Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
“ በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ብዙ ድልድዮች ዘላቂነት ያላቸው አይደሉም የብረት ናቸው። ወደ ኮንክሪት እንዲቀየሩ ጥያቄ እያቀረብን ነው ” - የሰሜን ወሎ ዞን መንገድ መምሪያ

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን የሚገኘውና ከባድ ጭነት ያየዘ ተሳቢ ሲጓዝበት ትላንት የተሰበረው ብረት ድልድይ በኮንክሪት መሰራት እንደሚገባው፣ ይህንንም ለፌደራል አካላት ማሳሰቡን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የድልድዩ መሰበር ያስከተለውን የትራንስፓርት እንቅስቃሴ መስተጓጎል ለመቅረፍ ምን እየተሰራ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበው ጥያቄም፣ ለጊዜው ተለዋጭ መንገድ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ መንገድ መምሪያ ገልጿል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ፀሐይነው ሲሳይ ምን አሉ?

“ትላንት ከሰዓት በኋላ የተሰበረው መንገዱ ከወልዲያ ቆቦ አላማጣ ቆቦ የሚያዘልቅ፣ ከትግራይ ክልል የሚያገናኝ፣ ከፍተኛ ትራፊክ የሚተላለፍበት መንገድ ነው።

ከፍተኛ ጭነት የጫነ ተሳቢ መኪና ሲጓዝበት የብረት ድልድዩ ከነመኪናው ታጥፏል። የፌደራል መንገድ ስለሆነ ጉዳዩን ለሚመለከታቸው አካላት አድርሰናል።

በሰዓቱም ችግር እንዳይፈጠር ተራ የሚያስጠብቁ አካላት እንዲያውቁት ተደርጎ ሥራ እየተሰራ ቆይቷል። ትላንትና ህብረተሰቡ እንዳይጉላላ በቅብብሎሽ ሰው እንዲተላለፍ ጥረት አድርገናል። 

መንገዱ አስቸኳይና ተለዋጭ መንገድ ስለሌለው ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ማሽን መድቦ በሰዓቱ ደርሷል። ሥራም ጀምሯል። ተለዋጭ መንገድ ከፈታ እየተደረገ ነው። ከፈታው አልተጠናቀቀም።

አሁን እየተሰራ ነው። የትራፊክ መጨናነቁን በከፈታው ትንሽ ማስተንፈስ ተችሏል። ሥራው እንደቀጠለ ነው። ግን ዘላቂ ነው ማለት አይቻልም። ለጊዜው ካጋጠመው ችግር አኳያ ነው ተለዋጭ መንገድ እየተሰራ ያለው”
ብለዋል።

አደጋው የደረሰው ተሽከርካሪው ከመጠን በላይ ጭኖ ነው ወይስ የድልድዩ የጥራት ችግር ነው? ስንል ላቀረብነው ተጨማሪ ጥያቄም ምላሽ ያሉትን ነግረውናል።

ምን መለሱ?

“በሚመለከታቸው ባለሙያዎች እናሳያለን። ግን ጭነቱም ክብደት እንዳለው ያሳያል። ተሽከርካሪው የድንጋይ ከሰል ነው ተጭኖ ወደ ድልድዩ የገባው የጭንት ክብደት ሊኖር እንደሚችል ያሳያል።

የሌላም ከሆነ ይታያል። በዋናነት ግን ድልድዩም ቢሆን የብረት ድልድይ ነው። ለስምንት ዓመታት አገልገልግሏል።

ይህ ብቻ ሳይሆን አካባቢው፣ በዚሁ በቀጠናችን በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ብዙ ድልድዮች ዘላቂነት ያላቸው አይደሉም የብረት ናቸው። ወደ ኮንክሪት እንዲቀየሩ ጥያቄ እያቀረብን ነው። ሌሎችም የሚያሰጉን ይኖራሉ”
ነው ያሉት።

ይሄው ድልድይ በሰሜኑ ጦርነት የመሰበር አደጋ ደርሶበት ነበር እንዴ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ “ይሄኛው ሳይሆን አላውሃ ድልድይ ነበር ጉዳት የደረሰበት። እሱም የብረት ነው። ይሄም እዛው ቀጥሎ ያለ ነው” ብለዋል።

አሁን የመሰበር አደጋ የደረሰበት ድልድይ ለመጠገን ምን ያክል ወጪ እንደሚጠይቅ ስንጠይቃቸው ደግሞ፣ “እኛ ሥራ እንዲሰራ ነው ጥያቄ እያቀረብን ያለነው። ርዝመቱ ከ48 እስከ 50 ሜትር ነው” ሲሉ አስረድተዋል።

“ቀላል ወጪ ይጠይቃል ተብሎ አይታሰብም። ምንም ቢሆን ከመሰራት ውጪ አማራጭ የለውም። ፌደራል ተለዋጭ መንገድ የለውም። መንገዱ ክልልን ከክልል፣ ወረዳዎችን ከዞን የሚያገናኝ ነው” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94268
Create:
Last Update:

“ በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ብዙ ድልድዮች ዘላቂነት ያላቸው አይደሉም የብረት ናቸው። ወደ ኮንክሪት እንዲቀየሩ ጥያቄ እያቀረብን ነው ” - የሰሜን ወሎ ዞን መንገድ መምሪያ

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን የሚገኘውና ከባድ ጭነት ያየዘ ተሳቢ ሲጓዝበት ትላንት የተሰበረው ብረት ድልድይ በኮንክሪት መሰራት እንደሚገባው፣ ይህንንም ለፌደራል አካላት ማሳሰቡን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የድልድዩ መሰበር ያስከተለውን የትራንስፓርት እንቅስቃሴ መስተጓጎል ለመቅረፍ ምን እየተሰራ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበው ጥያቄም፣ ለጊዜው ተለዋጭ መንገድ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ መንገድ መምሪያ ገልጿል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ፀሐይነው ሲሳይ ምን አሉ?

“ትላንት ከሰዓት በኋላ የተሰበረው መንገዱ ከወልዲያ ቆቦ አላማጣ ቆቦ የሚያዘልቅ፣ ከትግራይ ክልል የሚያገናኝ፣ ከፍተኛ ትራፊክ የሚተላለፍበት መንገድ ነው።

ከፍተኛ ጭነት የጫነ ተሳቢ መኪና ሲጓዝበት የብረት ድልድዩ ከነመኪናው ታጥፏል። የፌደራል መንገድ ስለሆነ ጉዳዩን ለሚመለከታቸው አካላት አድርሰናል።

በሰዓቱም ችግር እንዳይፈጠር ተራ የሚያስጠብቁ አካላት እንዲያውቁት ተደርጎ ሥራ እየተሰራ ቆይቷል። ትላንትና ህብረተሰቡ እንዳይጉላላ በቅብብሎሽ ሰው እንዲተላለፍ ጥረት አድርገናል። 

መንገዱ አስቸኳይና ተለዋጭ መንገድ ስለሌለው ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ማሽን መድቦ በሰዓቱ ደርሷል። ሥራም ጀምሯል። ተለዋጭ መንገድ ከፈታ እየተደረገ ነው። ከፈታው አልተጠናቀቀም።

አሁን እየተሰራ ነው። የትራፊክ መጨናነቁን በከፈታው ትንሽ ማስተንፈስ ተችሏል። ሥራው እንደቀጠለ ነው። ግን ዘላቂ ነው ማለት አይቻልም። ለጊዜው ካጋጠመው ችግር አኳያ ነው ተለዋጭ መንገድ እየተሰራ ያለው”
ብለዋል።

አደጋው የደረሰው ተሽከርካሪው ከመጠን በላይ ጭኖ ነው ወይስ የድልድዩ የጥራት ችግር ነው? ስንል ላቀረብነው ተጨማሪ ጥያቄም ምላሽ ያሉትን ነግረውናል።

ምን መለሱ?

“በሚመለከታቸው ባለሙያዎች እናሳያለን። ግን ጭነቱም ክብደት እንዳለው ያሳያል። ተሽከርካሪው የድንጋይ ከሰል ነው ተጭኖ ወደ ድልድዩ የገባው የጭንት ክብደት ሊኖር እንደሚችል ያሳያል።

የሌላም ከሆነ ይታያል። በዋናነት ግን ድልድዩም ቢሆን የብረት ድልድይ ነው። ለስምንት ዓመታት አገልገልግሏል።

ይህ ብቻ ሳይሆን አካባቢው፣ በዚሁ በቀጠናችን በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ብዙ ድልድዮች ዘላቂነት ያላቸው አይደሉም የብረት ናቸው። ወደ ኮንክሪት እንዲቀየሩ ጥያቄ እያቀረብን ነው። ሌሎችም የሚያሰጉን ይኖራሉ”
ነው ያሉት።

ይሄው ድልድይ በሰሜኑ ጦርነት የመሰበር አደጋ ደርሶበት ነበር እንዴ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ “ይሄኛው ሳይሆን አላውሃ ድልድይ ነበር ጉዳት የደረሰበት። እሱም የብረት ነው። ይሄም እዛው ቀጥሎ ያለ ነው” ብለዋል።

አሁን የመሰበር አደጋ የደረሰበት ድልድይ ለመጠገን ምን ያክል ወጪ እንደሚጠይቅ ስንጠይቃቸው ደግሞ፣ “እኛ ሥራ እንዲሰራ ነው ጥያቄ እያቀረብን ያለነው። ርዝመቱ ከ48 እስከ 50 ሜትር ነው” ሲሉ አስረድተዋል።

“ቀላል ወጪ ይጠይቃል ተብሎ አይታሰብም። ምንም ቢሆን ከመሰራት ውጪ አማራጭ የለውም። ፌደራል ተለዋጭ መንገድ የለውም። መንገዱ ክልልን ከክልል፣ ወረዳዎችን ከዞን የሚያገናኝ ነው” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94268

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The last couple days have exemplified that uncertainty. On Thursday, news emerged that talks in Turkey between the Russia and Ukraine yielded no positive result. But on Friday, Reuters reported that Russian President Vladimir Putin said there had been some “positive shifts” in talks between the two sides. Two days after Russia invaded Ukraine, an account on the Telegram messaging platform posing as President Volodymyr Zelenskiy urged his armed forces to surrender. As such, the SC would like to remind investors to always exercise caution when evaluating investment opportunities, especially those promising unrealistically high returns with little or no risk. Investors should also never deposit money into someone’s personal bank account if instructed. Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more. In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American