Telegram Group & Telegram Channel
<ቅናተኛ> ነኝ! በተለይ በእሷማ ቀናለሁ!

የዕድሜ'ዬን ግማሽ የኖርኩት እሷን 'ልመስል' ስፅፍ ሳጠፋ ነው። ግን እሷን 'መሆን' አልቻልኩም።

የመሰልኩ በመሰለኝ ሰአትም ፊቱ ስቆም ከሙሉዕነቴ ይልቅ ባዶነቴ ያሳብቅብኛል።

ፈት ነኝ! አምስቴ አግብቼ ፈትቻለው። ያፈገገልኝ ሁሉ ጓዶሎዬን መሙያ እየመሰለኝ ከመኝታ ለመሰየም ቀናት አይፈጅብኝም።

. . .እሷን ግን መሆን አልቻልኩም።

ራሴው ለገፋውት አጨብጫቢ እሻለው፣ ያላከበርኩትን ክብር እንዲከብር ስንቴ ጠብቄሃለሁ ግን እንኳን መሆን መምሰል ራሱ አልቻልኩም።

መቼ'ለት ነው . . . ወግ ማዕረግ በደምግባት አገኝ ብዬ ከአንዱ ልባም ተጠጋው....ምን ዋጋ አለው? ፈጣሪን አለመፍራቴ አይሎብኝ "ውበት ሀሰት ነው" ብሎ ተረተብኝ።

ያቺ አጥንቴ የነቀዘላት ሴት ግን የከበረች፣ በጎዳና ከመታየት ይልቅ በጓዳዋ የተሸሸገች ናት።

. . .አንድ ባል ነው ያላት እንደ ንጉስ ያከበረችው ከመኳንንት ጋር ሲቀመጥ 'ፐ'! ሞገስስ በሱ ቀረ የሚባልላት!

ከመስታዎቴ ቆሜ ገፄ ላይ እሷን ስስል ውዬ አድራለው። የኀላ ኀላ አለመሆኔ ጎልቶ ከወደ ህሊናዬ ያንቧርቅብኛል።

'ራስን መሆን' የሚባል መድኃኒት አለ። በሌላ መስታዎት ራሴን ለማየት ስፍጨረጨር ለካስ የማላድን መድኃኒተኛ ኖሬያለሁ። ፍለጋዬን አስተካክያለው "በአንዱ ቀመር የሌላው ስሌት አይሰራም!"

አሁን የተስፋ ጭላንጭል አለኝ። እኔ ውስጥ እሷን ከመፈለግ የሚልቀው እኔነቴ ጥልቀት እኔን መፈለጉ ነው። ምን አልባት መሲሁ ይመጣ ይሆናል። ጉዴን ነግሮ በፃፈለኝ ማንነት ሌላውን እሆን ብዬ የሰረዝኩ የደለዝኩትን ሽሮ በራስን መሆን ባህር ዳግም ካጠመቀኝ... እጠብቃለው!

እስከዚያው ግን:
የማያቋርጥ ጠፈጠፍ፣ በዝናብ ጊዜ የሚያፈስ ቤት የሚመስለውን አመሌን ይዤ ወጣለው። 'አእምሮ የጎደለው' አገኝ ይሆን ብዬ... 'ከአላዋቂዎች' መካከል ልዝብ አንደበቴን ሰምቶ የሚሳብ ልቦናዬን በጌጤ የመዘነ አይጠፋምና።

አርያም ተስፋዬ(2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/118
Create:
Last Update:

<ቅናተኛ> ነኝ! በተለይ በእሷማ ቀናለሁ!

የዕድሜ'ዬን ግማሽ የኖርኩት እሷን 'ልመስል' ስፅፍ ሳጠፋ ነው። ግን እሷን 'መሆን' አልቻልኩም።

የመሰልኩ በመሰለኝ ሰአትም ፊቱ ስቆም ከሙሉዕነቴ ይልቅ ባዶነቴ ያሳብቅብኛል።

ፈት ነኝ! አምስቴ አግብቼ ፈትቻለው። ያፈገገልኝ ሁሉ ጓዶሎዬን መሙያ እየመሰለኝ ከመኝታ ለመሰየም ቀናት አይፈጅብኝም።

. . .እሷን ግን መሆን አልቻልኩም።

ራሴው ለገፋውት አጨብጫቢ እሻለው፣ ያላከበርኩትን ክብር እንዲከብር ስንቴ ጠብቄሃለሁ ግን እንኳን መሆን መምሰል ራሱ አልቻልኩም።

መቼ'ለት ነው . . . ወግ ማዕረግ በደምግባት አገኝ ብዬ ከአንዱ ልባም ተጠጋው....ምን ዋጋ አለው? ፈጣሪን አለመፍራቴ አይሎብኝ "ውበት ሀሰት ነው" ብሎ ተረተብኝ።

ያቺ አጥንቴ የነቀዘላት ሴት ግን የከበረች፣ በጎዳና ከመታየት ይልቅ በጓዳዋ የተሸሸገች ናት።

. . .አንድ ባል ነው ያላት እንደ ንጉስ ያከበረችው ከመኳንንት ጋር ሲቀመጥ 'ፐ'! ሞገስስ በሱ ቀረ የሚባልላት!

ከመስታዎቴ ቆሜ ገፄ ላይ እሷን ስስል ውዬ አድራለው። የኀላ ኀላ አለመሆኔ ጎልቶ ከወደ ህሊናዬ ያንቧርቅብኛል።

'ራስን መሆን' የሚባል መድኃኒት አለ። በሌላ መስታዎት ራሴን ለማየት ስፍጨረጨር ለካስ የማላድን መድኃኒተኛ ኖሬያለሁ። ፍለጋዬን አስተካክያለው "በአንዱ ቀመር የሌላው ስሌት አይሰራም!"

አሁን የተስፋ ጭላንጭል አለኝ። እኔ ውስጥ እሷን ከመፈለግ የሚልቀው እኔነቴ ጥልቀት እኔን መፈለጉ ነው። ምን አልባት መሲሁ ይመጣ ይሆናል። ጉዴን ነግሮ በፃፈለኝ ማንነት ሌላውን እሆን ብዬ የሰረዝኩ የደለዝኩትን ሽሮ በራስን መሆን ባህር ዳግም ካጠመቀኝ... እጠብቃለው!

እስከዚያው ግን:
የማያቋርጥ ጠፈጠፍ፣ በዝናብ ጊዜ የሚያፈስ ቤት የሚመስለውን አመሌን ይዤ ወጣለው። 'አእምሮ የጎደለው' አገኝ ይሆን ብዬ... 'ከአላዋቂዎች' መካከል ልዝብ አንደበቴን ሰምቶ የሚሳብ ልቦናዬን በጌጤ የመዘነ አይጠፋምና።

አርያም ተስፋዬ(2013)

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/118

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

"He has kind of an old-school cyber-libertarian world view where technology is there to set you free," Maréchal said. Unlike Silicon Valley giants such as Facebook and Twitter, which run very public anti-disinformation programs, Brooking said: "Telegram is famously lax or absent in its content moderation policy." Stocks dropped on Friday afternoon, as gains made earlier in the day on hopes for diplomatic progress between Russia and Ukraine turned to losses. Technology stocks were hit particularly hard by higher bond yields. Official government accounts have also spread fake fact checks. An official Twitter account for the Russia diplomatic mission in Geneva shared a fake debunking video claiming without evidence that "Western and Ukrainian media are creating thousands of fake news on Russia every day." The video, which has amassed almost 30,000 views, offered a "how-to" spot misinformation. "There are several million Russians who can lift their head up from propaganda and try to look for other sources, and I'd say that most look for it on Telegram," he said.
from us


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American