Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94108-94109-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94109 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
" ' ብር (ጉቦ) ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ " - ቅሬታ አቅራቢዎች በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ሳይት 3 የብሎክ 734 እና 735 ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገቡት የቆጣሪ እዳ ውዝግብ ምክንያት ሃይል ከተቋረጠባቸው 1 ወር ከ 5 ቀን መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ…
" ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ብሎክ 734 እና 735 የጋራ መኖሪያ መንደር የሚኖሩ ነዋሪዎች ከቆጣሪ እዳ ጋር በተገናኘ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ዝርዝር ምላሽ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

" ነዋሪዎቹ ሃይል የተቋረጠባቸው በየብሎኩ የገባላቸውን ቆጣሪዎች ትተው በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ለኮንስትራክሽን ሥራ የገባውን ቆጣሪ እንዳይቆጥር አድርገው ሲጠቀሙ በእኛ ኢንስፔክሽን ቲም (የምልከታ ቡድን) በ15/04/17 ዓ/ም በተረገ ምልከታ ተደርሶባቸው ነው።

በእኛ አሰራር መሰረት ደግሞ ቆጣሪን እንዳይቆጥር አድርጎ ሲጠቀም የተገኘ ካለ አገልግሎቱን በማቋረጥ ሂሳቡ ይሰላል በድጋሚ ሃይል ለማግኘት ያንን ሂሳብ መክፈል አለበት።

በዚህ ምክንያት ሃይል ተቋርጧል ከተቋረጠ በኋላ ሲጠቀሙ የነበሩትን ሂሳብ አስልተን በደብዳቤ ክፈሉ ብለን አሳውቀናቸዋል።

በእነሱ ስም ቆጣሪው ስለሌለ በቤቶች ልማት ጽ/ቤት ስም አሳውቀናቸዋል በተደጋጋሚ ለመክፈል ፈቃደኛ አልነበሩም ኤሌክትሪኩ ተቋርጦ ነው ያለው።

ቆጣሪው ቢሉ የወጣው በኮንትራክተሩ ሳይሆን በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛ የምናውቀው በኮንትራክተር የገባ ቆጣሪ የለም ውላችንም ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ነው ኮንትራክተሩን አናውቀውም።

አንድን ኮንትራክተር ሊቀጥረው የሚችለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛም ውል የሚኖረን ከኮንትራክተሩ ጋር ሳይሆን ኮንትራክተሩን ቀጥሮ ከሚያሰራው ተቋም ጋር ነው ሃላፊነቱን ወስዶ ደብዳቤ ጽፎ ቆጣሪ ይግባ የሚለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው።

በስርቆት ቆጣሪ በማሰናከል ኤሌክትሪክ ሲጠቀሙ ሲገኝ የመጀመሪያው እርምጃ አገልግሎት ተቋርጦ መንግስት ያጣውን ገንዘብ ታስቦ ክፈሉ ብሎ ማሳወቅ ነው ነዋሪዎች እኛን አይመለከትንም እያሉ ነው ነገር ግን እየተጠቀሙ ነው አይ ቤቶች ልማት እኔን አይመለከተኝም ኮንትራክተሩን ነው ካለም ሃላፊነት መውሰድ አለበት " ብለዋል።


አቶ ብርሃኑ ነዋሪዎቹ ቆጣሪው እንዳይቆጥር በማሰናከል ካርድ መሙላት ካቆሙ ጀምሮ በሦስት ቆጣሪዎች የተጠራቀመው እዳ ቅጣትን ጨምሮ 480,538 ብር መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንን ያህል መጠን ኤሌክትሪክ ሃይል የተጠቀሙት ተብለው ለቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተላከ ደብዳቤ የተገለጹት የጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ብሎክ 734 ፣ 735 ፣ 750 እና 751 ነዋሪዎች ሲሆኑ ነገር ግን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት በኮርፖሬሽኑ በኩል በመሆኑ የተጠቀሰውን ክፍያ እንዲፈጽም አገልግሎቱ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን በተደጋጋሚ መጠየቁን ነገር ግን እስካሁን ክፍያው አለመፈጸሙን አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።

ነዋሪዎች ሃይል ከቆጣሪው ጠልፈው አለመጠቀማቸውን እና ቆጣሪዎቹ መንገድ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ምክንያት ነዋሪ ያልሆኑ አካላት መስመሩን እንደሚጠቀሙ ይገልጻሉ ታውቁታላቹ ወይ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄ ዳይሬክተሩ ምላሽ ሰጥተዋል።

" በእኛ በኩል እንደዚህ አይነት ጥቆማ አልደረሰንም ይህንን ቆጣሪ ካስገባን በኋላ በየወሩ ለንባብ ስንመጣ እንዲሁም በእቅድ ምልከታ እናደርጋለን የተጠቀስነውን ችግር ያገኘነው ለምልከታ ስንመጣ ነው። ይሄንን ጥቆማ እንመለከተዋለን በቦታው ስንሄድ ግን የተባለውን ጉዳይ አልተመለከትንም " ብለዋል።

ቆጣሪዎቹ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ለግንባታ አላማ ነበር የተቀመጡት ግንባታው ከተጠናቀቀ ቆይቷል ለምን አልተነሱም ስንል ላነሳነው ጥያቄም።

" ቤቶች ልማት አገልግሎቱን ጨርሰናል ቆጣሪው ይነሳልን አገልግሎቱን አንጠቀመውም ብለው ደብዳቤ መጻፍ አለባቸው ውል አለን ዝም ብለን ቆጣሪ ማንሳት አይቻልም ይግባልን ተብሎ በደብዳቤ እንደተጠየቀው ሁሉ ይነሳልን ብለው ሲጠይቁ ብቻ ነው የሚነሳው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ዳይሬክተሩ ነዋሪዎች የተቋረጠው ሃይል ተመልሶ እንዲቀጠል ጉቦ ክፈሉ ያለን ባለሞያ አለ ሲሉ ላነሱት ቅሬታም " ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን ምላሽ የሚያካትት ይሆናል።

በተጨማሪም ነዋሪዎች ከተጠቀሱት ቆጣሪዎች ላይ ሃይል መቀጠላቸውን እና አለመቀጠላቸውን እንዲሁም ሌሎችም ነዋሪዎች ያቀረቧቸውን ቅሬታዎች በሚመለከት በቦታው ተገኝቶ ምልከታ ማድረግ እንደሚቻል የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቦታው በመገኘት ቅሬታውን በማጣራት የሚያሳውቅ መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94109
Create:
Last Update:

" ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ብሎክ 734 እና 735 የጋራ መኖሪያ መንደር የሚኖሩ ነዋሪዎች ከቆጣሪ እዳ ጋር በተገናኘ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ዝርዝር ምላሽ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

" ነዋሪዎቹ ሃይል የተቋረጠባቸው በየብሎኩ የገባላቸውን ቆጣሪዎች ትተው በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ለኮንስትራክሽን ሥራ የገባውን ቆጣሪ እንዳይቆጥር አድርገው ሲጠቀሙ በእኛ ኢንስፔክሽን ቲም (የምልከታ ቡድን) በ15/04/17 ዓ/ም በተረገ ምልከታ ተደርሶባቸው ነው።

በእኛ አሰራር መሰረት ደግሞ ቆጣሪን እንዳይቆጥር አድርጎ ሲጠቀም የተገኘ ካለ አገልግሎቱን በማቋረጥ ሂሳቡ ይሰላል በድጋሚ ሃይል ለማግኘት ያንን ሂሳብ መክፈል አለበት።

በዚህ ምክንያት ሃይል ተቋርጧል ከተቋረጠ በኋላ ሲጠቀሙ የነበሩትን ሂሳብ አስልተን በደብዳቤ ክፈሉ ብለን አሳውቀናቸዋል።

በእነሱ ስም ቆጣሪው ስለሌለ በቤቶች ልማት ጽ/ቤት ስም አሳውቀናቸዋል በተደጋጋሚ ለመክፈል ፈቃደኛ አልነበሩም ኤሌክትሪኩ ተቋርጦ ነው ያለው።

ቆጣሪው ቢሉ የወጣው በኮንትራክተሩ ሳይሆን በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛ የምናውቀው በኮንትራክተር የገባ ቆጣሪ የለም ውላችንም ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ነው ኮንትራክተሩን አናውቀውም።

አንድን ኮንትራክተር ሊቀጥረው የሚችለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛም ውል የሚኖረን ከኮንትራክተሩ ጋር ሳይሆን ኮንትራክተሩን ቀጥሮ ከሚያሰራው ተቋም ጋር ነው ሃላፊነቱን ወስዶ ደብዳቤ ጽፎ ቆጣሪ ይግባ የሚለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው።

በስርቆት ቆጣሪ በማሰናከል ኤሌክትሪክ ሲጠቀሙ ሲገኝ የመጀመሪያው እርምጃ አገልግሎት ተቋርጦ መንግስት ያጣውን ገንዘብ ታስቦ ክፈሉ ብሎ ማሳወቅ ነው ነዋሪዎች እኛን አይመለከትንም እያሉ ነው ነገር ግን እየተጠቀሙ ነው አይ ቤቶች ልማት እኔን አይመለከተኝም ኮንትራክተሩን ነው ካለም ሃላፊነት መውሰድ አለበት " ብለዋል።


አቶ ብርሃኑ ነዋሪዎቹ ቆጣሪው እንዳይቆጥር በማሰናከል ካርድ መሙላት ካቆሙ ጀምሮ በሦስት ቆጣሪዎች የተጠራቀመው እዳ ቅጣትን ጨምሮ 480,538 ብር መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንን ያህል መጠን ኤሌክትሪክ ሃይል የተጠቀሙት ተብለው ለቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተላከ ደብዳቤ የተገለጹት የጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ብሎክ 734 ፣ 735 ፣ 750 እና 751 ነዋሪዎች ሲሆኑ ነገር ግን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት በኮርፖሬሽኑ በኩል በመሆኑ የተጠቀሰውን ክፍያ እንዲፈጽም አገልግሎቱ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን በተደጋጋሚ መጠየቁን ነገር ግን እስካሁን ክፍያው አለመፈጸሙን አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።

ነዋሪዎች ሃይል ከቆጣሪው ጠልፈው አለመጠቀማቸውን እና ቆጣሪዎቹ መንገድ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ምክንያት ነዋሪ ያልሆኑ አካላት መስመሩን እንደሚጠቀሙ ይገልጻሉ ታውቁታላቹ ወይ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄ ዳይሬክተሩ ምላሽ ሰጥተዋል።

" በእኛ በኩል እንደዚህ አይነት ጥቆማ አልደረሰንም ይህንን ቆጣሪ ካስገባን በኋላ በየወሩ ለንባብ ስንመጣ እንዲሁም በእቅድ ምልከታ እናደርጋለን የተጠቀስነውን ችግር ያገኘነው ለምልከታ ስንመጣ ነው። ይሄንን ጥቆማ እንመለከተዋለን በቦታው ስንሄድ ግን የተባለውን ጉዳይ አልተመለከትንም " ብለዋል።

ቆጣሪዎቹ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ለግንባታ አላማ ነበር የተቀመጡት ግንባታው ከተጠናቀቀ ቆይቷል ለምን አልተነሱም ስንል ላነሳነው ጥያቄም።

" ቤቶች ልማት አገልግሎቱን ጨርሰናል ቆጣሪው ይነሳልን አገልግሎቱን አንጠቀመውም ብለው ደብዳቤ መጻፍ አለባቸው ውል አለን ዝም ብለን ቆጣሪ ማንሳት አይቻልም ይግባልን ተብሎ በደብዳቤ እንደተጠየቀው ሁሉ ይነሳልን ብለው ሲጠይቁ ብቻ ነው የሚነሳው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ዳይሬክተሩ ነዋሪዎች የተቋረጠው ሃይል ተመልሶ እንዲቀጠል ጉቦ ክፈሉ ያለን ባለሞያ አለ ሲሉ ላነሱት ቅሬታም " ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን ምላሽ የሚያካትት ይሆናል።

በተጨማሪም ነዋሪዎች ከተጠቀሱት ቆጣሪዎች ላይ ሃይል መቀጠላቸውን እና አለመቀጠላቸውን እንዲሁም ሌሎችም ነዋሪዎች ያቀረቧቸውን ቅሬታዎች በሚመለከት በቦታው ተገኝቶ ምልከታ ማድረግ እንደሚቻል የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቦታው በመገኘት ቅሬታውን በማጣራት የሚያሳውቅ መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94109

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Since January 2022, the SC has received a total of 47 complaints and enquiries on illegal investment schemes promoted through Telegram. These fraudulent schemes offer non-existent investment opportunities, promising very attractive and risk-free returns within a short span of time. They commonly offer unrealistic returns of as high as 1,000% within 24 hours or even within a few hours. In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed. Additionally, investors are often instructed to deposit monies into personal bank accounts of individuals who claim to represent a legitimate entity, and/or into an unrelated corporate account. To lend credence and to lure unsuspecting victims, perpetrators usually claim that their entity and/or the investment schemes are approved by financial authorities. Asked about its stance on disinformation, Telegram spokesperson Remi Vaughn told AFP: "As noted by our CEO, the sheer volume of information being shared on channels makes it extremely difficult to verify, so it's important that users double-check what they read." This ability to mix the public and the private, as well as the ability to use bots to engage with users has proved to be problematic. In early 2021, a database selling phone numbers pulled from Facebook was selling numbers for $20 per lookup. Similarly, security researchers found a network of deepfake bots on the platform that were generating images of people submitted by users to create non-consensual imagery, some of which involved children.
from sa


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American