Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ስድስት

ባሰበችው ቁጥርም ይሄ ንግግሩ ይገርማት ነበር። አሁን ግን ነገሮች እየተገለጡላት መጡ። "አፍቅሮኝ ነበር ማለት ነው" እራሷን ጠየቀች። ለዚህ ነው ወደ ንቅናቄው መግባቴን የተቃወመው? የመጨረሻውን ስብሰባ እንዳትካፈል ያላደረገው ጥረት እንዳልነበር ትዝ አላት። በተኩሱ መሀል መጥቶ ጎትቶ ሲወስዳት  ዐይኑ ላይ ይነበብ የነበረው ፍቅር ከየት እንደመጣ በዛን ጊዜ ለማወቅ ተቸግራ ነበር። ግን ለምን አልነገረኝም? እኮ ለምን? ልቧ በሀዘን ደምቷል።
      ታክሲው ካዛንቺስ ደርሶ ሲቆም ወረደች። የተባለው አድራሻ ጋ ለመድረስ ብዙ ሰአት አልወሰደባትም። አልአዛር ከተባለው ሰው የጥያቄዎቿን መልስ እንደምታገኝ ስለገመተች አድራሻው ላይ የሰፈረውን ቤት ለማግኘት ተቻኮለች። መለስተኛ ሆኖ የተደላደለ ኑሮ ሊኖርበት የሚችልበት ሰፊ ቤት አጠገብ ስትደርስ 'ይሄ መሆን አለበት' አለች በሆዷ። የበሩን መጥሪያ ተጫነችው። የሷን መምጣት በመጠባበቅ ላይ የነበሩ እስከሚመስላት ድረስ በሚያስደንቅ ፍጥነት የቤቱ በር ተከፈተ።
       ከፊት ለፊቷ የቆመውን ሰው ስታይ ደነገጠች።ቁርጥ እዮብን። ልቧ በድንጋጤ ምቷን ጨመረች። እንድትገባ በሩን ወለል አድርጎ ከፈተላት። ምንም ሳታመነታ ወደ ውስጥ ዘለቀች። ጊዜ ሳይፈጅ 'አልአዛር' ብሎ እጁን ለትውውቅ ዘረጋ። 'ብሌን' አለች ነገር ግን ራሷን ማስተዋወቅ አስፈላጊ መስሎ አልታያትም። ወጣቱ ካወቃት የቆየ ይመስላልና።
     አልአዛር ገና ብሌንን እንዳየ የወንድሙ እንደዛ በፍቅር መሰቃየት ተገለጠለት። ማንስ ቢሆን ከዚች ቆንጆ የፍቅር ወጥመድ ያመልጣል ሲል አሰበ። ሰውነቷ በድካምና በዱላ የተጎዳ ስለሚመስል ዛሬ ወንድሙ በአደራ ያስቀመጠውን ወረቀት ቢሰጣት ሊጎዳት ይችላል ብሎ ስለጠረጠረ ወረቀቱን ነገ ሊያሳያት ቀጠሮውን አራዘመ።
      ቤቱ የአንድ ወንድ መኖሪያ ብቻ አይመስልም። በፅዳት ተስተካክላ የተዘጋጀችው ሳሎን የሴት እጅ የግድ ያረፈባት መሆኑን ገመተች። እንደገባች ከፊቷ የነበረው ሶፋ ላይ ተዘረረች። ድካሙና ረሀቡ ተደራርበው አቅም አሳጥተዋታል። የልቧ ሀዘን ደግሞ ይበልጥ ሰውነቷን ጎዳው። "ወንድሙ  ነው?" እንዴት ወንድም እንዳለው ለማንም ሳይናገር ኖረ? ግራ ገብቷት ራሷን ጠየቀች።
      አልአዛር ፈጠን ብሎ የሚበላ አቀረበላት። ምግቡን ከፊት ለፊቷ ቀርቦ ስታየው የረሀብ ስሜቷ ተቀሰቀሰ። በልታ እንደጨረሰች ወጣቱ በአበላል ሁኔታዋ መገረሙ አይቀርም ብላ አሰበች። እሱ ግን የተረዳት ይመስላል።
       ራሷን በድንጋይ እንደተመታ ሰው ይፈልጣታል።መቋቋም እስኪያቅታት ድረስ ህመሙ እየጨመረ ሄደ። የራስ ምታት መድኃኒት ይኖርሃል? አለች ወጣቱን እያየች። ወደ መኝታ ክፍል ሄዶ ሁለት መድኃኒቶችን ይዞ መጣ። ይኸውና የራስ ምታት መድሀኒቱ ብሎ አንዱን ወደ እጇ አቀበላት። "ይሄ ደግሞ የእንቅልፍ ኪኒን ነው።" ብዙ እረፍት ያገኘሽ አትመስዪም አላት ፊቷን እያየ። ብሌን አላንገራገረችም ሁለቱንም መድኃኒቶች ዋጠቻቸው። የእንቅልፍ መድኃኒቱ ለመስራት ጊዜም አልወሰደበትም። ጭንቅላቷን ሶፋው ላይ አስደግፋ ለመተኛት ሞከረች። አልተመቻትም። ወጣቱ ሶፋው ላይ ሙሉ ለሙሉ ወጥታ እንድትተኛ ትራስና ወፍራም ጋቢ ከመኝታ ቤት አምጥቶ ሰጣት። መድኃኒቶቹን  መኝታ ቤት አስቀምጦ እስከሚመለስ እንቅልፍ ወስዷታል።
      ከሶፋው አጠገብ ቆሞ ሶፋው ላይ የተኛችሁን ብሌንን በአድናቆት ይመለከታታል። ሁለመናዋ ልብን ይማርካል። በብዙ ነገር ራሳቸውን አስጊጠው ከሚመለከታቸው ሴቶች ይልቅ በሷ ውስጥ ከጉስቁልናዋ በላይ ጎልቶ የሚታየው አፍዝዞታል። እጁን ዘርግቶ.......
✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/121
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ስድስት

ባሰበችው ቁጥርም ይሄ ንግግሩ ይገርማት ነበር። አሁን ግን ነገሮች እየተገለጡላት መጡ። "አፍቅሮኝ ነበር ማለት ነው" እራሷን ጠየቀች። ለዚህ ነው ወደ ንቅናቄው መግባቴን የተቃወመው? የመጨረሻውን ስብሰባ እንዳትካፈል ያላደረገው ጥረት እንዳልነበር ትዝ አላት። በተኩሱ መሀል መጥቶ ጎትቶ ሲወስዳት  ዐይኑ ላይ ይነበብ የነበረው ፍቅር ከየት እንደመጣ በዛን ጊዜ ለማወቅ ተቸግራ ነበር። ግን ለምን አልነገረኝም? እኮ ለምን? ልቧ በሀዘን ደምቷል።
      ታክሲው ካዛንቺስ ደርሶ ሲቆም ወረደች። የተባለው አድራሻ ጋ ለመድረስ ብዙ ሰአት አልወሰደባትም። አልአዛር ከተባለው ሰው የጥያቄዎቿን መልስ እንደምታገኝ ስለገመተች አድራሻው ላይ የሰፈረውን ቤት ለማግኘት ተቻኮለች። መለስተኛ ሆኖ የተደላደለ ኑሮ ሊኖርበት የሚችልበት ሰፊ ቤት አጠገብ ስትደርስ 'ይሄ መሆን አለበት' አለች በሆዷ። የበሩን መጥሪያ ተጫነችው። የሷን መምጣት በመጠባበቅ ላይ የነበሩ እስከሚመስላት ድረስ በሚያስደንቅ ፍጥነት የቤቱ በር ተከፈተ።
       ከፊት ለፊቷ የቆመውን ሰው ስታይ ደነገጠች።ቁርጥ እዮብን። ልቧ በድንጋጤ ምቷን ጨመረች። እንድትገባ በሩን ወለል አድርጎ ከፈተላት። ምንም ሳታመነታ ወደ ውስጥ ዘለቀች። ጊዜ ሳይፈጅ 'አልአዛር' ብሎ እጁን ለትውውቅ ዘረጋ። 'ብሌን' አለች ነገር ግን ራሷን ማስተዋወቅ አስፈላጊ መስሎ አልታያትም። ወጣቱ ካወቃት የቆየ ይመስላልና።
     አልአዛር ገና ብሌንን እንዳየ የወንድሙ እንደዛ በፍቅር መሰቃየት ተገለጠለት። ማንስ ቢሆን ከዚች ቆንጆ የፍቅር ወጥመድ ያመልጣል ሲል አሰበ። ሰውነቷ በድካምና በዱላ የተጎዳ ስለሚመስል ዛሬ ወንድሙ በአደራ ያስቀመጠውን ወረቀት ቢሰጣት ሊጎዳት ይችላል ብሎ ስለጠረጠረ ወረቀቱን ነገ ሊያሳያት ቀጠሮውን አራዘመ።
      ቤቱ የአንድ ወንድ መኖሪያ ብቻ አይመስልም። በፅዳት ተስተካክላ የተዘጋጀችው ሳሎን የሴት እጅ የግድ ያረፈባት መሆኑን ገመተች። እንደገባች ከፊቷ የነበረው ሶፋ ላይ ተዘረረች። ድካሙና ረሀቡ ተደራርበው አቅም አሳጥተዋታል። የልቧ ሀዘን ደግሞ ይበልጥ ሰውነቷን ጎዳው። "ወንድሙ  ነው?" እንዴት ወንድም እንዳለው ለማንም ሳይናገር ኖረ? ግራ ገብቷት ራሷን ጠየቀች።
      አልአዛር ፈጠን ብሎ የሚበላ አቀረበላት። ምግቡን ከፊት ለፊቷ ቀርቦ ስታየው የረሀብ ስሜቷ ተቀሰቀሰ። በልታ እንደጨረሰች ወጣቱ በአበላል ሁኔታዋ መገረሙ አይቀርም ብላ አሰበች። እሱ ግን የተረዳት ይመስላል።
       ራሷን በድንጋይ እንደተመታ ሰው ይፈልጣታል።መቋቋም እስኪያቅታት ድረስ ህመሙ እየጨመረ ሄደ። የራስ ምታት መድኃኒት ይኖርሃል? አለች ወጣቱን እያየች። ወደ መኝታ ክፍል ሄዶ ሁለት መድኃኒቶችን ይዞ መጣ። ይኸውና የራስ ምታት መድሀኒቱ ብሎ አንዱን ወደ እጇ አቀበላት። "ይሄ ደግሞ የእንቅልፍ ኪኒን ነው።" ብዙ እረፍት ያገኘሽ አትመስዪም አላት ፊቷን እያየ። ብሌን አላንገራገረችም ሁለቱንም መድኃኒቶች ዋጠቻቸው። የእንቅልፍ መድኃኒቱ ለመስራት ጊዜም አልወሰደበትም። ጭንቅላቷን ሶፋው ላይ አስደግፋ ለመተኛት ሞከረች። አልተመቻትም። ወጣቱ ሶፋው ላይ ሙሉ ለሙሉ ወጥታ እንድትተኛ ትራስና ወፍራም ጋቢ ከመኝታ ቤት አምጥቶ ሰጣት። መድኃኒቶቹን  መኝታ ቤት አስቀምጦ እስከሚመለስ እንቅልፍ ወስዷታል።
      ከሶፋው አጠገብ ቆሞ ሶፋው ላይ የተኛችሁን ብሌንን በአድናቆት ይመለከታታል። ሁለመናዋ ልብን ይማርካል። በብዙ ነገር ራሳቸውን አስጊጠው ከሚመለከታቸው ሴቶች ይልቅ በሷ ውስጥ ከጉስቁልናዋ በላይ ጎልቶ የሚታየው አፍዝዞታል። እጁን ዘርግቶ.......
✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/121

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram has gained a reputation as the “secure” communications app in the post-Soviet states, but whenever you make choices about your digital security, it’s important to start by asking yourself, “What exactly am I securing? And who am I securing it from?” These questions should inform your decisions about whether you are using the right tool or platform for your digital security needs. Telegram is certainly not the most secure messaging app on the market right now. Its security model requires users to place a great deal of trust in Telegram’s ability to protect user data. For some users, this may be good enough for now. For others, it may be wiser to move to a different platform for certain kinds of high-risk communications. 'Wild West' The perpetrators use various names to carry out the investment scams. They may also impersonate or clone licensed capital market intermediaries by using the names, logos, credentials, websites and other details of the legitimate entities to promote the illegal schemes. Russian President Vladimir Putin launched Russia's invasion of Ukraine in the early-morning hours of February 24, targeting several key cities with military strikes. Stocks closed in the red Friday as investors weighed upbeat remarks from Russian President Vladimir Putin about diplomatic discussions with Ukraine against a weaker-than-expected print on U.S. consumer sentiment.
from us


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American