Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-93080-93081-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/93081 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🚨“ አቶ ክርስቲያን ታደለና ዮሐንስ ቧያለው ዛሬ የሐኪም ቀጠሮ ነበራቸው ማረሚያ ቤቱ አልወሰዳቸውም ” - ቤተሰቦቻቸው 🔴 “ በሕይወት የመኖር መብታቸውን ነው ያሳጧቸው። የእስረኛ ዝውውር ወይስ በሕይወት የመኖር መብት ነው የሚቀድመው ? ” - ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ አዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት ባደረባቸው የጤና እክል በወቅቱ ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት ህመም የተዳረጉት አቶ…
“ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው ” - ጉዳዩን የሚከታተሉ አካል

ለ1 ዓመት ከ5 ወር በእስራት ላይ የሚገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው አብረዋቸው ከነበሩት 41 እስረኞች ተለይተው “ ለሕይወታቸው አስጊ ወደሆነ ቦታ ” ለማዘወር ተገደዋል ይህ ደግሞ ጭንቀት ፈጥሮብናል ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ሰኞ ታኀሳስ 14 ቀን 2017 ዓ/ም 41 እስረኞች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ እንደተዘዋወሩ ገልጸው፣ አቶ ዮሐንስን ለይተው “ በ‘ሸኔ ተጠርጥረው’ ካሉ ሰዎች " ጋር ወስደዋቸዋል ሲሉ ጠቁመዋል።

በመሆኑም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ያሉበትን ቦታ ጎብኝተው የአቶ ዮሐንስን ሕይወት ደህንነት እንዲያረጋግጡ ጠይቀዋል።

ስለአቶ ዮሐንስ ቧያለው በዝርዝር የተባለው ምንድን ነው ?

“ ትላንት እስረኞቹን ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ አዘዋውረዋል። 41 እስረኞችን ነው ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የወሰዱት። 

ከዚያ በኋላ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው አስቀርተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው።

እዛ ውስጥ ያሉት በ'ሸኔ' ተጠርጥረው ያሉ ሰዎች ናቸው።  ለይተው ከእነርሱ ጋር ነው  ያስቀመጡት። ‘ሸኔ ናችሁ’ ተብለው የታሰሩ፣ ‘ሸኔ’ የተባሉ ልጆች ናቸው እዛ ያሉት።

ይሄ ሁኔታውን ያከብደዋል። በዛ ላይ ደግሞ ኦፕራሲዮን ከተሰራ ሁለት ሳምንቱ ነው። አሁን ካስገቡት ቦታ አልጋ የሚባል ነገር የለም። ባዶ መሬት ላይ ነው እየተኛ ያለው።

አቶ ዮሐንስ አሁን የገባበት ቦታ በጣም የሚያሰጋ፣ እንኳን ኦፕራሲዮን የተደረገ ጤነኛ ሰውም የሚታመምበት ክፍል ነው። ቤቱ በጣም ቅዝቃዜ ስላለው እያነከሰ ነው። ”
ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ዮሐንስ ከ41 እስረኞች ተለይተው የተወሰዱት ምክንያት በግልጽ ሳይታወቅና ከአቶ ክርስቲያን ታደለ ጋር ኦፕራሲዮን ተሰርተው የነበረ ቢሆንም በቀጠሯቸው ቀን ሀኪም ቤት ሳይሄዱ በቀሩበት ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል።

አሁንም የጤናቸው ጉዳይ አሳሳቢ እንደሆነ፣ ለአቶ ዮሐንስ ማስታገሻ መድኃኒት እንኳ ለመውሰድ ፈቃድ እንዳልተገኘ፣ ቁስላቸውን መመርመር ባለመቻላቸው በጠና እየታመሙ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካላት ጠቁመዋል።

አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና ክርስቲያን ታደለ በአዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት በጠና ታመው በጊዜው ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት በሽታ ተጋልጠው ከቆዩ በኋላ ከሳምንታት በፊት ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም በቀጠሯቸው ቀን ወደ ህክምና ለመሄድ መከልከላቸውን መነገሩ ይታወሳል።

(የአቶ ዮሐንስን የቦታ ለውጥ እንዲገመግሙ መልክዕት የተላለፈላቸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ድርጊቱን ገምግመው ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ ማብራሪያቸው በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93081
Create:
Last Update:

“ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው ” - ጉዳዩን የሚከታተሉ አካል

ለ1 ዓመት ከ5 ወር በእስራት ላይ የሚገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው አብረዋቸው ከነበሩት 41 እስረኞች ተለይተው “ ለሕይወታቸው አስጊ ወደሆነ ቦታ ” ለማዘወር ተገደዋል ይህ ደግሞ ጭንቀት ፈጥሮብናል ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ሰኞ ታኀሳስ 14 ቀን 2017 ዓ/ም 41 እስረኞች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ እንደተዘዋወሩ ገልጸው፣ አቶ ዮሐንስን ለይተው “ በ‘ሸኔ ተጠርጥረው’ ካሉ ሰዎች " ጋር ወስደዋቸዋል ሲሉ ጠቁመዋል።

በመሆኑም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ያሉበትን ቦታ ጎብኝተው የአቶ ዮሐንስን ሕይወት ደህንነት እንዲያረጋግጡ ጠይቀዋል።

ስለአቶ ዮሐንስ ቧያለው በዝርዝር የተባለው ምንድን ነው ?

“ ትላንት እስረኞቹን ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ አዘዋውረዋል። 41 እስረኞችን ነው ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የወሰዱት። 

ከዚያ በኋላ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው አስቀርተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው።

እዛ ውስጥ ያሉት በ'ሸኔ' ተጠርጥረው ያሉ ሰዎች ናቸው።  ለይተው ከእነርሱ ጋር ነው  ያስቀመጡት። ‘ሸኔ ናችሁ’ ተብለው የታሰሩ፣ ‘ሸኔ’ የተባሉ ልጆች ናቸው እዛ ያሉት።

ይሄ ሁኔታውን ያከብደዋል። በዛ ላይ ደግሞ ኦፕራሲዮን ከተሰራ ሁለት ሳምንቱ ነው። አሁን ካስገቡት ቦታ አልጋ የሚባል ነገር የለም። ባዶ መሬት ላይ ነው እየተኛ ያለው።

አቶ ዮሐንስ አሁን የገባበት ቦታ በጣም የሚያሰጋ፣ እንኳን ኦፕራሲዮን የተደረገ ጤነኛ ሰውም የሚታመምበት ክፍል ነው። ቤቱ በጣም ቅዝቃዜ ስላለው እያነከሰ ነው። ”
ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ዮሐንስ ከ41 እስረኞች ተለይተው የተወሰዱት ምክንያት በግልጽ ሳይታወቅና ከአቶ ክርስቲያን ታደለ ጋር ኦፕራሲዮን ተሰርተው የነበረ ቢሆንም በቀጠሯቸው ቀን ሀኪም ቤት ሳይሄዱ በቀሩበት ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል።

አሁንም የጤናቸው ጉዳይ አሳሳቢ እንደሆነ፣ ለአቶ ዮሐንስ ማስታገሻ መድኃኒት እንኳ ለመውሰድ ፈቃድ እንዳልተገኘ፣ ቁስላቸውን መመርመር ባለመቻላቸው በጠና እየታመሙ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካላት ጠቁመዋል።

አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና ክርስቲያን ታደለ በአዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት በጠና ታመው በጊዜው ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት በሽታ ተጋልጠው ከቆዩ በኋላ ከሳምንታት በፊት ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም በቀጠሯቸው ቀን ወደ ህክምና ለመሄድ መከልከላቸውን መነገሩ ይታወሳል።

(የአቶ ዮሐንስን የቦታ ለውጥ እንዲገመግሙ መልክዕት የተላለፈላቸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ድርጊቱን ገምግመው ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ ማብራሪያቸው በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93081

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The regulator took order for the search and seizure operation from Judge Purushottam B Jadhav, Sebi Special Judge / Additional Sessions Judge. Two days after Russia invaded Ukraine, an account on the Telegram messaging platform posing as President Volodymyr Zelenskiy urged his armed forces to surrender. Perpetrators of these scams will create a public group on Telegram to promote these investment packages that are usually accompanied by fake testimonies and sometimes advertised as being Shariah-compliant. Interested investors will be asked to directly message the representatives to begin investing in the various investment packages offered. Asked about its stance on disinformation, Telegram spokesperson Remi Vaughn told AFP: "As noted by our CEO, the sheer volume of information being shared on channels makes it extremely difficult to verify, so it's important that users double-check what they read." In this regard, Sebi collaborated with the Telecom Regulatory Authority of India (TRAI) to reduce the vulnerability of the securities market to manipulation through misuse of mass communication medium like bulk SMS.
from fr


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American