Telegram Group & Telegram Channel
“ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” - የአቶ ክርስቲያን ታደለ ቤተሰብ

ለ1 አመት ከ4 ወራት በእስር ላይ ሆነው ፍትህ እየተጠባበቁ የሚገኙት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አበል አቶ ክርስቲያን ታደለ ከባድ የጤና እከል ስለገጠማቸው በሕይወት እንዲቆዩ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲጎበኟቸው የቅርብ ቤተሰባቸው አሳሰቡ።

ከፍትህ በፊት በሕይወት መቆየታቸው እንደሚቀድም ገልጸው፣ “ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።

የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ የጤናው ሁኔታ አሁንም በጣም አሳሰቢ ነው። ሰርጀሪ ተደርጎለት በሰዓታት ልዩነት ነው ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሰው። እዛም ሆኖ የደም መፍሰስ አለበት።

ሰኞ እለት ቀጠሮ ስለነበር ሂዶ ነበር የሚፈሰው ደም ምን እንደሆነ ለማወቅ ብለው ደም ወስደዋል። ባለፈው ከአንጀቱ ውስጥ በሰርጀሪ የወጣውንና የተወሰደውን ደም ውጤት ለማወቅ ለነገ ሐሙስ ተቀጥሯል።

ህመም አለው። ‘ከፍተኛ ህመም ነው የሚሰማኝ’ ነው የሚለው። ለጊዜው የሚያስታግስለትን መድኃኒት ነው የሚጠቀመው።

ከዚህ ቀደም አያመውም ነበር። አዋሽ አርባ ከሄደ በኋላ ነው የታመመው። አሁን ሲነግረን አሟቸው ከአዋሽ ወደ አዲስ አበባ አምጥተዋቸው ነበር። የዛኔም ምርመራና በቂ ህክምና አላደረገም። 

የዛኔ አብረዋቸው ከአዋሽ የመጡ አካላት ፕራይቬሲያቸውን በሚጥስ ሁኔታ ‘አብረን ገብተን እንመለከታለን ህክምናውን’ በሚል አለመግባባት ተፈጥሮ ህክምና ሳያገኙ ተመልሱ።

የዛኔ ቢታከም መታጠብ ነበር የሚጠበቅበት ለሰርጀሪም አይደርስም ነበር። ህመሙ በድርቀት የሚመጣ ሲሆን፣  አንጀቱ ውስጥ ሌላ የቋጠረ ነገር ነበር።

እሱንም አሁን ሀኪሞቹ ለማብራራት ቆርጠው ካወጡት በኋላ ለምርመራ ተወስዷል። ነገ ነው ውጤቱ የሚገለጸው።

የፍርድ ሂደቱን በተመለከተ በሚገርም ሁኔታ በጣም ረጅም፣ ረጅም የሆነ ቀጠሮ ነው የሚሰጠው። አሁንም ገና ለጥር 13 ነው ቀጠሮ የተሰጣቸው።
 
እንደ ቤተሰብ ከምንናገረው በላይ እጅግ በጣም ከባድ ነው ያለንበት ሁኔታ። እሱ በነበረበት ወቅት ጥሩ በሚባል ሁኔታ ላይ ነው የነበርነው፣ አሁን ላይ እንደዛ አይደለም።

ፍትህ እንጠብቃለን። ተስፋ አንቆርጥም። ግን አሁን ያለው ሂደት በፍትህ ስርዓቱ ክርስቲያንንም ተስፋ እንዳቆረጠው ነው በተደጋጋሚ የሚነግረን፣ እኛም የምናየው።

የደም መፍሰሱ እንኳ አልቆመለትም በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ያለው። የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ።

በቂ የሆነ ህክምና እንዲያገኝ ያለበትን ሁኔታ ተረድተው የሰብዓዊ መብት አካላት እንዲጎበኙት እንፈልጋለን ”
ሲሉ ተማጽነዋል።

(የአቶ ዮሐንስ ቧ ያለው የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ያቀረቡት እሮሮ በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/92943
Create:
Last Update:

“ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” - የአቶ ክርስቲያን ታደለ ቤተሰብ

ለ1 አመት ከ4 ወራት በእስር ላይ ሆነው ፍትህ እየተጠባበቁ የሚገኙት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አበል አቶ ክርስቲያን ታደለ ከባድ የጤና እከል ስለገጠማቸው በሕይወት እንዲቆዩ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲጎበኟቸው የቅርብ ቤተሰባቸው አሳሰቡ።

ከፍትህ በፊት በሕይወት መቆየታቸው እንደሚቀድም ገልጸው፣ “ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።

የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ የጤናው ሁኔታ አሁንም በጣም አሳሰቢ ነው። ሰርጀሪ ተደርጎለት በሰዓታት ልዩነት ነው ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሰው። እዛም ሆኖ የደም መፍሰስ አለበት።

ሰኞ እለት ቀጠሮ ስለነበር ሂዶ ነበር የሚፈሰው ደም ምን እንደሆነ ለማወቅ ብለው ደም ወስደዋል። ባለፈው ከአንጀቱ ውስጥ በሰርጀሪ የወጣውንና የተወሰደውን ደም ውጤት ለማወቅ ለነገ ሐሙስ ተቀጥሯል።

ህመም አለው። ‘ከፍተኛ ህመም ነው የሚሰማኝ’ ነው የሚለው። ለጊዜው የሚያስታግስለትን መድኃኒት ነው የሚጠቀመው።

ከዚህ ቀደም አያመውም ነበር። አዋሽ አርባ ከሄደ በኋላ ነው የታመመው። አሁን ሲነግረን አሟቸው ከአዋሽ ወደ አዲስ አበባ አምጥተዋቸው ነበር። የዛኔም ምርመራና በቂ ህክምና አላደረገም። 

የዛኔ አብረዋቸው ከአዋሽ የመጡ አካላት ፕራይቬሲያቸውን በሚጥስ ሁኔታ ‘አብረን ገብተን እንመለከታለን ህክምናውን’ በሚል አለመግባባት ተፈጥሮ ህክምና ሳያገኙ ተመልሱ።

የዛኔ ቢታከም መታጠብ ነበር የሚጠበቅበት ለሰርጀሪም አይደርስም ነበር። ህመሙ በድርቀት የሚመጣ ሲሆን፣  አንጀቱ ውስጥ ሌላ የቋጠረ ነገር ነበር።

እሱንም አሁን ሀኪሞቹ ለማብራራት ቆርጠው ካወጡት በኋላ ለምርመራ ተወስዷል። ነገ ነው ውጤቱ የሚገለጸው።

የፍርድ ሂደቱን በተመለከተ በሚገርም ሁኔታ በጣም ረጅም፣ ረጅም የሆነ ቀጠሮ ነው የሚሰጠው። አሁንም ገና ለጥር 13 ነው ቀጠሮ የተሰጣቸው።
 
እንደ ቤተሰብ ከምንናገረው በላይ እጅግ በጣም ከባድ ነው ያለንበት ሁኔታ። እሱ በነበረበት ወቅት ጥሩ በሚባል ሁኔታ ላይ ነው የነበርነው፣ አሁን ላይ እንደዛ አይደለም።

ፍትህ እንጠብቃለን። ተስፋ አንቆርጥም። ግን አሁን ያለው ሂደት በፍትህ ስርዓቱ ክርስቲያንንም ተስፋ እንዳቆረጠው ነው በተደጋጋሚ የሚነግረን፣ እኛም የምናየው።

የደም መፍሰሱ እንኳ አልቆመለትም በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ያለው። የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ።

በቂ የሆነ ህክምና እንዲያገኝ ያለበትን ሁኔታ ተረድተው የሰብዓዊ መብት አካላት እንዲጎበኙት እንፈልጋለን ”
ሲሉ ተማጽነዋል።

(የአቶ ዮሐንስ ቧ ያለው የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ያቀረቡት እሮሮ በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/92943

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

As the war in Ukraine rages, the messaging app Telegram has emerged as the go-to place for unfiltered live war updates for both Ukrainian refugees and increasingly isolated Russians alike. "There is a significant risk of insider threat or hacking of Telegram systems that could expose all of these chats to the Russian government," said Eva Galperin with the Electronic Frontier Foundation, which has called for Telegram to improve its privacy practices. In addition, Telegram's architecture limits the ability to slow the spread of false information: the lack of a central public feed, and the fact that comments are easily disabled in channels, reduce the space for public pushback. Emerson Brooking, a disinformation expert at the Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, said: "Back in the Wild West period of content moderation, like 2014 or 2015, maybe they could have gotten away with it, but it stands in marked contrast with how other companies run themselves today." Recently, Durav wrote on his Telegram channel that users' right to privacy, in light of the war in Ukraine, is "sacred, now more than ever."
from ye


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American