Telegram Group & Telegram Channel
<ቅናተኛ> ነኝ! በተለይ በእሷማ ቀናለሁ!

የዕድሜ'ዬን ግማሽ የኖርኩት እሷን 'ልመስል' ስፅፍ ሳጠፋ ነው። ግን እሷን 'መሆን' አልቻልኩም።

የመሰልኩ በመሰለኝ ሰአትም ፊቱ ስቆም ከሙሉዕነቴ ይልቅ ባዶነቴ ያሳብቅብኛል።

ፈት ነኝ! አምስቴ አግብቼ ፈትቻለው። ያፈገገልኝ ሁሉ ጓዶሎዬን መሙያ እየመሰለኝ ከመኝታ ለመሰየም ቀናት አይፈጅብኝም።

. . .እሷን ግን መሆን አልቻልኩም።

ራሴው ለገፋውት አጨብጫቢ እሻለው፣ ያላከበርኩትን ክብር እንዲከብር ስንቴ ጠብቄሃለሁ ግን እንኳን መሆን መምሰል ራሱ አልቻልኩም።

መቼ'ለት ነው . . . ወግ ማዕረግ በደምግባት አገኝ ብዬ ከአንዱ ልባም ተጠጋው....ምን ዋጋ አለው? ፈጣሪን አለመፍራቴ አይሎብኝ "ውበት ሀሰት ነው" ብሎ ተረተብኝ።

ያቺ አጥንቴ የነቀዘላት ሴት ግን የከበረች፣ በጎዳና ከመታየት ይልቅ በጓዳዋ የተሸሸገች ናት።

. . .አንድ ባል ነው ያላት እንደ ንጉስ ያከበረችው ከመኳንንት ጋር ሲቀመጥ 'ፐ'! ሞገስስ በሱ ቀረ የሚባልላት!

ከመስታዎቴ ቆሜ ገፄ ላይ እሷን ስስል ውዬ አድራለው። የኀላ ኀላ አለመሆኔ ጎልቶ ከወደ ህሊናዬ ያንቧርቅብኛል።

'ራስን መሆን' የሚባል መድኃኒት አለ። በሌላ መስታዎት ራሴን ለማየት ስፍጨረጨር ለካስ የማላድን መድኃኒተኛ ኖሬያለሁ። ፍለጋዬን አስተካክያለው "በአንዱ ቀመር የሌላው ስሌት አይሰራም!"

አሁን የተስፋ ጭላንጭል አለኝ። እኔ ውስጥ እሷን ከመፈለግ የሚልቀው እኔነቴ ጥልቀት እኔን መፈለጉ ነው። ምን አልባት መሲሁ ይመጣ ይሆናል። ጉዴን ነግሮ በፃፈለኝ ማንነት ሌላውን እሆን ብዬ የሰረዝኩ የደለዝኩትን ሽሮ በራስን መሆን ባህር ዳግም ካጠመቀኝ... እጠብቃለው!

እስከዚያው ግን:
የማያቋርጥ ጠፈጠፍ፣ በዝናብ ጊዜ የሚያፈስ ቤት የሚመስለውን አመሌን ይዤ ወጣለው። 'አእምሮ የጎደለው' አገኝ ይሆን ብዬ... 'ከአላዋቂዎች' መካከል ልዝብ አንደበቴን ሰምቶ የሚሳብ ልቦናዬን በጌጤ የመዘነ አይጠፋምና።

አርያም ተስፋዬ(2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/118
Create:
Last Update:

<ቅናተኛ> ነኝ! በተለይ በእሷማ ቀናለሁ!

የዕድሜ'ዬን ግማሽ የኖርኩት እሷን 'ልመስል' ስፅፍ ሳጠፋ ነው። ግን እሷን 'መሆን' አልቻልኩም።

የመሰልኩ በመሰለኝ ሰአትም ፊቱ ስቆም ከሙሉዕነቴ ይልቅ ባዶነቴ ያሳብቅብኛል።

ፈት ነኝ! አምስቴ አግብቼ ፈትቻለው። ያፈገገልኝ ሁሉ ጓዶሎዬን መሙያ እየመሰለኝ ከመኝታ ለመሰየም ቀናት አይፈጅብኝም።

. . .እሷን ግን መሆን አልቻልኩም።

ራሴው ለገፋውት አጨብጫቢ እሻለው፣ ያላከበርኩትን ክብር እንዲከብር ስንቴ ጠብቄሃለሁ ግን እንኳን መሆን መምሰል ራሱ አልቻልኩም።

መቼ'ለት ነው . . . ወግ ማዕረግ በደምግባት አገኝ ብዬ ከአንዱ ልባም ተጠጋው....ምን ዋጋ አለው? ፈጣሪን አለመፍራቴ አይሎብኝ "ውበት ሀሰት ነው" ብሎ ተረተብኝ።

ያቺ አጥንቴ የነቀዘላት ሴት ግን የከበረች፣ በጎዳና ከመታየት ይልቅ በጓዳዋ የተሸሸገች ናት።

. . .አንድ ባል ነው ያላት እንደ ንጉስ ያከበረችው ከመኳንንት ጋር ሲቀመጥ 'ፐ'! ሞገስስ በሱ ቀረ የሚባልላት!

ከመስታዎቴ ቆሜ ገፄ ላይ እሷን ስስል ውዬ አድራለው። የኀላ ኀላ አለመሆኔ ጎልቶ ከወደ ህሊናዬ ያንቧርቅብኛል።

'ራስን መሆን' የሚባል መድኃኒት አለ። በሌላ መስታዎት ራሴን ለማየት ስፍጨረጨር ለካስ የማላድን መድኃኒተኛ ኖሬያለሁ። ፍለጋዬን አስተካክያለው "በአንዱ ቀመር የሌላው ስሌት አይሰራም!"

አሁን የተስፋ ጭላንጭል አለኝ። እኔ ውስጥ እሷን ከመፈለግ የሚልቀው እኔነቴ ጥልቀት እኔን መፈለጉ ነው። ምን አልባት መሲሁ ይመጣ ይሆናል። ጉዴን ነግሮ በፃፈለኝ ማንነት ሌላውን እሆን ብዬ የሰረዝኩ የደለዝኩትን ሽሮ በራስን መሆን ባህር ዳግም ካጠመቀኝ... እጠብቃለው!

እስከዚያው ግን:
የማያቋርጥ ጠፈጠፍ፣ በዝናብ ጊዜ የሚያፈስ ቤት የሚመስለውን አመሌን ይዤ ወጣለው። 'አእምሮ የጎደለው' አገኝ ይሆን ብዬ... 'ከአላዋቂዎች' መካከል ልዝብ አንደበቴን ሰምቶ የሚሳብ ልቦናዬን በጌጤ የመዘነ አይጠፋምና።

አርያም ተስፋዬ(2013)

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/118

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Just days after Russia invaded Ukraine, Durov wrote that Telegram was "increasingly becoming a source of unverified information," and he worried about the app being used to "incite ethnic hatred." Unlike Silicon Valley giants such as Facebook and Twitter, which run very public anti-disinformation programs, Brooking said: "Telegram is famously lax or absent in its content moderation policy." In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed. In addition, Telegram now supports the use of third-party streaming tools like OBS Studio and XSplit to broadcast live video, allowing users to add overlays and multi-screen layouts for a more professional look. The fake Zelenskiy account reached 20,000 followers on Telegram before it was shut down, a remedial action that experts say is all too rare.
from ye


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American