Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል። ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል። ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ…
#TPLF

" የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " - በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ

በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ከጥር 5 እስከ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ አተኩሮ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።

ይህንን ተከትሎ ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም ቡድኑ ፦
- እስከ አሁን ያልተረጋገጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት፤
- ተፈናቃዮች እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው አለመመለስ፤
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያወጣውን መግለጫ፤
- የፕሪቶሪያ የሰላም ውል አፈፃፀም በሚሉ አጀንዳዎች ላይ መወያየቱን ገልጾ " ቀጣይ የመፍትሄ እና የትግል አቅጣጫ አስቀምጫለሁ " ብሏል።

የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ ፤ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት እውቅና የሰጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት አለመረጋገጡ ጠቅሶ " ተፈናቃይ እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው ሃዘን እና ቁጣ ተስምተኞናል ይህንን አስመልክቶ ' ይበቃል ' በሚል የተካሄደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ እደግፋለሁ " ብሏል።

ቡድኑ በመግለጫው " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ እንዳይፈፀም የኢትዮጵያ መንግስት እንቅፋት እየሆነ ነው ፡ በትግራይ ውስጥ የበቀለ #ከሃዲ_ሃይልም በተጨማሪ ስምምነቱ እያደናቀፈ ነው " የሚል ክስ አሰምቷል።

እንዴት እንደሆነ ባያብራራም " ችግሩ ከስር መሰረቱ ለመለወጥ ቆርጬ ተነስቻለሁ " ብሏል።

በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ DDR ተቀባይነት ያለው እንደሆነ የገለፀም ሲሆን " ይሁን እንጂ DDR እንደምክንያት በመጠቀም የትግራይ ሰራዊት ለማፍረስ እየተደረገ ያለው ሴራ ተቀባይነተ የለውም " ሲል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ህወሓት ህጋዊ ጉባኤ እንዲያካሂድ በማስመልከት በቅርቡ ያወጣው ቀን ገደብ ያካተተ መግለጫ አስመልክቶ በሰጠው ምላሽ ፥ " ቦርዱ ' ጉባኤ አካሂዱ ' የሚል ጨምሮ በተንኮል የተተበተቡ የተለያዩ  ትእዛዞች ከመስጠት ተቆጥቦ የተፈጠሩ ልዩነቶች  በፓለቲካዊ ውይይት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት በማስቀጠሉ ላይ ያተኩር "  ብሏል።

" ህወሓት ሁሌም ለሁለትዮሽ ውይይት ዝግጁ ነው ፤ የትግራይ ህዝብ ትግል እና መስዋእትነት የሚያራክስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔ ግን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " ሲል አቋሙን አንጸባርቋል።

ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደሩ በማቋቋም የአንበሳ ድርሻ እንደነበረው እና እንዳለው የጠቀሰው መግለጫው " አሁንም እንዲጠናከር ይሰራል ይሁን እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማጠናከር እና ለመቆጣጠር በሚል ይቋቋማል የሚባለው ካውንስል አካል መሆን አልፈግም " ሲል ግልፅ አድርጓል።

በሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ በመግለጫው ማጠቃለያ ፤ " የኢትዮጵያ መንግስት ከጣልቃ ገብነት ተቆጥቦ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በቅን ልቦና በመፈፀም ለዘላቂ ሰላም እንዲሰራ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል። 

የህወሓት ቡድን ለሁለት ተከፍሎ የለየለት አለመግባባት ውስጥ ከገባ ወራት የተቆጠሩ ሲሆን ከወራት በፊት ለሁለት የተከፈሉት አመራሮች እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች አዲስ አበባ ሄደው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት አድርገው ነበር።

ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ግን እስከ ዛሬ መግባባት ሳይፈጥሩ በመግላጫ ምልልስ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ህወሓት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን በመግለጽ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጾ ነበር።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም። በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93809
Create:
Last Update:

#TPLF

" የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " - በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ

በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ከጥር 5 እስከ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ አተኩሮ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።

ይህንን ተከትሎ ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም ቡድኑ ፦
- እስከ አሁን ያልተረጋገጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት፤
- ተፈናቃዮች እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው አለመመለስ፤
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያወጣውን መግለጫ፤
- የፕሪቶሪያ የሰላም ውል አፈፃፀም በሚሉ አጀንዳዎች ላይ መወያየቱን ገልጾ " ቀጣይ የመፍትሄ እና የትግል አቅጣጫ አስቀምጫለሁ " ብሏል።

የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ ፤ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት እውቅና የሰጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት አለመረጋገጡ ጠቅሶ " ተፈናቃይ እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው ሃዘን እና ቁጣ ተስምተኞናል ይህንን አስመልክቶ ' ይበቃል ' በሚል የተካሄደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ እደግፋለሁ " ብሏል።

ቡድኑ በመግለጫው " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ እንዳይፈፀም የኢትዮጵያ መንግስት እንቅፋት እየሆነ ነው ፡ በትግራይ ውስጥ የበቀለ #ከሃዲ_ሃይልም በተጨማሪ ስምምነቱ እያደናቀፈ ነው " የሚል ክስ አሰምቷል።

እንዴት እንደሆነ ባያብራራም " ችግሩ ከስር መሰረቱ ለመለወጥ ቆርጬ ተነስቻለሁ " ብሏል።

በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ DDR ተቀባይነት ያለው እንደሆነ የገለፀም ሲሆን " ይሁን እንጂ DDR እንደምክንያት በመጠቀም የትግራይ ሰራዊት ለማፍረስ እየተደረገ ያለው ሴራ ተቀባይነተ የለውም " ሲል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ህወሓት ህጋዊ ጉባኤ እንዲያካሂድ በማስመልከት በቅርቡ ያወጣው ቀን ገደብ ያካተተ መግለጫ አስመልክቶ በሰጠው ምላሽ ፥ " ቦርዱ ' ጉባኤ አካሂዱ ' የሚል ጨምሮ በተንኮል የተተበተቡ የተለያዩ  ትእዛዞች ከመስጠት ተቆጥቦ የተፈጠሩ ልዩነቶች  በፓለቲካዊ ውይይት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት በማስቀጠሉ ላይ ያተኩር "  ብሏል።

" ህወሓት ሁሌም ለሁለትዮሽ ውይይት ዝግጁ ነው ፤ የትግራይ ህዝብ ትግል እና መስዋእትነት የሚያራክስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔ ግን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " ሲል አቋሙን አንጸባርቋል።

ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደሩ በማቋቋም የአንበሳ ድርሻ እንደነበረው እና እንዳለው የጠቀሰው መግለጫው " አሁንም እንዲጠናከር ይሰራል ይሁን እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማጠናከር እና ለመቆጣጠር በሚል ይቋቋማል የሚባለው ካውንስል አካል መሆን አልፈግም " ሲል ግልፅ አድርጓል።

በሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ በመግለጫው ማጠቃለያ ፤ " የኢትዮጵያ መንግስት ከጣልቃ ገብነት ተቆጥቦ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በቅን ልቦና በመፈፀም ለዘላቂ ሰላም እንዲሰራ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል። 

የህወሓት ቡድን ለሁለት ተከፍሎ የለየለት አለመግባባት ውስጥ ከገባ ወራት የተቆጠሩ ሲሆን ከወራት በፊት ለሁለት የተከፈሉት አመራሮች እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች አዲስ አበባ ሄደው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት አድርገው ነበር።

ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ግን እስከ ዛሬ መግባባት ሳይፈጥሩ በመግላጫ ምልልስ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ህወሓት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን በመግለጽ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጾ ነበር።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም። በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93809

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

"Markets were cheering this economic recovery and return to strong economic growth, but the cheers will turn to tears if the inflation outbreak pushes businesses and consumers to the brink of recession," he added. In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed. Sebi said data, emails and other documents are being retrieved from the seized devices and detailed investigation is in progress. The S&P 500 fell 1.3% to 4,204.36, and the Dow Jones Industrial Average was down 0.7% to 32,943.33. The Dow posted a fifth straight weekly loss — its longest losing streak since 2019. The Nasdaq Composite tumbled 2.2% to 12,843.81. Though all three indexes opened in the green, stocks took a turn after a new report showed U.S. consumer sentiment deteriorated more than expected in early March as consumers' inflation expectations soared to the highest since 1981. The fake Zelenskiy account reached 20,000 followers on Telegram before it was shut down, a remedial action that experts say is all too rare.
from ye


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American