Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ዘጠኝ
ደብዳቤውን አንብባ እንደጨረሰች ራሷን ጉልበቶቿ መሀል ወሸቀቻቸው። ለምን ይሄን ሁሉ መስዋዕትነት? ለምን ይህን ያህል ለአንዲት ሴት ራስን አሳልፎ መስጠት? በምላሹ ታፍቅረው አታፍቅረው ሳያውቅ ለምን ራሱን ለእሷ ሰጠ? በህይወት ቢኖርና ይህንን ጥያቄዋን ቢመልስላት በወደደች ነበር ግን እዮብ አይመለስ አሸልቧል።

ተሳሳትክ እዮብ ብትነግረኝ ይሻል ነበር። ከጭንቅላቴ የማይሻር ጠባሳ ተውክብኝ! መቼም ከፊቴ የተዘረረውን ያንተን አካል መዘንጋት አልችልም ፣ከአእምሮዬ ሊጠፋ አይችልም። እዮብ ስህተት ሰርተኻል አዎ በጣም ተሳስተሃል! እጇ ላከ የነበረውን ወረቀት ጨመደደችው። ምን ልታስብ እንደሚገባት ማወቅ አልቻለችም። ብቻ ልትከፍለው የማትችለው የእዮብ ውለታ አለባት።

አፈቅረው ነበር? እራሷን ጠየቀች ልቧ የአዎንታም የአሉታም ምላሽ አልሰጣትም። ለረጅም ሰአት አነባች። አልአዛር ለማባበል አልሞከረም። ምክንያቱም የእሱም እምባ እየፈሰሰ ነበር። አንድ ብቸኛ ወንድሙን እንዳጣ ገብቶታል። በጀግንነት የሞተው የወንድሙ ወኔና ድፍረት ታወሰው። ለእዚች ከፊት ለፊቱ ለተቀመጠችው ሴት የነበረው የፍቅር ጥንካሬ የተለየ ነበር። ምን ያደርጋል? በህይወት ሳለ መፈቀሯን ሳታውቅ ከሞተ በኅላ ለፍቅሯ የከፈለውን መስዋዕትነት የተረዳችው ወጣት ላታገግም ቆስላለች። በምንም መንገድ ሊያፅናናት አይችልም።

ማን ያውቃል? ጊዜ የሚያመጣው አይታወቅም አለ ለራሱ እዮብን ልትዘነጋ የምትችልበት መንገድ ይኖራል።  በተቻለው መጠን ሀዘኗን ልትረሳ የምትችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በሙሉ አቅሙ ቆርጧል። ከመንግስትም የደንነት አባላት ጋር በነበረው የጠበቀ ግንኙነት አንድ የውሸት መታወቂያ ሊያገኝላት ችሏል። የእሷን መምጣት ቀደም ብሎ እየጠበቀች ስለነበር ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ዝግጁ አድርጓል።

መታወቂያውን ከኪሱ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠው። 'መአዛ አሸናፊ' ይላል። ምንድን ነው በሚል ሁኔታ ተመለከተችው። አዲሱ ስምሽ ነው ትንሽ ራስሽን መቀየር ይኖርብሻል አለና ትርምስምሱ የወጣውን ረጅም ፀጉሯን አየ። መቆረጥ ሳይኖርበት አይቀርም። በተወሰነ መልኩ የፊትሽን ገፅታ ሊቀይረው ይችላል። ግን ይህን የመሰለ ፀጉር ተቆርጦ ሲወድግ ያሳዝናል ሲል አሰበ።

ብሌን አላመነታችም። በህይወት መኖር እስካለባት ድረስ ራሷን መለወጧ የግድ ነው። ሻወር መውሰድ ፈልጋለች። አልአዛር ጭንቅላቷን ያነበበ ይመስል መታጠብ ከፈለግሽ ሻወር ቤቱን ላሳይሽ እችላለሁ።  ፀጉርሽን የምትቆርጪበት መቀስ በስተቀኝ ባለው ኮመዲኖ ላይ ይገኛል። አላት ጊዜ ሳታጠፋ ልብሷን አወላልቃ ውሀው ውስጥ ተነከረች። ውሀው እንደውጪው ቆሻሻዋ ልቧ ውስጥም ያለውን ሸክም መውሰድ ቢችል ምንኛ በተደሰተች ነበር። ዐይኗን ጨፍና ከላይ የሚወርደውን ውሀ ከጭንቅላቷ ጀምሮ ታች እስኪደርስ ድረስ ታዳምጠዋለች። ከውሀው አንድ መፍትሔ ታገኝ ይመስል አሁንም አሁንም ትነከራለች። ሰውነቷ ቢፀዳም መውጣቱን ጠላችው። በጣም ከምትወዳት  ምስኪን እናቷ ጋር እንደማትገናኝ ተረድታለች። ይሄኔ እማዬ ሞቴን ሰምታ ሀዘን ተቀምጣ ይሆናል ስትል አሰበች። በራ ሄዳ አይዞሽ በህይወት አለውልሽ ልትላት ተመኘች።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/124
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ዘጠኝ
ደብዳቤውን አንብባ እንደጨረሰች ራሷን ጉልበቶቿ መሀል ወሸቀቻቸው። ለምን ይሄን ሁሉ መስዋዕትነት? ለምን ይህን ያህል ለአንዲት ሴት ራስን አሳልፎ መስጠት? በምላሹ ታፍቅረው አታፍቅረው ሳያውቅ ለምን ራሱን ለእሷ ሰጠ? በህይወት ቢኖርና ይህንን ጥያቄዋን ቢመልስላት በወደደች ነበር ግን እዮብ አይመለስ አሸልቧል።

ተሳሳትክ እዮብ ብትነግረኝ ይሻል ነበር። ከጭንቅላቴ የማይሻር ጠባሳ ተውክብኝ! መቼም ከፊቴ የተዘረረውን ያንተን አካል መዘንጋት አልችልም ፣ከአእምሮዬ ሊጠፋ አይችልም። እዮብ ስህተት ሰርተኻል አዎ በጣም ተሳስተሃል! እጇ ላከ የነበረውን ወረቀት ጨመደደችው። ምን ልታስብ እንደሚገባት ማወቅ አልቻለችም። ብቻ ልትከፍለው የማትችለው የእዮብ ውለታ አለባት።

አፈቅረው ነበር? እራሷን ጠየቀች ልቧ የአዎንታም የአሉታም ምላሽ አልሰጣትም። ለረጅም ሰአት አነባች። አልአዛር ለማባበል አልሞከረም። ምክንያቱም የእሱም እምባ እየፈሰሰ ነበር። አንድ ብቸኛ ወንድሙን እንዳጣ ገብቶታል። በጀግንነት የሞተው የወንድሙ ወኔና ድፍረት ታወሰው። ለእዚች ከፊት ለፊቱ ለተቀመጠችው ሴት የነበረው የፍቅር ጥንካሬ የተለየ ነበር። ምን ያደርጋል? በህይወት ሳለ መፈቀሯን ሳታውቅ ከሞተ በኅላ ለፍቅሯ የከፈለውን መስዋዕትነት የተረዳችው ወጣት ላታገግም ቆስላለች። በምንም መንገድ ሊያፅናናት አይችልም።

ማን ያውቃል? ጊዜ የሚያመጣው አይታወቅም አለ ለራሱ እዮብን ልትዘነጋ የምትችልበት መንገድ ይኖራል።  በተቻለው መጠን ሀዘኗን ልትረሳ የምትችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በሙሉ አቅሙ ቆርጧል። ከመንግስትም የደንነት አባላት ጋር በነበረው የጠበቀ ግንኙነት አንድ የውሸት መታወቂያ ሊያገኝላት ችሏል። የእሷን መምጣት ቀደም ብሎ እየጠበቀች ስለነበር ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ዝግጁ አድርጓል።

መታወቂያውን ከኪሱ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠው። 'መአዛ አሸናፊ' ይላል። ምንድን ነው በሚል ሁኔታ ተመለከተችው። አዲሱ ስምሽ ነው ትንሽ ራስሽን መቀየር ይኖርብሻል አለና ትርምስምሱ የወጣውን ረጅም ፀጉሯን አየ። መቆረጥ ሳይኖርበት አይቀርም። በተወሰነ መልኩ የፊትሽን ገፅታ ሊቀይረው ይችላል። ግን ይህን የመሰለ ፀጉር ተቆርጦ ሲወድግ ያሳዝናል ሲል አሰበ።

ብሌን አላመነታችም። በህይወት መኖር እስካለባት ድረስ ራሷን መለወጧ የግድ ነው። ሻወር መውሰድ ፈልጋለች። አልአዛር ጭንቅላቷን ያነበበ ይመስል መታጠብ ከፈለግሽ ሻወር ቤቱን ላሳይሽ እችላለሁ።  ፀጉርሽን የምትቆርጪበት መቀስ በስተቀኝ ባለው ኮመዲኖ ላይ ይገኛል። አላት ጊዜ ሳታጠፋ ልብሷን አወላልቃ ውሀው ውስጥ ተነከረች። ውሀው እንደውጪው ቆሻሻዋ ልቧ ውስጥም ያለውን ሸክም መውሰድ ቢችል ምንኛ በተደሰተች ነበር። ዐይኗን ጨፍና ከላይ የሚወርደውን ውሀ ከጭንቅላቷ ጀምሮ ታች እስኪደርስ ድረስ ታዳምጠዋለች። ከውሀው አንድ መፍትሔ ታገኝ ይመስል አሁንም አሁንም ትነከራለች። ሰውነቷ ቢፀዳም መውጣቱን ጠላችው። በጣም ከምትወዳት  ምስኪን እናቷ ጋር እንደማትገናኝ ተረድታለች። ይሄኔ እማዬ ሞቴን ሰምታ ሀዘን ተቀምጣ ይሆናል ስትል አሰበች። በራ ሄዳ አይዞሽ በህይወት አለውልሽ ልትላት ተመኘች።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/124

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Now safely in France with his spouse and three of his children, Kliuchnikov scrolls through Telegram to learn about the devastation happening in his home country. The Security Service of Ukraine said in a tweet that it was able to effectively target Russian convoys near Kyiv because of messages sent to an official Telegram bot account called "STOP Russian War." Telegram, which does little policing of its content, has also became a hub for Russian propaganda and misinformation. Many pro-Kremlin channels have become popular, alongside accounts of journalists and other independent observers. Given the pro-privacy stance of the platform, it’s taken as a given that it’ll be used for a number of reasons, not all of them good. And Telegram has been attached to a fair few scandals related to terrorism, sexual exploitation and crime. Back in 2015, Vox described Telegram as “ISIS’ app of choice,” saying that the platform’s real use is the ability to use channels to distribute material to large groups at once. Telegram has acted to remove public channels affiliated with terrorism, but Pavel Durov reiterated that he had no business snooping on private conversations. In a message on his Telegram channel recently recounting the episode, Durov wrote: "I lost my company and my home, but would do it again – without hesitation."
from vn


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American