የIMF ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ምን አሉ ?
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።
በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።
የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
ምን አሉ ?
ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።
" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።
" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።
ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።
ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።
የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።
@tikvahethiopia
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።
በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።
የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
ምን አሉ ?
ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።
" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።
" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።
ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።
ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።
የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።
@tikvahethiopia
group-telegram.com/tikvahethiopia/94378
Create:
Last Update:
Last Update:
የIMF ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ምን አሉ ?
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።
በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።
የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
ምን አሉ ?
ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።
" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።
" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።
ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።
ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።
የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።
@tikvahethiopia
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።
በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።
የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
ምን አሉ ?
ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።
" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።
" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።
ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።
ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።
ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።
የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA
Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94378