Telegram Group & Telegram Channel
<ቅናተኛ> ነኝ! በተለይ በእሷማ ቀናለሁ!

የዕድሜ'ዬን ግማሽ የኖርኩት እሷን 'ልመስል' ስፅፍ ሳጠፋ ነው። ግን እሷን 'መሆን' አልቻልኩም።

የመሰልኩ በመሰለኝ ሰአትም ፊቱ ስቆም ከሙሉዕነቴ ይልቅ ባዶነቴ ያሳብቅብኛል።

ፈት ነኝ! አምስቴ አግብቼ ፈትቻለው። ያፈገገልኝ ሁሉ ጓዶሎዬን መሙያ እየመሰለኝ ከመኝታ ለመሰየም ቀናት አይፈጅብኝም።

. . .እሷን ግን መሆን አልቻልኩም።

ራሴው ለገፋውት አጨብጫቢ እሻለው፣ ያላከበርኩትን ክብር እንዲከብር ስንቴ ጠብቄሃለሁ ግን እንኳን መሆን መምሰል ራሱ አልቻልኩም።

መቼ'ለት ነው . . . ወግ ማዕረግ በደምግባት አገኝ ብዬ ከአንዱ ልባም ተጠጋው....ምን ዋጋ አለው? ፈጣሪን አለመፍራቴ አይሎብኝ "ውበት ሀሰት ነው" ብሎ ተረተብኝ።

ያቺ አጥንቴ የነቀዘላት ሴት ግን የከበረች፣ በጎዳና ከመታየት ይልቅ በጓዳዋ የተሸሸገች ናት።

. . .አንድ ባል ነው ያላት እንደ ንጉስ ያከበረችው ከመኳንንት ጋር ሲቀመጥ 'ፐ'! ሞገስስ በሱ ቀረ የሚባልላት!

ከመስታዎቴ ቆሜ ገፄ ላይ እሷን ስስል ውዬ አድራለው። የኀላ ኀላ አለመሆኔ ጎልቶ ከወደ ህሊናዬ ያንቧርቅብኛል።

'ራስን መሆን' የሚባል መድኃኒት አለ። በሌላ መስታዎት ራሴን ለማየት ስፍጨረጨር ለካስ የማላድን መድኃኒተኛ ኖሬያለሁ። ፍለጋዬን አስተካክያለው "በአንዱ ቀመር የሌላው ስሌት አይሰራም!"

አሁን የተስፋ ጭላንጭል አለኝ። እኔ ውስጥ እሷን ከመፈለግ የሚልቀው እኔነቴ ጥልቀት እኔን መፈለጉ ነው። ምን አልባት መሲሁ ይመጣ ይሆናል። ጉዴን ነግሮ በፃፈለኝ ማንነት ሌላውን እሆን ብዬ የሰረዝኩ የደለዝኩትን ሽሮ በራስን መሆን ባህር ዳግም ካጠመቀኝ... እጠብቃለው!

እስከዚያው ግን:
የማያቋርጥ ጠፈጠፍ፣ በዝናብ ጊዜ የሚያፈስ ቤት የሚመስለውን አመሌን ይዤ ወጣለው። 'አእምሮ የጎደለው' አገኝ ይሆን ብዬ... 'ከአላዋቂዎች' መካከል ልዝብ አንደበቴን ሰምቶ የሚሳብ ልቦናዬን በጌጤ የመዘነ አይጠፋምና።

አርያም ተስፋዬ(2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/118
Create:
Last Update:

<ቅናተኛ> ነኝ! በተለይ በእሷማ ቀናለሁ!

የዕድሜ'ዬን ግማሽ የኖርኩት እሷን 'ልመስል' ስፅፍ ሳጠፋ ነው። ግን እሷን 'መሆን' አልቻልኩም።

የመሰልኩ በመሰለኝ ሰአትም ፊቱ ስቆም ከሙሉዕነቴ ይልቅ ባዶነቴ ያሳብቅብኛል።

ፈት ነኝ! አምስቴ አግብቼ ፈትቻለው። ያፈገገልኝ ሁሉ ጓዶሎዬን መሙያ እየመሰለኝ ከመኝታ ለመሰየም ቀናት አይፈጅብኝም።

. . .እሷን ግን መሆን አልቻልኩም።

ራሴው ለገፋውት አጨብጫቢ እሻለው፣ ያላከበርኩትን ክብር እንዲከብር ስንቴ ጠብቄሃለሁ ግን እንኳን መሆን መምሰል ራሱ አልቻልኩም።

መቼ'ለት ነው . . . ወግ ማዕረግ በደምግባት አገኝ ብዬ ከአንዱ ልባም ተጠጋው....ምን ዋጋ አለው? ፈጣሪን አለመፍራቴ አይሎብኝ "ውበት ሀሰት ነው" ብሎ ተረተብኝ።

ያቺ አጥንቴ የነቀዘላት ሴት ግን የከበረች፣ በጎዳና ከመታየት ይልቅ በጓዳዋ የተሸሸገች ናት።

. . .አንድ ባል ነው ያላት እንደ ንጉስ ያከበረችው ከመኳንንት ጋር ሲቀመጥ 'ፐ'! ሞገስስ በሱ ቀረ የሚባልላት!

ከመስታዎቴ ቆሜ ገፄ ላይ እሷን ስስል ውዬ አድራለው። የኀላ ኀላ አለመሆኔ ጎልቶ ከወደ ህሊናዬ ያንቧርቅብኛል።

'ራስን መሆን' የሚባል መድኃኒት አለ። በሌላ መስታዎት ራሴን ለማየት ስፍጨረጨር ለካስ የማላድን መድኃኒተኛ ኖሬያለሁ። ፍለጋዬን አስተካክያለው "በአንዱ ቀመር የሌላው ስሌት አይሰራም!"

አሁን የተስፋ ጭላንጭል አለኝ። እኔ ውስጥ እሷን ከመፈለግ የሚልቀው እኔነቴ ጥልቀት እኔን መፈለጉ ነው። ምን አልባት መሲሁ ይመጣ ይሆናል። ጉዴን ነግሮ በፃፈለኝ ማንነት ሌላውን እሆን ብዬ የሰረዝኩ የደለዝኩትን ሽሮ በራስን መሆን ባህር ዳግም ካጠመቀኝ... እጠብቃለው!

እስከዚያው ግን:
የማያቋርጥ ጠፈጠፍ፣ በዝናብ ጊዜ የሚያፈስ ቤት የሚመስለውን አመሌን ይዤ ወጣለው። 'አእምሮ የጎደለው' አገኝ ይሆን ብዬ... 'ከአላዋቂዎች' መካከል ልዝብ አንደበቴን ሰምቶ የሚሳብ ልቦናዬን በጌጤ የመዘነ አይጠፋምና።

አርያም ተስፋዬ(2013)

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/118

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In February 2014, the Ukrainian people ousted pro-Russian president Viktor Yanukovych, prompting Russia to invade and annex the Crimean peninsula. By the start of April, Pavel Durov had given his notice, with TechCrunch saying at the time that the CEO had resisted pressure to suppress pages criticizing the Russian government. The Russian invasion of Ukraine has been a driving force in markets for the past few weeks. Artem Kliuchnikov and his family fled Ukraine just days before the Russian invasion. "There are several million Russians who can lift their head up from propaganda and try to look for other sources, and I'd say that most look for it on Telegram," he said. Perpetrators of such fraud use various marketing techniques to attract subscribers on their social media channels.
from vn


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American