Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የ11 ዓመት እስር ተፈርዶባቸዋል !

ኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ ከግብፅ ጉቦ ሲበሉ የነበሩት ሴናተር ቦብ ሜንዴዝ የ11 ዓመታት እስር ተፈረደባቸው።

" የግብጽን ጥቅም ለማስከበር ጉቦ ተቀብለዋል " የተባሉት አሜሪካዊው ሴናተር ቦብ ሜንዴዝ የ11 ዓመት እስር ተፈርዶባቸዋል።

ባለፉት 40 ዓመታት በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ የነበሩት ቦብ ሜነንዴዝ ለዓመታት የሀገሪቱ ውጭ ግንኙነት ስራዎች ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰው ነበሩ፡፡

ሜኔንዴዝ ዲሞክራት ፓርቲን ወክለው የአሜሪካ ህግ አውጪ ምክር ቤት ውስጥ ሰርተዋል።

በፈረንጆቹ 2020 ላይ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ በንቃት እንዲሳተፉ የተደረጉ ሲሆን ከፍተኛ ጫና ሲያደርጉ ነበር።

ፖለቲከኛው ይህን ያደረጉት ከግብጽ ባለስልጣናት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ጉቦ ከተቀበሉ በኋላ ነበር፡፡

የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መሪዎች በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሶስትዮሽ ውይይት በማድረግ ላይ የነበሩ ሲሆን የወቅቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ ውይይት ወደ ዋሸንግተን እንዲመጣ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡

በዋሸንግተን በተደረጉት ተከታታይ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ ኢትዮጵያ በጫና ወደ ስምምነት እንድትመጣ ግፊት ሲደረግ እንደነበር እና ኢትዮጵያ ስምምነቱን " አልፈርምም " በሚል አቋም መጽናቷ የሚታወቅ ነው።

በወቅቱም የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ አውጥቶ ነበር፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ፖለቲከኛው ከግብጽ እና ኳታር ኩባንያዎች ጋር ያልተገባ ጥቅም ትስስር በመፍጠር 150 ሺህ ዶላር የሚያወጣ ወርቅ እና ከ450 ሺህ ዶላር በላይ ገንዘብ ተከፍሏቸዋል።

የሀገሪቱ ፍትህ ተቋማት ባደረጉት ምርመራ ሜኔንዴዝ በጉቦ መቀበል፣ በፍትህ ማዛባት እና ሌሎችም ወንጀሎች ክስ ተመስርቶባቸው በክርክር ላይ ቆይተዋል፡፡

የተመሰረተባቸውን ክስ አምነዋል የተባለ ሲሆን እድሜያቸውን፣ አስቀድሞ አስተዳድራዊ ቅጣቶች እንደተላለፈባቸው እና ሌሎች ምክንያቶችን ታሳቢ አድርጎ ቅጣቱን እንዲቀንስላቸው በጠበቃቸው በኩል ጠይቀዋል።

የሀገሪቱ አቃቢ ህግ በቦብ ሜኔንዴዝ ላይ የ15 ዓመት እስር እንዲተላለፍባቸው ፍርድ ቤቱን የጠየቁ ሲሆን ፍርድ ቤቱም በሴናተሩ ላይ በ11 ዓመት እስር እንዲቀጡ ወስኗል ተብሏል።

መረጃውን ሲኤንኤንን (CNN) ዋቢ በማድረግ ያስነበበው አል አይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94134
Create:
Last Update:

የ11 ዓመት እስር ተፈርዶባቸዋል !

ኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ ከግብፅ ጉቦ ሲበሉ የነበሩት ሴናተር ቦብ ሜንዴዝ የ11 ዓመታት እስር ተፈረደባቸው።

" የግብጽን ጥቅም ለማስከበር ጉቦ ተቀብለዋል " የተባሉት አሜሪካዊው ሴናተር ቦብ ሜንዴዝ የ11 ዓመት እስር ተፈርዶባቸዋል።

ባለፉት 40 ዓመታት በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ የነበሩት ቦብ ሜነንዴዝ ለዓመታት የሀገሪቱ ውጭ ግንኙነት ስራዎች ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰው ነበሩ፡፡

ሜኔንዴዝ ዲሞክራት ፓርቲን ወክለው የአሜሪካ ህግ አውጪ ምክር ቤት ውስጥ ሰርተዋል።

በፈረንጆቹ 2020 ላይ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ በንቃት እንዲሳተፉ የተደረጉ ሲሆን ከፍተኛ ጫና ሲያደርጉ ነበር።

ፖለቲከኛው ይህን ያደረጉት ከግብጽ ባለስልጣናት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ጉቦ ከተቀበሉ በኋላ ነበር፡፡

የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መሪዎች በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሶስትዮሽ ውይይት በማድረግ ላይ የነበሩ ሲሆን የወቅቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ ውይይት ወደ ዋሸንግተን እንዲመጣ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡

በዋሸንግተን በተደረጉት ተከታታይ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ ኢትዮጵያ በጫና ወደ ስምምነት እንድትመጣ ግፊት ሲደረግ እንደነበር እና ኢትዮጵያ ስምምነቱን " አልፈርምም " በሚል አቋም መጽናቷ የሚታወቅ ነው።

በወቅቱም የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ አውጥቶ ነበር፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ፖለቲከኛው ከግብጽ እና ኳታር ኩባንያዎች ጋር ያልተገባ ጥቅም ትስስር በመፍጠር 150 ሺህ ዶላር የሚያወጣ ወርቅ እና ከ450 ሺህ ዶላር በላይ ገንዘብ ተከፍሏቸዋል።

የሀገሪቱ ፍትህ ተቋማት ባደረጉት ምርመራ ሜኔንዴዝ በጉቦ መቀበል፣ በፍትህ ማዛባት እና ሌሎችም ወንጀሎች ክስ ተመስርቶባቸው በክርክር ላይ ቆይተዋል፡፡

የተመሰረተባቸውን ክስ አምነዋል የተባለ ሲሆን እድሜያቸውን፣ አስቀድሞ አስተዳድራዊ ቅጣቶች እንደተላለፈባቸው እና ሌሎች ምክንያቶችን ታሳቢ አድርጎ ቅጣቱን እንዲቀንስላቸው በጠበቃቸው በኩል ጠይቀዋል።

የሀገሪቱ አቃቢ ህግ በቦብ ሜኔንዴዝ ላይ የ15 ዓመት እስር እንዲተላለፍባቸው ፍርድ ቤቱን የጠየቁ ሲሆን ፍርድ ቤቱም በሴናተሩ ላይ በ11 ዓመት እስር እንዲቀጡ ወስኗል ተብሏል።

መረጃውን ሲኤንኤንን (CNN) ዋቢ በማድረግ ያስነበበው አል አይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94134

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Such instructions could actually endanger people — citizens receive air strike warnings via smartphone alerts. Overall, extreme levels of fear in the market seems to have morphed into something more resembling concern. For example, the Cboe Volatility Index fell from its 2022 peak of 36, which it hit Monday, to around 30 on Friday, a sign of easing tensions. Meanwhile, while the price of WTI crude oil slipped from Sunday’s multiyear high $130 of barrel to $109 a pop. Markets have been expecting heavy restrictions on Russian oil, some of which the U.S. has already imposed, and that would reduce the global supply and bring about even more burdensome inflation. At this point, however, Durov had already been working on Telegram with his brother, and further planned a mobile-first social network with an explicit focus on anti-censorship. Later in April, he told TechCrunch that he had left Russia and had “no plans to go back,” saying that the nation was currently “incompatible with internet business at the moment.” He added later that he was looking for a country that matched his libertarian ideals to base his next startup. But because group chats and the channel features are not end-to-end encrypted, Galperin said user privacy is potentially under threat. Apparently upbeat developments in Russia's discussions with Ukraine helped at least temporarily send investors back into risk assets. Russian President Vladimir Putin said during a meeting with his Belarusian counterpart Alexander Lukashenko that there were "certain positive developments" occurring in the talks with Ukraine, according to a transcript of their meeting. Putin added that discussions were happening "almost on a daily basis."
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American