

" ' ብር (ጉቦ) ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ " - ቅሬታ አቅራቢዎች

በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ሳይት 3 የብሎክ 734 እና 735 ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገቡት የቆጣሪ እዳ ውዝግብ ምክንያት ሃይል ከተቋረጠባቸው 1 ወር ከ 5 ቀን መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጠቀሱት ብሎኮች ሃይል ያቋረጠው " በሦስት ቆጣሪዎች ያልተከፈለኝ ከ160 ሺ ብር በላይ እዳ አለ " በማለቱ ምክንያት ነው።

ቆጣሪዎቹ የተተከሉት ሳይቶቹ በግንባታ ላይ በነበሩበት ወቅት የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገባው ውል ሲሆን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት ደግሞ ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ውል በገባው እና ግንባታዎቹን ባከናወነው የስራ ተቋራጭ (ኮንትራክተር) ስም ነው።

" ይህ በሆነበት ሁኔታ ቆጣሪዎቹን ባልተረከብንበት እና ከእነዚህም ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለን ባልተጠቀምንበት ሁኔታ እዳውን ክፈሉ ተብለናል " ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተዋል።

" የመኖሪያ መንደሩ በግንባታ ላይ በነበረበት ወቅት የስራ ተቋራጩ (ኮንትራክተሩ) የተጠቀማቸው እና ግንባታቸው ተጠናቆ ከገባን በኋላም እንዲነሱ ባልተደረጉ ቆጣሪዎች ምክንያት የቆጣሪዎቹን የተጠራቀመ የክፍያ እዳ ክፈሉ ተብለናል ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆናችንም ምክንያት ላለፈው አንድ ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ ሃይል ታቋርጦብናል" ነው ያሉት።

በሁለቱ ብሎኮች ከ60 በላይ ነዋሪዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛኛዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ በሚገኙ የልማት ሥራዎች ምክንያት የተነሱ እና ከሁለት ዓመት እስከ ሁለት ወር ለሚሆን ጊዜ ገብተው መኖር የጀመሩ ናቸው።

ነዋሪዎቹ ቅሬታቸውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ያሳወቁ ሲሆን ጽ/ቤቶቹም ሃይል እንዲመለስላቸው የሚጠይቅ ደብዳቤ በተናጠል ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽፈዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው እና በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ኢ/ር በላይ ሞቱማ ተፈርሞ በ07/05/17 ዓም የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ብሎኮቹን የገነባው ኮንትራክተር ቆጣሪዎቹን ከኮርፖሬሽኑ መረከቡን ከግንባታው በኋላም እነዚህን ቆጣሪዎች ከኮንትራክተሩ በመረከብ ለነዋሪዎች አለመተላለፉን እና አሁንም በኮንትራክተሩ የተመዘገበ መሆኑን ይገልጻል።

በዚህም ምክንያት ከቆጣሪው ጋር ተያይዞ የሚመጣ እዳ ሁሉ ኮንትራክተሩን እንጂ ነዋሪዎችን እንደማይመለከት በማስረዳት አስፈላጊውን ህጋዊ ድጋፍ ይደረግላቸው ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጠይቋል።

የለሚኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በበኩሉ በ 09/05/17 ዓም በጻፈው ደብዳቤ  የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የጻፈውን ደብዳቤ በመጥቀስ ለነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ እንዲደርግ እንገልጻለን ብሏል።

ሁለቱም ጽ/ቤቶች በተናጠል በጻፉት ደብዳቤ ሃይል የተቋረጠባቸው ነዋሪዎች  የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ቢጠይቁም አገልግሎቱ ሃይሉን ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ላለፉት አንድ ወር በላይ በጨለማ ለመቀመጥ መገደዳቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ነዋሪዎች በዝርዝር ባቀረቡት ቅሬታ ምን አሉ ?

" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጠራቀመውን እዳ ኮንትራክተሩን ፈልጋቹ አስከፍሉ ወይም የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እዳውን እንዲከፍል አድርጉ እያለን ነው እነሱ በተዋዋሉት እኛ የምንጠየቀው ለምንድነው ?

መንገድ ላይ ያሉ ቆጣሪዎች እንዲነሱ ማህበረሰቡ ከአመት በፊት ጀምሮ አቤቱታ እያቀረበ ነው ያለው አልተሰማንም ቆጣሪዎቹ ሃይል አልተቋረጠባቸውም፣ አላነሳቸውም እኛ ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል አልቀጠልንም።

በዚህም ምክንያት ተዋውለን ለብሎካችን ያስገባነውን ስሪ ፌዝ ቆጣሪ ሃይል አቋረጡብን ለምን ? ስንል የዛኛውን ቆጣሪ እዳ ካልከፈላቹ ተባልን ባልገባነው ውል ባልተጠቀምንበት ሃይል ክፈሉ ተብለን ለምን እንገደዳለን ? እዳው የተመዘገበው በኮንትራክተሩ ነው እኛ ለምንድነው የምንከፍለው።

ምግብ ለማብሰል እንጨት እና ከሰል ነው እየተጠቀምን ያለነው ተማሪዎች አሉ የሚመገቡትን ትተን ፈተና የሚፈተኑበት ጊዜ እንደመሆኑ ያጥኑ እንኳን ቢባል በምን ? ለተጨማሪ እና አላስፈላጊ ለሆነ ወጪ ነው የተዳረግነው።

ፊዩዝ በተደጋጋሚ እያመጡ እየነቀሉ እያዋጣን መክፈል ሥራ ሆነብን ሲበዛብን ከወር በፊት ሊነቅል የመጣውን ሰራተኛ ለማስቆም ሞከርን ለምን ታስቆሙታላቹ በሚል አጠፉብን በዚህ ምክንያት እየተበቀሉን ነው እስካሁን መብራት የለንም።

እያዋጣን ጉቦ መክፈል ሰልችቶናል ' ብር ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ ይሄንን እና ሌሎች ነገሮች ስላሳወቅንባቸው ሌሎች ተመሳሳይ የሆኑ ቆጣሪ ያለባቸው ሳይቶች ላይ እንደዚህ አይነት እርምጃ ሳይወሰድ እኛ ላይ የተደረገው ለብቀላ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፣የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እና የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በጉዳዩ ላይ የሰጡት ምላሽ በቀጣይ ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94096

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram was founded in 2013 by two Russian brothers, Nikolai and Pavel Durov. So, uh, whenever I hear about Telegram, it’s always in relation to something bad. What gives? He adds: "Telegram has become my primary news source." But Kliuchnikov, the Ukranian now in France, said he will use Signal or WhatsApp for sensitive conversations, but questions around privacy on Telegram do not give him pause when it comes to sharing information about the war. The Dow Jones Industrial Average fell 230 points, or 0.7%. Meanwhile, the S&P 500 and the Nasdaq Composite dropped 1.3% and 2.2%, respectively. All three indexes began the day with gains before selling off.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American