Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94108-94109-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94109 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
" ' ብር (ጉቦ) ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ " - ቅሬታ አቅራቢዎች በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ሳይት 3 የብሎክ 734 እና 735 ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገቡት የቆጣሪ እዳ ውዝግብ ምክንያት ሃይል ከተቋረጠባቸው 1 ወር ከ 5 ቀን መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ…
" ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ብሎክ 734 እና 735 የጋራ መኖሪያ መንደር የሚኖሩ ነዋሪዎች ከቆጣሪ እዳ ጋር በተገናኘ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ዝርዝር ምላሽ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

" ነዋሪዎቹ ሃይል የተቋረጠባቸው በየብሎኩ የገባላቸውን ቆጣሪዎች ትተው በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ለኮንስትራክሽን ሥራ የገባውን ቆጣሪ እንዳይቆጥር አድርገው ሲጠቀሙ በእኛ ኢንስፔክሽን ቲም (የምልከታ ቡድን) በ15/04/17 ዓ/ም በተረገ ምልከታ ተደርሶባቸው ነው።

በእኛ አሰራር መሰረት ደግሞ ቆጣሪን እንዳይቆጥር አድርጎ ሲጠቀም የተገኘ ካለ አገልግሎቱን በማቋረጥ ሂሳቡ ይሰላል በድጋሚ ሃይል ለማግኘት ያንን ሂሳብ መክፈል አለበት።

በዚህ ምክንያት ሃይል ተቋርጧል ከተቋረጠ በኋላ ሲጠቀሙ የነበሩትን ሂሳብ አስልተን በደብዳቤ ክፈሉ ብለን አሳውቀናቸዋል።

በእነሱ ስም ቆጣሪው ስለሌለ በቤቶች ልማት ጽ/ቤት ስም አሳውቀናቸዋል በተደጋጋሚ ለመክፈል ፈቃደኛ አልነበሩም ኤሌክትሪኩ ተቋርጦ ነው ያለው።

ቆጣሪው ቢሉ የወጣው በኮንትራክተሩ ሳይሆን በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛ የምናውቀው በኮንትራክተር የገባ ቆጣሪ የለም ውላችንም ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ነው ኮንትራክተሩን አናውቀውም።

አንድን ኮንትራክተር ሊቀጥረው የሚችለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛም ውል የሚኖረን ከኮንትራክተሩ ጋር ሳይሆን ኮንትራክተሩን ቀጥሮ ከሚያሰራው ተቋም ጋር ነው ሃላፊነቱን ወስዶ ደብዳቤ ጽፎ ቆጣሪ ይግባ የሚለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው።

በስርቆት ቆጣሪ በማሰናከል ኤሌክትሪክ ሲጠቀሙ ሲገኝ የመጀመሪያው እርምጃ አገልግሎት ተቋርጦ መንግስት ያጣውን ገንዘብ ታስቦ ክፈሉ ብሎ ማሳወቅ ነው ነዋሪዎች እኛን አይመለከትንም እያሉ ነው ነገር ግን እየተጠቀሙ ነው አይ ቤቶች ልማት እኔን አይመለከተኝም ኮንትራክተሩን ነው ካለም ሃላፊነት መውሰድ አለበት " ብለዋል።


አቶ ብርሃኑ ነዋሪዎቹ ቆጣሪው እንዳይቆጥር በማሰናከል ካርድ መሙላት ካቆሙ ጀምሮ በሦስት ቆጣሪዎች የተጠራቀመው እዳ ቅጣትን ጨምሮ 480,538 ብር መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንን ያህል መጠን ኤሌክትሪክ ሃይል የተጠቀሙት ተብለው ለቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተላከ ደብዳቤ የተገለጹት የጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ብሎክ 734 ፣ 735 ፣ 750 እና 751 ነዋሪዎች ሲሆኑ ነገር ግን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት በኮርፖሬሽኑ በኩል በመሆኑ የተጠቀሰውን ክፍያ እንዲፈጽም አገልግሎቱ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን በተደጋጋሚ መጠየቁን ነገር ግን እስካሁን ክፍያው አለመፈጸሙን አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።

ነዋሪዎች ሃይል ከቆጣሪው ጠልፈው አለመጠቀማቸውን እና ቆጣሪዎቹ መንገድ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ምክንያት ነዋሪ ያልሆኑ አካላት መስመሩን እንደሚጠቀሙ ይገልጻሉ ታውቁታላቹ ወይ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄ ዳይሬክተሩ ምላሽ ሰጥተዋል።

" በእኛ በኩል እንደዚህ አይነት ጥቆማ አልደረሰንም ይህንን ቆጣሪ ካስገባን በኋላ በየወሩ ለንባብ ስንመጣ እንዲሁም በእቅድ ምልከታ እናደርጋለን የተጠቀስነውን ችግር ያገኘነው ለምልከታ ስንመጣ ነው። ይሄንን ጥቆማ እንመለከተዋለን በቦታው ስንሄድ ግን የተባለውን ጉዳይ አልተመለከትንም " ብለዋል።

ቆጣሪዎቹ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ለግንባታ አላማ ነበር የተቀመጡት ግንባታው ከተጠናቀቀ ቆይቷል ለምን አልተነሱም ስንል ላነሳነው ጥያቄም።

" ቤቶች ልማት አገልግሎቱን ጨርሰናል ቆጣሪው ይነሳልን አገልግሎቱን አንጠቀመውም ብለው ደብዳቤ መጻፍ አለባቸው ውል አለን ዝም ብለን ቆጣሪ ማንሳት አይቻልም ይግባልን ተብሎ በደብዳቤ እንደተጠየቀው ሁሉ ይነሳልን ብለው ሲጠይቁ ብቻ ነው የሚነሳው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ዳይሬክተሩ ነዋሪዎች የተቋረጠው ሃይል ተመልሶ እንዲቀጠል ጉቦ ክፈሉ ያለን ባለሞያ አለ ሲሉ ላነሱት ቅሬታም " ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን ምላሽ የሚያካትት ይሆናል።

በተጨማሪም ነዋሪዎች ከተጠቀሱት ቆጣሪዎች ላይ ሃይል መቀጠላቸውን እና አለመቀጠላቸውን እንዲሁም ሌሎችም ነዋሪዎች ያቀረቧቸውን ቅሬታዎች በሚመለከት በቦታው ተገኝቶ ምልከታ ማድረግ እንደሚቻል የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቦታው በመገኘት ቅሬታውን በማጣራት የሚያሳውቅ መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94109
Create:
Last Update:

" ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ብሎክ 734 እና 735 የጋራ መኖሪያ መንደር የሚኖሩ ነዋሪዎች ከቆጣሪ እዳ ጋር በተገናኘ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ዝርዝር ምላሽ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

" ነዋሪዎቹ ሃይል የተቋረጠባቸው በየብሎኩ የገባላቸውን ቆጣሪዎች ትተው በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ለኮንስትራክሽን ሥራ የገባውን ቆጣሪ እንዳይቆጥር አድርገው ሲጠቀሙ በእኛ ኢንስፔክሽን ቲም (የምልከታ ቡድን) በ15/04/17 ዓ/ም በተረገ ምልከታ ተደርሶባቸው ነው።

በእኛ አሰራር መሰረት ደግሞ ቆጣሪን እንዳይቆጥር አድርጎ ሲጠቀም የተገኘ ካለ አገልግሎቱን በማቋረጥ ሂሳቡ ይሰላል በድጋሚ ሃይል ለማግኘት ያንን ሂሳብ መክፈል አለበት።

በዚህ ምክንያት ሃይል ተቋርጧል ከተቋረጠ በኋላ ሲጠቀሙ የነበሩትን ሂሳብ አስልተን በደብዳቤ ክፈሉ ብለን አሳውቀናቸዋል።

በእነሱ ስም ቆጣሪው ስለሌለ በቤቶች ልማት ጽ/ቤት ስም አሳውቀናቸዋል በተደጋጋሚ ለመክፈል ፈቃደኛ አልነበሩም ኤሌክትሪኩ ተቋርጦ ነው ያለው።

ቆጣሪው ቢሉ የወጣው በኮንትራክተሩ ሳይሆን በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛ የምናውቀው በኮንትራክተር የገባ ቆጣሪ የለም ውላችንም ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ነው ኮንትራክተሩን አናውቀውም።

አንድን ኮንትራክተር ሊቀጥረው የሚችለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው እኛም ውል የሚኖረን ከኮንትራክተሩ ጋር ሳይሆን ኮንትራክተሩን ቀጥሮ ከሚያሰራው ተቋም ጋር ነው ሃላፊነቱን ወስዶ ደብዳቤ ጽፎ ቆጣሪ ይግባ የሚለው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው።

በስርቆት ቆጣሪ በማሰናከል ኤሌክትሪክ ሲጠቀሙ ሲገኝ የመጀመሪያው እርምጃ አገልግሎት ተቋርጦ መንግስት ያጣውን ገንዘብ ታስቦ ክፈሉ ብሎ ማሳወቅ ነው ነዋሪዎች እኛን አይመለከትንም እያሉ ነው ነገር ግን እየተጠቀሙ ነው አይ ቤቶች ልማት እኔን አይመለከተኝም ኮንትራክተሩን ነው ካለም ሃላፊነት መውሰድ አለበት " ብለዋል።


አቶ ብርሃኑ ነዋሪዎቹ ቆጣሪው እንዳይቆጥር በማሰናከል ካርድ መሙላት ካቆሙ ጀምሮ በሦስት ቆጣሪዎች የተጠራቀመው እዳ ቅጣትን ጨምሮ 480,538 ብር መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንን ያህል መጠን ኤሌክትሪክ ሃይል የተጠቀሙት ተብለው ለቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተላከ ደብዳቤ የተገለጹት የጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ብሎክ 734 ፣ 735 ፣ 750 እና 751 ነዋሪዎች ሲሆኑ ነገር ግን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት በኮርፖሬሽኑ በኩል በመሆኑ የተጠቀሰውን ክፍያ እንዲፈጽም አገልግሎቱ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን በተደጋጋሚ መጠየቁን ነገር ግን እስካሁን ክፍያው አለመፈጸሙን አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።

ነዋሪዎች ሃይል ከቆጣሪው ጠልፈው አለመጠቀማቸውን እና ቆጣሪዎቹ መንገድ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ምክንያት ነዋሪ ያልሆኑ አካላት መስመሩን እንደሚጠቀሙ ይገልጻሉ ታውቁታላቹ ወይ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄ ዳይሬክተሩ ምላሽ ሰጥተዋል።

" በእኛ በኩል እንደዚህ አይነት ጥቆማ አልደረሰንም ይህንን ቆጣሪ ካስገባን በኋላ በየወሩ ለንባብ ስንመጣ እንዲሁም በእቅድ ምልከታ እናደርጋለን የተጠቀስነውን ችግር ያገኘነው ለምልከታ ስንመጣ ነው። ይሄንን ጥቆማ እንመለከተዋለን በቦታው ስንሄድ ግን የተባለውን ጉዳይ አልተመለከትንም " ብለዋል።

ቆጣሪዎቹ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ለግንባታ አላማ ነበር የተቀመጡት ግንባታው ከተጠናቀቀ ቆይቷል ለምን አልተነሱም ስንል ላነሳነው ጥያቄም።

" ቤቶች ልማት አገልግሎቱን ጨርሰናል ቆጣሪው ይነሳልን አገልግሎቱን አንጠቀመውም ብለው ደብዳቤ መጻፍ አለባቸው ውል አለን ዝም ብለን ቆጣሪ ማንሳት አይቻልም ይግባልን ተብሎ በደብዳቤ እንደተጠየቀው ሁሉ ይነሳልን ብለው ሲጠይቁ ብቻ ነው የሚነሳው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ዳይሬክተሩ ነዋሪዎች የተቋረጠው ሃይል ተመልሶ እንዲቀጠል ጉቦ ክፈሉ ያለን ባለሞያ አለ ሲሉ ላነሱት ቅሬታም " ከክፍያ ለመሸሽ የተቋሙን ገጽታ ማበላሸት አይቻልም በህግ እንጠይቃለን ፣ ከፖሊስ እና ጸረ ሙስና ጋር በመሆን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንን ምላሽ የሚያካትት ይሆናል።

በተጨማሪም ነዋሪዎች ከተጠቀሱት ቆጣሪዎች ላይ ሃይል መቀጠላቸውን እና አለመቀጠላቸውን እንዲሁም ሌሎችም ነዋሪዎች ያቀረቧቸውን ቅሬታዎች በሚመለከት በቦታው ተገኝቶ ምልከታ ማድረግ እንደሚቻል የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቦታው በመገኘት ቅሬታውን በማጣራት የሚያሳውቅ መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94109

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Pavel Durov, a billionaire who embraces an all-black wardrobe and is often compared to the character Neo from "the Matrix," funds Telegram through his personal wealth and debt financing. And despite being one of the world's most popular tech companies, Telegram reportedly has only about 30 employees who defer to Durov for most major decisions about the platform. "Your messages about the movement of the enemy through the official chatbot … bring new trophies every day," the government agency tweeted. Ukrainian forces have since put up a strong resistance to the Russian troops amid the war that has left hundreds of Ukrainian civilians, including children, dead, according to the United Nations. Ukrainian and international officials have accused Russia of targeting civilian populations with shelling and bombardments. That hurt tech stocks. For the past few weeks, the 10-year yield has traded between 1.72% and 2%, as traders moved into the bond for safety when Russia headlines were ugly—and out of it when headlines improved. Now, the yield is touching its pandemic-era high. If the yield breaks above that level, that could signal that it’s on a sustainable path higher. Higher long-dated bond yields make future profits less valuable—and many tech companies are valued on the basis of profits forecast for many years in the future. In addition, Telegram's architecture limits the ability to slow the spread of false information: the lack of a central public feed, and the fact that comments are easily disabled in channels, reduce the space for public pushback.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American