Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94008-94009-94010-94011-94012-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94010 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ውጤቱ ህዝብን እና አገር የሚያጠፋ አካሄድ በመሆኑ መቆም አለበት " - የተለየ አቋም ያላቸው ከፍተኛ የትግራይ ኃይል አመራሮች 

በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ የትግራይ ኃይል አመራር መኮንኖች ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ያወጡት መግለጫ ተቃውሞ እየገጠመው ነው።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደርን በመቃወም በብሄራዊ የምርጫ ቦርድ እውቅና ያልተሰጠው ጉባኤ ያካሄደው በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት እውቅና እንደሚሰጡ ያስታወቁት የትግራይ ኃይል አመራሮችን ጊዚያዊ አስተዳደሩ በፅኑ ተቃውሟቸዋል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩን መግለጫ ተከትሎ በአመራሮቹ ሰብሰባ ላይ የተሳተፉ የተለየ አቋም እንዳላቸው የገለጹ ከፍተኛ የትግራይ ኃይል አመራሮች ፥ " የሰራዊት አመራር በመሆን የፓለቲካ ፓርቲ የሚመስል ሰራዊት ለመገንባት የሚደረግ እንቅስቃሴ ውጤቱ ህዝብን እና አገር የሚያጠፋ አካሄድ እንዲቆም ጥሪ እናቀርባለን " ብለዋል።

የተለየ አቋም እንዳላቸው በመግለጫቸው ያሳወቁት ከፍተኛ አመራሮቹ ፤ " አንድ የፓለቲካ ፓርቲ እና በዚህም በዚያም ያሉት ቡድኖችን የሚመለከት አጀንዳ ላይ መወያየት እና አቋም መያዝ ከሰራዊቱ ተልእኮ ውጪና ወታደራዊ ወንጀል በመሆኑ በጥብቅ እንቃወማለን " ሲሉ አብራርተዋል።

" ስለሆነም ከሰራዊቱ ተልእኮ እና የስራ ስምሪት ውጪ ' ጠላት ነው ' በሚል ፍረጃ የጊዚያዊ አስተዳደሩን ፕሬዜዳንት ለመቀየር የሚደረግ የፓለቲካ እንቅስቃሴ ተቋማዊ አሰራር የሚጥስ በመሆኑ እንዲቆም በጥብቅ እንጠይቃለን " ሲሉ አክለዋል።

የክልሉ ምስራቃዊ ፣ ደቡብ ምስራቃዊ ፣ የደቡባዊ ዞን ኦፍላ ወረዳ እንዲሁም በራስ ተነሳሽነት መሰባሰባቸውን የገለፁ የመቐለ ከተማ ወጣቶች ባወጡት መግለጫ ፤ " ወታደራዊ  መኮንኖች ከተልእኮ እና ከተሰጣቸው ህዝባዊ እና መንግስታዊ  ስምሪት ባፈነገጠ መልኩ ወደ አንዱ ቡድን በማዳላት ያወጡት መግለጫ በአስቸኳይ እንዲያርሙት " ሲሉ ጠይቀዋል።

የትላንቱ የመግለጫ ተቃዋሚዎች  ፤ " አመራሮቹ ያወጡት ህገ-ወጥ መግለጫ ጅምር ሰላሙ የሚያጨልምና የሚያመክን በመሆኑ ፤ ለህግ እና ስርዓት ተገዢ ከሆኑ አመራር እና አባላት ጋር በመሆን እስከ መጨረሻ ብፅናት እንደምንታገላችሁ ልናሳውቃችሁ እንፈልጋለን " ሲሉ አስጠንቅቀዋል

ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የትላንቱን መግለጫ በመቃወም ለቪኦኤ በሰጡት አጭር ቃል ፥ " የትግራይ ሰራዊት የቡድኖች መጫወቻ እንዲሆን የሚደረግ ሙከራ ተቀባይነት የሌለው ስህተት ነው ፤ ወታደራዊ መኮንኖቹ ፓለቲከኛ መሆን ካሰኛቸው ወታደራዊ ሃላፊነታቸው በመተው የፈለጉት ፓርቲ አባል መሆን ይችላሉ። ከዚህ ውጭ ያደረጉት ስህተት ግን በአስቸኳይ እንደሚያሩሙት ተስፋ አደርጋለሁ " ብለዋል።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94010
Create:
Last Update:

#Update

" እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ውጤቱ ህዝብን እና አገር የሚያጠፋ አካሄድ በመሆኑ መቆም አለበት " - የተለየ አቋም ያላቸው ከፍተኛ የትግራይ ኃይል አመራሮች 

በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ የትግራይ ኃይል አመራር መኮንኖች ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ያወጡት መግለጫ ተቃውሞ እየገጠመው ነው።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደርን በመቃወም በብሄራዊ የምርጫ ቦርድ እውቅና ያልተሰጠው ጉባኤ ያካሄደው በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት እውቅና እንደሚሰጡ ያስታወቁት የትግራይ ኃይል አመራሮችን ጊዚያዊ አስተዳደሩ በፅኑ ተቃውሟቸዋል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩን መግለጫ ተከትሎ በአመራሮቹ ሰብሰባ ላይ የተሳተፉ የተለየ አቋም እንዳላቸው የገለጹ ከፍተኛ የትግራይ ኃይል አመራሮች ፥ " የሰራዊት አመራር በመሆን የፓለቲካ ፓርቲ የሚመስል ሰራዊት ለመገንባት የሚደረግ እንቅስቃሴ ውጤቱ ህዝብን እና አገር የሚያጠፋ አካሄድ እንዲቆም ጥሪ እናቀርባለን " ብለዋል።

የተለየ አቋም እንዳላቸው በመግለጫቸው ያሳወቁት ከፍተኛ አመራሮቹ ፤ " አንድ የፓለቲካ ፓርቲ እና በዚህም በዚያም ያሉት ቡድኖችን የሚመለከት አጀንዳ ላይ መወያየት እና አቋም መያዝ ከሰራዊቱ ተልእኮ ውጪና ወታደራዊ ወንጀል በመሆኑ በጥብቅ እንቃወማለን " ሲሉ አብራርተዋል።

" ስለሆነም ከሰራዊቱ ተልእኮ እና የስራ ስምሪት ውጪ ' ጠላት ነው ' በሚል ፍረጃ የጊዚያዊ አስተዳደሩን ፕሬዜዳንት ለመቀየር የሚደረግ የፓለቲካ እንቅስቃሴ ተቋማዊ አሰራር የሚጥስ በመሆኑ እንዲቆም በጥብቅ እንጠይቃለን " ሲሉ አክለዋል።

የክልሉ ምስራቃዊ ፣ ደቡብ ምስራቃዊ ፣ የደቡባዊ ዞን ኦፍላ ወረዳ እንዲሁም በራስ ተነሳሽነት መሰባሰባቸውን የገለፁ የመቐለ ከተማ ወጣቶች ባወጡት መግለጫ ፤ " ወታደራዊ  መኮንኖች ከተልእኮ እና ከተሰጣቸው ህዝባዊ እና መንግስታዊ  ስምሪት ባፈነገጠ መልኩ ወደ አንዱ ቡድን በማዳላት ያወጡት መግለጫ በአስቸኳይ እንዲያርሙት " ሲሉ ጠይቀዋል።

የትላንቱ የመግለጫ ተቃዋሚዎች  ፤ " አመራሮቹ ያወጡት ህገ-ወጥ መግለጫ ጅምር ሰላሙ የሚያጨልምና የሚያመክን በመሆኑ ፤ ለህግ እና ስርዓት ተገዢ ከሆኑ አመራር እና አባላት ጋር በመሆን እስከ መጨረሻ ብፅናት እንደምንታገላችሁ ልናሳውቃችሁ እንፈልጋለን " ሲሉ አስጠንቅቀዋል

ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የትላንቱን መግለጫ በመቃወም ለቪኦኤ በሰጡት አጭር ቃል ፥ " የትግራይ ሰራዊት የቡድኖች መጫወቻ እንዲሆን የሚደረግ ሙከራ ተቀባይነት የሌለው ስህተት ነው ፤ ወታደራዊ መኮንኖቹ ፓለቲከኛ መሆን ካሰኛቸው ወታደራዊ ሃላፊነታቸው በመተው የፈለጉት ፓርቲ አባል መሆን ይችላሉ። ከዚህ ውጭ ያደረጉት ስህተት ግን በአስቸኳይ እንደሚያሩሙት ተስፋ አደርጋለሁ " ብለዋል።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA









Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94010

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

"Russians are really disconnected from the reality of what happening to their country," Andrey said. "So Telegram has become essential for understanding what's going on to the Russian-speaking world." Lastly, the web previews of t.me links have been given a new look, adding chat backgrounds and design elements from the fully-features Telegram Web client. In a message on his Telegram channel recently recounting the episode, Durov wrote: "I lost my company and my home, but would do it again – without hesitation." Following this, Sebi, in an order passed in January 2022, established that the administrators of a Telegram channel having a large subscriber base enticed the subscribers to act upon recommendations that were circulated by those administrators on the channel, leading to significant price and volume impact in various scrips. Multiple pro-Kremlin media figures circulated the post's false claims, including prominent Russian journalist Vladimir Soloviev and the state-controlled Russian outlet RT, according to the DFR Lab's report.
from vn


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American