Telegram Group & Telegram Channel
የIMF ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ምን አሉ ?

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።

በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።

ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።

ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።

የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94378
Create:
Last Update:

የIMF ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ምን አሉ ?

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ የስራ ቆይታ አድርገዋል።

በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

ዳይሬክተሯ ፤ " የኢትዮጵያ ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያውያን ለትዕግስት እንዲያሳዩ እና ከመንግስት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረቶች ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ " የሪፎርሙን ግቦች ለማሳካት የአንድነት አስፈላጊ ነው " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

" ኢትዮጵያ የተቀበለችው ሪፎርም ከባድ እና ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም እጅግ ትልቅ ውጤት ያስገኛል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪዬን አቀርባለሁ " ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ " ህብረተሰቡ ከሪፎርሙ ጀርባ በመሰባሰብ በአንድነት ድጋፍ ማድረግ አለበት " ብለዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ ኢኮኖሚውን የበለጠ አጥጋቢና ብቁ ለማድረግ ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ " ብለው " እባካችሁ መንግሥት ሥራውን እንዲያጠናቅቅ ድጋፍ አድርጉ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

የዋጋ ንረትን ለመፍታት የሚሰራው ስራ ውስብስብ መሆኑን ያልሸሸጉት ዳይሬክተራ " የዋጋ ንረትን ወደ ታች ለማውረድ ጠንካራ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች፣ የኢኮኖሚውን የማምረት አቅም ማስፋት፣ የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግ እና የግሉ ሴክተርን ማብቃት ይጠይቃል " ብለዋል።

ሌላው ያነሱት ጉዳይ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የዕዳ መልሶ ማደራጀት ድርድር በተመለከተ ነው።

ጆርጂዬቫ ፤ " የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል ፤ ከኢትዮጵያ አበዳሪዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ይህ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የIMF ፕሮግራም አካል ሆነውን የታክስ እርምጃዎችን በተመለከተም ፤ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለብሄራዊ በጀቱ ድጋፍ ለማድረግ ወሳኝ የሆኑ የታክስ አቅሞችን መለየታቸውን ጠቁመዋል።

ጆርጂዬቫ ፥ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ከIMF የመጀመሪያ ትንበያዎች መብለጡን ማብራራታቸውን ዘሪፖርተር አስነብቧል።

የማኔጂንግ ዳይሬክተራ ንግግር ተከትሎ " መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚገናኝ አይደለም " የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡም ተመልክተናል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94378

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

'Wild West' This provided opportunity to their linked entities to offload their shares at higher prices and make significant profits at the cost of unsuspecting retail investors. Unlike Silicon Valley giants such as Facebook and Twitter, which run very public anti-disinformation programs, Brooking said: "Telegram is famously lax or absent in its content moderation policy." On February 27th, Durov posted that Channels were becoming a source of unverified information and that the company lacks the ability to check on their veracity. He urged users to be mistrustful of the things shared on Channels, and initially threatened to block the feature in the countries involved for the length of the war, saying that he didn’t want Telegram to be used to aggravate conflict or incite ethnic hatred. He did, however, walk back this plan when it became clear that they had also become a vital communications tool for Ukrainian officials and citizens to help coordinate their resistance and evacuations. As a result, the pandemic saw many newcomers to Telegram, including prominent anti-vaccine activists who used the app's hands-off approach to share false information on shots, a study from the Institute for Strategic Dialogue shows.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American