Telegram Group & Telegram Channel
የIMF ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ምን አሉ ?

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።

በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።

ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።

ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።

የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94378
Create:
Last Update:

የIMF ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ምን አሉ ?

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።

በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።

ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።

ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።

የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94378

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The Security Service of Ukraine said in a tweet that it was able to effectively target Russian convoys near Kyiv because of messages sent to an official Telegram bot account called "STOP Russian War." Lastly, the web previews of t.me links have been given a new look, adding chat backgrounds and design elements from the fully-features Telegram Web client. Also in the latest update is the ability for users to create a unique @username from the Settings page, providing others with an easy way to contact them via Search or their t.me/username link without sharing their phone number. The message was not authentic, with the real Zelenskiy soon denying the claim on his official Telegram channel, but the incident highlighted a major problem: disinformation quickly spreads unchecked on the encrypted app. In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American