Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " በትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክህደት የፈፀመ ቡድን " ሲል ፈረጀ። በምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " ብሄራዊ ክህደት ፈፅሟል " ሲል የፈረጀው ማእከላዊ ኮሚቴ " ቡድኑ ከአፍራሽ ተግባሩ እንዲቆጠብ " መላው የትግራይ ህዝብ እና አባላት እንዲታገሉት…
#Tigray

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " - በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት

ለሁለት በተከፈሉት የህወሓት አመራሮች መካከል ያለው የመግለጫ ምልልስ አሁንም ቀጥሏል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ፤ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም ላወጣው መግለጫ መልስ ሰጥቷል።

በዚህም በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል ፈርጆታል። 

" በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደር ቃሉን አጥፈዋል በአጭር ጊዜ ልኩ ለማስገባት በማካሂደው ትግል ህዝቡ ከጎኔ ይቁም የሚል የሚያስደምም መግለጫ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም በመገናኛ ብዙሃን አሰራጭቷል " ሲል የአቶ ጌታቸው ቡድን ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድን " በመባል የተገለፀው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የፌደራል መንግስት የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሁለት ሳምንት እንዲነሳ ቀጠሮ ተሰጥቶኛል " ሲል እንዳልቆየ " ጊዚያዊ አስተዳደሩን በአጭር ጊዜ መልክ ለማስያዝ ወሰኜ ቃል ገብቻለሁ ተከተሉኝ " የሚል የክተት ጥሪ አቅርቧል ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" የዚህ አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ አካሄድ ለህዝብ አዲስ አይፈለም " ያለው መግለጫው  " ቡድኑ ከፌደራል መንግስት የሚነጋገረው እና የሚስማማው ሌላ ለትግራይ ህዝብ የሚለው ደግሞ ሌላ " ሲል ገልፆታል።

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን  እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " ሲል  በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ የትግራይን ህዝብ ከፌደራል መንግስት የሚያጋጭ አቅጣጫ እየተከተለ መሆኑ ያወጣው መግለጫ አመላካች ነው " ሲል አክሏል።

የደብረጽዮን (ዶ/ር) ቡድን ህዝቡ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ እንዲያምፅ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው በሚል ተከሷል።

ከፌደራል መንግስት በድብቅ " የውጭ ሽምጋይ ሳያስፈልገን ጉዳያችን ብቻችን መጨረስ እንችላለን " በማለት ስልጣን ይለምናልም ተብሏል።

" ቡድኑ ከስልጣን ውጪ የትግራይ ህዝብ ጉዳይ እንደ ጉዳዩ የማይቆጥር ራስ ወዳድ " ሲል አቶ ጌታቸው የሚመሩት ህወሓት አብጠልጥሎታል።

ከዚህ በተጨማሪ ፤ " ለስልጣን ሲል ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዳይመለሱ የመከልከል እና የማደናቀፍ ስራውን ቀጥሎበታል ፣ ዴሞብላይዜሽን (DDR) እንዲደናቀፍ ሴራዎች እየሸረበ ነው " ሲል ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ ቃሉ እና ተግባሩ ለየቅል ናቸው ፤ የህዝብ ችግር እና መከራ እንዳይፈታ በማወሳሰብ እንደ ምክንያት ተጠቅሞ ህዝብን እና መንግስት በማቃቃር በአመፅ ስልጣን ላይ ለመቆየት  ሙጥኝ ያለ ፀረ ህዝብ ነው " ሲል  ፈርጆታል።

የትግራይ ህዝብ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጡት አስተዳደራዊ ፣ ፓለቲካዊ ተልእኮዎች በተሰጠው ጊዜ አጠናቅቆ በህዝብ የተመረጠ መደበኛ መንግስት እንዲኖር የሚደረገው ትግል በመደገፍ  " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል የጠራውን የነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) ቢድን " የሚያካሂደውን አፍራሽ ተግባር በፅኑ እንዲቃወመውና እንዲያመክነው ጥሪውን አቅርቧል።

ከትላትና በስቲያ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " በትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክህደት የፈፀመ ቡድን " ሲል መፈረጁ ይታወሳል።

አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በተገኙበት ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመሩት ውይይት ቢደረግም ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ጠንከር ባሉ መግለጫዎች አንድ ሁለት እየተባባሉ ነው።

የመግለጫዎቹ ይዘት ጠንካራ ከመሆናቸው አልፎ እየተወረወሩ ያሉት ቃላት ነገሩ ከመርገብ ይልቅ እየተካረረ እየሄደ እንዳለ ማሳያ ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/92842
Create:
Last Update:

#Tigray

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " - በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት

ለሁለት በተከፈሉት የህወሓት አመራሮች መካከል ያለው የመግለጫ ምልልስ አሁንም ቀጥሏል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ፤ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም ላወጣው መግለጫ መልስ ሰጥቷል።

በዚህም በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል ፈርጆታል። 

" በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደር ቃሉን አጥፈዋል በአጭር ጊዜ ልኩ ለማስገባት በማካሂደው ትግል ህዝቡ ከጎኔ ይቁም የሚል የሚያስደምም መግለጫ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም በመገናኛ ብዙሃን አሰራጭቷል " ሲል የአቶ ጌታቸው ቡድን ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድን " በመባል የተገለፀው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የፌደራል መንግስት የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሁለት ሳምንት እንዲነሳ ቀጠሮ ተሰጥቶኛል " ሲል እንዳልቆየ " ጊዚያዊ አስተዳደሩን በአጭር ጊዜ መልክ ለማስያዝ ወሰኜ ቃል ገብቻለሁ ተከተሉኝ " የሚል የክተት ጥሪ አቅርቧል ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" የዚህ አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ አካሄድ ለህዝብ አዲስ አይፈለም " ያለው መግለጫው  " ቡድኑ ከፌደራል መንግስት የሚነጋገረው እና የሚስማማው ሌላ ለትግራይ ህዝብ የሚለው ደግሞ ሌላ " ሲል ገልፆታል።

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን  እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " ሲል  በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ የትግራይን ህዝብ ከፌደራል መንግስት የሚያጋጭ አቅጣጫ እየተከተለ መሆኑ ያወጣው መግለጫ አመላካች ነው " ሲል አክሏል።

የደብረጽዮን (ዶ/ር) ቡድን ህዝቡ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ እንዲያምፅ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው በሚል ተከሷል።

ከፌደራል መንግስት በድብቅ " የውጭ ሽምጋይ ሳያስፈልገን ጉዳያችን ብቻችን መጨረስ እንችላለን " በማለት ስልጣን ይለምናልም ተብሏል።

" ቡድኑ ከስልጣን ውጪ የትግራይ ህዝብ ጉዳይ እንደ ጉዳዩ የማይቆጥር ራስ ወዳድ " ሲል አቶ ጌታቸው የሚመሩት ህወሓት አብጠልጥሎታል።

ከዚህ በተጨማሪ ፤ " ለስልጣን ሲል ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዳይመለሱ የመከልከል እና የማደናቀፍ ስራውን ቀጥሎበታል ፣ ዴሞብላይዜሽን (DDR) እንዲደናቀፍ ሴራዎች እየሸረበ ነው " ሲል ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ ቃሉ እና ተግባሩ ለየቅል ናቸው ፤ የህዝብ ችግር እና መከራ እንዳይፈታ በማወሳሰብ እንደ ምክንያት ተጠቅሞ ህዝብን እና መንግስት በማቃቃር በአመፅ ስልጣን ላይ ለመቆየት  ሙጥኝ ያለ ፀረ ህዝብ ነው " ሲል  ፈርጆታል።

የትግራይ ህዝብ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጡት አስተዳደራዊ ፣ ፓለቲካዊ ተልእኮዎች በተሰጠው ጊዜ አጠናቅቆ በህዝብ የተመረጠ መደበኛ መንግስት እንዲኖር የሚደረገው ትግል በመደገፍ  " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል የጠራውን የነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) ቢድን " የሚያካሂደውን አፍራሽ ተግባር በፅኑ እንዲቃወመውና እንዲያመክነው ጥሪውን አቅርቧል።

ከትላትና በስቲያ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " በትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክህደት የፈፀመ ቡድን " ሲል መፈረጁ ይታወሳል።

አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በተገኙበት ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመሩት ውይይት ቢደረግም ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ጠንከር ባሉ መግለጫዎች አንድ ሁለት እየተባባሉ ነው።

የመግለጫዎቹ ይዘት ጠንካራ ከመሆናቸው አልፎ እየተወረወሩ ያሉት ቃላት ነገሩ ከመርገብ ይልቅ እየተካረረ እየሄደ እንዳለ ማሳያ ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/92842

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The regulator said it has been undertaking several campaigns to educate the investors to be vigilant while taking investment decisions based on stock tips. Telegram does offer end-to-end encrypted communications through Secret Chats, but this is not the default setting. Standard conversations use the MTProto method, enabling server-client encryption but with them stored on the server for ease-of-access. This makes using Telegram across multiple devices simple, but also means that the regular Telegram chats you’re having with folks are not as secure as you may believe. "There are several million Russians who can lift their head up from propaganda and try to look for other sources, and I'd say that most look for it on Telegram," he said. In a statement, the regulator said the search and seizure operation was carried out against seven individuals and one corporate entity at multiple locations in Ahmedabad and Bhavnagar in Gujarat, Neemuch in Madhya Pradesh, Delhi, and Mumbai. If you initiate a Secret Chat, however, then these communications are end-to-end encrypted and are tied to the device you are using. That means it’s less convenient to access them across multiple platforms, but you are at far less risk of snooping. Back in the day, Secret Chats received some praise from the EFF, but the fact that its standard system isn’t as secure earned it some criticism. If you’re looking for something that is considered more reliable by privacy advocates, then Signal is the EFF’s preferred platform, although that too is not without some caveats.
from vn


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American