Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🚨“ አቶ ክርስቲያን ታደለና ዮሐንስ ቧያለው ዛሬ የሐኪም ቀጠሮ ነበራቸው ማረሚያ ቤቱ አልወሰዳቸውም ” - ቤተሰቦቻቸው 🔴 “ በሕይወት የመኖር መብታቸውን ነው ያሳጧቸው። የእስረኛ ዝውውር ወይስ በሕይወት የመኖር መብት ነው የሚቀድመው ? ” - ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ አዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት ባደረባቸው የጤና እክል በወቅቱ ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት ህመም የተዳረጉት አቶ…
“ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው ” - ጉዳዩን የሚከታተሉ አካል

ለ1 ዓመት ከ5 ወር በእስራት ላይ የሚገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው አብረዋቸው ከነበሩት 41 እስረኞች ተለይተው “ ለሕይወታቸው አስጊ ወደሆነ ቦታ ” ለማዘወር ተገደዋል ይህ ደግሞ ጭንቀት ፈጥሮብናል ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ሰኞ ታኀሳስ 14 ቀን 2017 ዓ/ም 41 እስረኞች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ እንደተዘዋወሩ ገልጸው፣ አቶ ዮሐንስን ለይተው “ በ‘ሸኔ ተጠርጥረው’ ካሉ ሰዎች " ጋር ወስደዋቸዋል ሲሉ ጠቁመዋል።

በመሆኑም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ያሉበትን ቦታ ጎብኝተው የአቶ ዮሐንስን ሕይወት ደህንነት እንዲያረጋግጡ ጠይቀዋል።

ስለአቶ ዮሐንስ ቧያለው በዝርዝር የተባለው ምንድን ነው ?

“ ትላንት እስረኞቹን ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ አዘዋውረዋል። 41 እስረኞችን ነው ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የወሰዱት። 

ከዚያ በኋላ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው አስቀርተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው።

እዛ ውስጥ ያሉት በ'ሸኔ' ተጠርጥረው ያሉ ሰዎች ናቸው።  ለይተው ከእነርሱ ጋር ነው  ያስቀመጡት። ‘ሸኔ ናችሁ’ ተብለው የታሰሩ፣ ‘ሸኔ’ የተባሉ ልጆች ናቸው እዛ ያሉት።

ይሄ ሁኔታውን ያከብደዋል። በዛ ላይ ደግሞ ኦፕራሲዮን ከተሰራ ሁለት ሳምንቱ ነው። አሁን ካስገቡት ቦታ አልጋ የሚባል ነገር የለም። ባዶ መሬት ላይ ነው እየተኛ ያለው።

አቶ ዮሐንስ አሁን የገባበት ቦታ በጣም የሚያሰጋ፣ እንኳን ኦፕራሲዮን የተደረገ ጤነኛ ሰውም የሚታመምበት ክፍል ነው። ቤቱ በጣም ቅዝቃዜ ስላለው እያነከሰ ነው። ”
ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ዮሐንስ ከ41 እስረኞች ተለይተው የተወሰዱት ምክንያት በግልጽ ሳይታወቅና ከአቶ ክርስቲያን ታደለ ጋር ኦፕራሲዮን ተሰርተው የነበረ ቢሆንም በቀጠሯቸው ቀን ሀኪም ቤት ሳይሄዱ በቀሩበት ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል።

አሁንም የጤናቸው ጉዳይ አሳሳቢ እንደሆነ፣ ለአቶ ዮሐንስ ማስታገሻ መድኃኒት እንኳ ለመውሰድ ፈቃድ እንዳልተገኘ፣ ቁስላቸውን መመርመር ባለመቻላቸው በጠና እየታመሙ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካላት ጠቁመዋል።

አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና ክርስቲያን ታደለ በአዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት በጠና ታመው በጊዜው ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት በሽታ ተጋልጠው ከቆዩ በኋላ ከሳምንታት በፊት ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም በቀጠሯቸው ቀን ወደ ህክምና ለመሄድ መከልከላቸውን መነገሩ ይታወሳል።

(የአቶ ዮሐንስን የቦታ ለውጥ እንዲገመግሙ መልክዕት የተላለፈላቸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ድርጊቱን ገምግመው ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ ማብራሪያቸው በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93081
Create:
Last Update:

“ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው ” - ጉዳዩን የሚከታተሉ አካል

ለ1 ዓመት ከ5 ወር በእስራት ላይ የሚገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው አብረዋቸው ከነበሩት 41 እስረኞች ተለይተው “ ለሕይወታቸው አስጊ ወደሆነ ቦታ ” ለማዘወር ተገደዋል ይህ ደግሞ ጭንቀት ፈጥሮብናል ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ሰኞ ታኀሳስ 14 ቀን 2017 ዓ/ም 41 እስረኞች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ እንደተዘዋወሩ ገልጸው፣ አቶ ዮሐንስን ለይተው “ በ‘ሸኔ ተጠርጥረው’ ካሉ ሰዎች " ጋር ወስደዋቸዋል ሲሉ ጠቁመዋል።

በመሆኑም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ያሉበትን ቦታ ጎብኝተው የአቶ ዮሐንስን ሕይወት ደህንነት እንዲያረጋግጡ ጠይቀዋል።

ስለአቶ ዮሐንስ ቧያለው በዝርዝር የተባለው ምንድን ነው ?

“ ትላንት እስረኞቹን ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ አዘዋውረዋል። 41 እስረኞችን ነው ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የወሰዱት። 

ከዚያ በኋላ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው አስቀርተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው።

እዛ ውስጥ ያሉት በ'ሸኔ' ተጠርጥረው ያሉ ሰዎች ናቸው።  ለይተው ከእነርሱ ጋር ነው  ያስቀመጡት። ‘ሸኔ ናችሁ’ ተብለው የታሰሩ፣ ‘ሸኔ’ የተባሉ ልጆች ናቸው እዛ ያሉት።

ይሄ ሁኔታውን ያከብደዋል። በዛ ላይ ደግሞ ኦፕራሲዮን ከተሰራ ሁለት ሳምንቱ ነው። አሁን ካስገቡት ቦታ አልጋ የሚባል ነገር የለም። ባዶ መሬት ላይ ነው እየተኛ ያለው።

አቶ ዮሐንስ አሁን የገባበት ቦታ በጣም የሚያሰጋ፣ እንኳን ኦፕራሲዮን የተደረገ ጤነኛ ሰውም የሚታመምበት ክፍል ነው። ቤቱ በጣም ቅዝቃዜ ስላለው እያነከሰ ነው። ”
ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ዮሐንስ ከ41 እስረኞች ተለይተው የተወሰዱት ምክንያት በግልጽ ሳይታወቅና ከአቶ ክርስቲያን ታደለ ጋር ኦፕራሲዮን ተሰርተው የነበረ ቢሆንም በቀጠሯቸው ቀን ሀኪም ቤት ሳይሄዱ በቀሩበት ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል።

አሁንም የጤናቸው ጉዳይ አሳሳቢ እንደሆነ፣ ለአቶ ዮሐንስ ማስታገሻ መድኃኒት እንኳ ለመውሰድ ፈቃድ እንዳልተገኘ፣ ቁስላቸውን መመርመር ባለመቻላቸው በጠና እየታመሙ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካላት ጠቁመዋል።

አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና ክርስቲያን ታደለ በአዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት በጠና ታመው በጊዜው ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት በሽታ ተጋልጠው ከቆዩ በኋላ ከሳምንታት በፊት ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም በቀጠሯቸው ቀን ወደ ህክምና ለመሄድ መከልከላቸውን መነገሩ ይታወሳል።

(የአቶ ዮሐንስን የቦታ ለውጥ እንዲገመግሙ መልክዕት የተላለፈላቸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ድርጊቱን ገምግመው ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ ማብራሪያቸው በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93081

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram does offer end-to-end encrypted communications through Secret Chats, but this is not the default setting. Standard conversations use the MTProto method, enabling server-client encryption but with them stored on the server for ease-of-access. This makes using Telegram across multiple devices simple, but also means that the regular Telegram chats you’re having with folks are not as secure as you may believe. Telegram has gained a reputation as the “secure” communications app in the post-Soviet states, but whenever you make choices about your digital security, it’s important to start by asking yourself, “What exactly am I securing? And who am I securing it from?” These questions should inform your decisions about whether you are using the right tool or platform for your digital security needs. Telegram is certainly not the most secure messaging app on the market right now. Its security model requires users to place a great deal of trust in Telegram’s ability to protect user data. For some users, this may be good enough for now. For others, it may be wiser to move to a different platform for certain kinds of high-risk communications. The last couple days have exemplified that uncertainty. On Thursday, news emerged that talks in Turkey between the Russia and Ukraine yielded no positive result. But on Friday, Reuters reported that Russian President Vladimir Putin said there had been some “positive shifts” in talks between the two sides. Messages are not fully encrypted by default. That means the company could, in theory, access the content of the messages, or be forced to hand over the data at the request of a government. In 2018, Russia banned Telegram although it reversed the prohibition two years later.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American