TIKVAH-ETHIOPIA
አሜሪካ በቀጥታ ወደ ጦርነቱ ትገባ ይሁን ? እስራኤል በኢራን ላይ እያካሄደችው ባለው ጥቃት ውስጥ አሜሪካ ስለምትሳተፍበት ሁኔታ ለመወያየት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሐውስ ውስጥ አስቸኳይ ስብሰባ ከከፍተኛ ባለሥልጣኖቻቸው ጋር አድርገዋል። አንድ ሰዓት ከ20 ደቂቃ በቆየው ስብሰባ ላይ ዋነኛ አጀንዳ የነበረው እስራኤል በኢራን የኒውክሌር ማዕከላት ላይ እየፈጸመችው ባለው ጥቃት ውስጥ አሜሪካ መሳትፍ እንዳለባት…
#Update
እስራኤል በኢራን ላይ በፈጸመችው ጥቃት እስከ እሁድ ምሽት ድረስ 224 ሰዎች መገደላቸውን 1 ሺህ 277 መጎዳታቸውን ኢራን አስታውቃለች።
እስራኤል በበኩሏ በኢራን ጥቃት 20 ሰዎች እንደተገደሉባት ገልጻለች።
ተባብሶ በቀጠለው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ምክንያት ነዋሪዎች ከአካባቢያቸው እንዲወጡ በሁለቱም በኩል መልዕክት እየተላለፈ ነው።
ኢራን የእስራኤሏ ሃይፋ ከተማ በተወሰነው ክፍል ያሉ ነዋሪዎች ለህይወታቸው አደጋ ስለሚኖር አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
እስራኤልም ነዋሪዎች ከተለያዩ የቴህራን ክፍሎች ለቀው እንዲወጡ እያስጠነቀቅች ነው። በዚህም ሰዎች በቻሉት አቅም ወደ አጎራባች ከተማ እየወጡ እንዳለ ተነግሯል።
መረጃው ቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
እስራኤል በኢራን ላይ በፈጸመችው ጥቃት እስከ እሁድ ምሽት ድረስ 224 ሰዎች መገደላቸውን 1 ሺህ 277 መጎዳታቸውን ኢራን አስታውቃለች።
እስራኤል በበኩሏ በኢራን ጥቃት 20 ሰዎች እንደተገደሉባት ገልጻለች።
ተባብሶ በቀጠለው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ምክንያት ነዋሪዎች ከአካባቢያቸው እንዲወጡ በሁለቱም በኩል መልዕክት እየተላለፈ ነው።
ኢራን የእስራኤሏ ሃይፋ ከተማ በተወሰነው ክፍል ያሉ ነዋሪዎች ለህይወታቸው አደጋ ስለሚኖር አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
እስራኤልም ነዋሪዎች ከተለያዩ የቴህራን ክፍሎች ለቀው እንዲወጡ እያስጠነቀቅች ነው። በዚህም ሰዎች በቻሉት አቅም ወደ አጎራባች ከተማ እየወጡ እንዳለ ተነግሯል።
መረጃው ቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኮሌጆች ወደ ጠቅላላ ትምህርት ለመግባት ዝግጅት ላይ ናቸው " -አስተያየት ሰጪ የዘርፉ ተዋናዮች ➡️ " አብዛኞቹ ኮሌጆች በራሳቸው መንገድ መክሰማቸው አይቀርም " አብዛኞቹ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መቀጠል ስላልቻሉ ትምህርት ቤት ከፍተው ለመስራት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ስማችን አይጠቀስ ያሉና በዘርፉ የተሰማሩ ተዋናዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ፣…
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት " ስጋት ላይ ጥሎናል " ያሉት አዲስ መመሪያ ምን ይዟል ?
የኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አሰራር ስርዓት ለማስያዝ በሚል ዳግም ምዝገባ በማካሔድ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም በሰጣቸው መግለጫዎች አስታውቋል፡፡
በዚህ ሒደት 85 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዲሱ መስፈርት መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ እንደሚዘጉም ተገልፆ ነበር፡፡
በመመሪያው መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ያመለከቱት 287 ተቋማትም፣ አብዛኞቹ መስፈርቱን እንደማያሟሉ እየተገለፀ ይገኛል፡፡ ሆኖም እስካሁን ድረስ በአዲሱ መመሪያ ተመዝነው የትኞቹ እንደሚቀጥሉና እንደማይቀጥሉ አልተገለፀም፡፡
የዘርፉ ተዋናዮች በበኩላቸው፣ “ የዳግም ምዝገባ መመሪያውና የያዛቸው መመዘኛዎች የሚተገበሩና የሚያሰሩ አይደሉም፣ በዚህ መመሪያ ተመዝነው የሚቀጥሉት ተቋማት ጥቂቶች ብቻ ነው የሚሆኑት፣ አብዛኞቹም መዘጋታቸው አይቀሬ ነው ” ይላሉ፡፡
ለመሆኑ በዳግመ ምዝገባ መመሪያው ላይ የተቀመጡት ዋና ዋናዎቹ መመዘኛዎች ምን ይላሉ፣ የትምህርት ተቋማቱን ስጋት ላይ የጣሉትስ እንዴት ነው በማለት የጠየቅናቸው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች የሚከተለውን አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል፡፡
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች ፦
“ በመመሪያ ላይ የተቀመጠውና የግል ተቋማትን አቅም ያላገናዘበው አንደኛው መመዘኛ የመማሪያ ህንፃን ይመለከታል፡፡ አንድ ተቋም አምስትና ከዚያ በላይ ፕሮግራሞችን የሚሰጥ ከሆነ አንድ ሙሉ ህንፃ ብቻውን መያዝ አለበት ይላል፡፡ አብዛኞቹ ኮሌጆች የሆነ አንድ ህንፃ ላይ የተወሰኑ ፎቆችን ተከራይተው የሚሰሩ ናቸው፡፡ ይህን ፎቅ ብቻችሁን ያዙት ሲባሉ አቅሙ የላቸውም፡፡
መንግስት እንዲህ አይነት መመሪያ ሲያወጣ በሊዝ መሬት እንድናገኝና የራሳችንን ህንፃ እንድንገነባ እንኳ ሁኔታዎችን አያመቻችም፡፡ ለትምህርት ዘርፍ የተመቻቹ ዕድሎች የሉም፡፡ ለምሳሌ ከውጭ የሚገቡ ለትምህርት አስፈላጊ የሆኑ መፃህፍት፣ ኮምፒዩተሮችና ቁሳቁሶች ከቀረጥ ነፃ መግባት ነበረባቸው፣ ይህ አልተደረገም፡፡
ሁለተኛው መስፈርት የሰው ሀይልን የሚመለከት ነው፡፡ አስተማሪዎችና የቢሮ ሰራተኞች የዶክትሬት ዲግሪ ያላቸው ይሁኑ ይላል፡፡
በእኛ ሀገር ያሉ ዶክተሮች ጥቂቶች ናቸው፡፡ ብዙዎቹ በመንግስት ድጋፍ በውጭ ሀገራት የተማሩ ናቸው፡፡ ቀደም ሲል የግል ኮሌጆች ከመንግስት ተቋማት መምህራንን እየተጋሩ ሲያስተምሩ ነበር፡፡
ይህም ጥያቄ ሲያስነሳ የመንግስት አካላት ባሉበት ውይይት ሲደረግበት ነበር፡፡ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን በሁለቱም ቦታዎች እንዲያስተምሩ/ዱዋል ኢምፕሎይመንት/ እንዲፈቀድላቸው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በአንድ ፕሮግራም ውስጥ ብዙ ፒኤችዲ የያዙ መምህራን አሉ፣ ትርፍ ሰዓት አላቸው፣ ጫና አይበዛባቸውም፡፡ ስለዚህ በግል ኮሌጆችም ያስተምሩ የሚል ነበር ውይይቱ፡፡
ይህ ውይይት መጨረሻው ላይ ከደረሰ በኋላ ወደኋላ ተመለሰ፡፡ ምክንያቱ አይታወቅም፡፡ በዚህ ምክንያት ዶክተር መምህራንን አናገኝም፡፡
ከላይ ካለው ከዲኑ ጀምሮ እስከ ቢሮ ሰራተኞች ድረስ ዶክተሮች ይሁኑ ይላል መመሪያው፡፡ እስከ ማስተርስ ድረስ የሚያስተምሩት መምህራን ዶክተሮች ቢሆኑ እንስማማለን፣ ሁሉም የተቋሙ ሰራተኞች ዶክተሮች ይሁኑ ማለት ግን አያስኬድም፡፡ በቂ የሰው ሀይል የለም ገበያው ውስጥ፡፡
ሶስተኛው ነጥብ፣ ከመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ የተቀመጠው ነው፡፡ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና፣ በትንሹ 25 ከመቶ ተማሪዎችን ያላሳለፈ ተቋም መዘጋት እንዳለበት ይገልፃል መመዘኛው፡፡ ይህን መስፈርት ልተግብረው ስትል ችግር ያመጣል፡፡
ለምሳሌ ፦ በ2016 ዓ.ም የነበረውን የመውጫ ፈተና ብነግርህ፣ 202 ተቋማት ተፈታኝ ተማሪዎችን አቅርበው፣ 25 ተቋማት አንድም ተማሪ አላሳለፉም፡፡ ከ25 በመቶ በላይ ያሳለፉትም 27 ናቸው፡፡ ከዚህ ውጭ ያሉት ይዘጋሉ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ መመዘኛ የሚደረስበት አይደለም፡፡ ይህ በሒደት ነው እንጂ በአንዴ ይተግበር መባል የለበትም፡፡
አራተኛው አስቸጋሪ መመዘኛ የምንለው የስፖርት ማዘውተሪያ በሚል የተቀመጠው ነው፡፡ ይህም በተወሰነ ደረጃ የሚያስኬድ አይደለም፡፡
አዲስ ተቋም ከሆነ ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን ብር በዝግ አካውንት/የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥ አለበት የሚልም አለ፡፡ ይህ በጣም ከባድ ነው፡፡ አዳዲስ ተቋማት ቁሳቁስ ነው ሊያሟሉበት የሚገባው ይህን ገንዘብ፡፡
ገበያው ላይ ያለው ተማሪም ዝቅተኛ ነው፡፡ በመመሪያው ላይ ያሉትን መመዘኛዎች ሁሉ አሟልተው ዳግም ተመዘገቡ እንኳን ብንል፣ ተቋማቱ ተማሪ የማያገኙ ከሆነ መዘጋታቸው አይቀርም፡፡ ስለዚህ ሞክሩት፣ ስርዓቱ በራሱ ከገበያ ያስወጣችኋል ነው እያሉን ያሉት በአጭሩ፡፡ ይህ ሁሉ ተደምሮ ሁኔታውን ከባድ ያደርገዋል፡፡
በአዲሱ መመሪያ ላይ ሀሳብ ሰጥተናል፡፡ በማህበራችን በኩል መሻሻል አለበት የምንለውን ጉዳይ በሰነድ አዘጋጅተን አስገብተናል፣ አንድም ማስተካከያ አልተደረገም፣ ጥያቄያችን መልስ አላገኘም፡፡
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ያዘጋጀው መድረክም፣ ይህን መመሪያ እወቁት የሚል እንጂ፣ በመመሪያው ላይ እንወያይ የሚል አልነበረም፡፡ የእኛን አስተያየት አካትቱ በሚል ብዙ ጭቅጭቅ ነበር፣ ሰሚ አላገኘንም፡፡ መጀመሪያ ያስተዋወቁን መመሪያ ፀድቆ ነው ወደ ትግበራ የተገባው፡፡
ጥያቄያችን ይህ እርምጃ በሒደት መወሰድ/መተግበር ነበረበት የሚል ነው፡፡ በአንዴ መደረግ የለበትም፡፡ በአንድ ቀን ሁሉንም ነገር ከመሰረቱ እንቀይረው ማለት አያስኬድም፣ አሉታዊ ተፅዕኖም ያስከትላል፡፡ ተማሪዎች ከአንድ ተቋም ወደ ሌላ ተቋም እየተዛወሩ በመንገላታት ላይ ናቸው፡፡ በርካታ ሰራተኞቻቸውን የበተኑ ተቋማት አሉ፡፡ የተቋማት አሰራር ስርዓት መያዝ አለበት፣ የትምህርት ጥራትም መረጋገጥ አለበት፣ ግን ደግሞ ይህ መሆን የሚችለው በሒደት ነው፡፡ ይህ መታየት አለበት፡፡ ”
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በዚህ ጉዳይ ዙርያ ምላሽና ማብራሪያ ይዞ ይቀርባል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አሰራር ስርዓት ለማስያዝ በሚል ዳግም ምዝገባ በማካሔድ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም በሰጣቸው መግለጫዎች አስታውቋል፡፡
በዚህ ሒደት 85 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዲሱ መስፈርት መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ እንደሚዘጉም ተገልፆ ነበር፡፡
በመመሪያው መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ያመለከቱት 287 ተቋማትም፣ አብዛኞቹ መስፈርቱን እንደማያሟሉ እየተገለፀ ይገኛል፡፡ ሆኖም እስካሁን ድረስ በአዲሱ መመሪያ ተመዝነው የትኞቹ እንደሚቀጥሉና እንደማይቀጥሉ አልተገለፀም፡፡
የዘርፉ ተዋናዮች በበኩላቸው፣ “ የዳግም ምዝገባ መመሪያውና የያዛቸው መመዘኛዎች የሚተገበሩና የሚያሰሩ አይደሉም፣ በዚህ መመሪያ ተመዝነው የሚቀጥሉት ተቋማት ጥቂቶች ብቻ ነው የሚሆኑት፣ አብዛኞቹም መዘጋታቸው አይቀሬ ነው ” ይላሉ፡፡
ለመሆኑ በዳግመ ምዝገባ መመሪያው ላይ የተቀመጡት ዋና ዋናዎቹ መመዘኛዎች ምን ይላሉ፣ የትምህርት ተቋማቱን ስጋት ላይ የጣሉትስ እንዴት ነው በማለት የጠየቅናቸው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች የሚከተለውን አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል፡፡
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች ፦
“ በመመሪያ ላይ የተቀመጠውና የግል ተቋማትን አቅም ያላገናዘበው አንደኛው መመዘኛ የመማሪያ ህንፃን ይመለከታል፡፡ አንድ ተቋም አምስትና ከዚያ በላይ ፕሮግራሞችን የሚሰጥ ከሆነ አንድ ሙሉ ህንፃ ብቻውን መያዝ አለበት ይላል፡፡ አብዛኞቹ ኮሌጆች የሆነ አንድ ህንፃ ላይ የተወሰኑ ፎቆችን ተከራይተው የሚሰሩ ናቸው፡፡ ይህን ፎቅ ብቻችሁን ያዙት ሲባሉ አቅሙ የላቸውም፡፡
መንግስት እንዲህ አይነት መመሪያ ሲያወጣ በሊዝ መሬት እንድናገኝና የራሳችንን ህንፃ እንድንገነባ እንኳ ሁኔታዎችን አያመቻችም፡፡ ለትምህርት ዘርፍ የተመቻቹ ዕድሎች የሉም፡፡ ለምሳሌ ከውጭ የሚገቡ ለትምህርት አስፈላጊ የሆኑ መፃህፍት፣ ኮምፒዩተሮችና ቁሳቁሶች ከቀረጥ ነፃ መግባት ነበረባቸው፣ ይህ አልተደረገም፡፡
ሁለተኛው መስፈርት የሰው ሀይልን የሚመለከት ነው፡፡ አስተማሪዎችና የቢሮ ሰራተኞች የዶክትሬት ዲግሪ ያላቸው ይሁኑ ይላል፡፡
በእኛ ሀገር ያሉ ዶክተሮች ጥቂቶች ናቸው፡፡ ብዙዎቹ በመንግስት ድጋፍ በውጭ ሀገራት የተማሩ ናቸው፡፡ ቀደም ሲል የግል ኮሌጆች ከመንግስት ተቋማት መምህራንን እየተጋሩ ሲያስተምሩ ነበር፡፡
ይህም ጥያቄ ሲያስነሳ የመንግስት አካላት ባሉበት ውይይት ሲደረግበት ነበር፡፡ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን በሁለቱም ቦታዎች እንዲያስተምሩ/ዱዋል ኢምፕሎይመንት/ እንዲፈቀድላቸው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በአንድ ፕሮግራም ውስጥ ብዙ ፒኤችዲ የያዙ መምህራን አሉ፣ ትርፍ ሰዓት አላቸው፣ ጫና አይበዛባቸውም፡፡ ስለዚህ በግል ኮሌጆችም ያስተምሩ የሚል ነበር ውይይቱ፡፡
ይህ ውይይት መጨረሻው ላይ ከደረሰ በኋላ ወደኋላ ተመለሰ፡፡ ምክንያቱ አይታወቅም፡፡ በዚህ ምክንያት ዶክተር መምህራንን አናገኝም፡፡
ከላይ ካለው ከዲኑ ጀምሮ እስከ ቢሮ ሰራተኞች ድረስ ዶክተሮች ይሁኑ ይላል መመሪያው፡፡ እስከ ማስተርስ ድረስ የሚያስተምሩት መምህራን ዶክተሮች ቢሆኑ እንስማማለን፣ ሁሉም የተቋሙ ሰራተኞች ዶክተሮች ይሁኑ ማለት ግን አያስኬድም፡፡ በቂ የሰው ሀይል የለም ገበያው ውስጥ፡፡
ሶስተኛው ነጥብ፣ ከመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ የተቀመጠው ነው፡፡ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና፣ በትንሹ 25 ከመቶ ተማሪዎችን ያላሳለፈ ተቋም መዘጋት እንዳለበት ይገልፃል መመዘኛው፡፡ ይህን መስፈርት ልተግብረው ስትል ችግር ያመጣል፡፡
ለምሳሌ ፦ በ2016 ዓ.ም የነበረውን የመውጫ ፈተና ብነግርህ፣ 202 ተቋማት ተፈታኝ ተማሪዎችን አቅርበው፣ 25 ተቋማት አንድም ተማሪ አላሳለፉም፡፡ ከ25 በመቶ በላይ ያሳለፉትም 27 ናቸው፡፡ ከዚህ ውጭ ያሉት ይዘጋሉ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ መመዘኛ የሚደረስበት አይደለም፡፡ ይህ በሒደት ነው እንጂ በአንዴ ይተግበር መባል የለበትም፡፡
አራተኛው አስቸጋሪ መመዘኛ የምንለው የስፖርት ማዘውተሪያ በሚል የተቀመጠው ነው፡፡ ይህም በተወሰነ ደረጃ የሚያስኬድ አይደለም፡፡
አዲስ ተቋም ከሆነ ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን ብር በዝግ አካውንት/የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥ አለበት የሚልም አለ፡፡ ይህ በጣም ከባድ ነው፡፡ አዳዲስ ተቋማት ቁሳቁስ ነው ሊያሟሉበት የሚገባው ይህን ገንዘብ፡፡
ገበያው ላይ ያለው ተማሪም ዝቅተኛ ነው፡፡ በመመሪያው ላይ ያሉትን መመዘኛዎች ሁሉ አሟልተው ዳግም ተመዘገቡ እንኳን ብንል፣ ተቋማቱ ተማሪ የማያገኙ ከሆነ መዘጋታቸው አይቀርም፡፡ ስለዚህ ሞክሩት፣ ስርዓቱ በራሱ ከገበያ ያስወጣችኋል ነው እያሉን ያሉት በአጭሩ፡፡ ይህ ሁሉ ተደምሮ ሁኔታውን ከባድ ያደርገዋል፡፡
በአዲሱ መመሪያ ላይ ሀሳብ ሰጥተናል፡፡ በማህበራችን በኩል መሻሻል አለበት የምንለውን ጉዳይ በሰነድ አዘጋጅተን አስገብተናል፣ አንድም ማስተካከያ አልተደረገም፣ ጥያቄያችን መልስ አላገኘም፡፡
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ያዘጋጀው መድረክም፣ ይህን መመሪያ እወቁት የሚል እንጂ፣ በመመሪያው ላይ እንወያይ የሚል አልነበረም፡፡ የእኛን አስተያየት አካትቱ በሚል ብዙ ጭቅጭቅ ነበር፣ ሰሚ አላገኘንም፡፡ መጀመሪያ ያስተዋወቁን መመሪያ ፀድቆ ነው ወደ ትግበራ የተገባው፡፡
ጥያቄያችን ይህ እርምጃ በሒደት መወሰድ/መተግበር ነበረበት የሚል ነው፡፡ በአንዴ መደረግ የለበትም፡፡ በአንድ ቀን ሁሉንም ነገር ከመሰረቱ እንቀይረው ማለት አያስኬድም፣ አሉታዊ ተፅዕኖም ያስከትላል፡፡ ተማሪዎች ከአንድ ተቋም ወደ ሌላ ተቋም እየተዛወሩ በመንገላታት ላይ ናቸው፡፡ በርካታ ሰራተኞቻቸውን የበተኑ ተቋማት አሉ፡፡ የተቋማት አሰራር ስርዓት መያዝ አለበት፣ የትምህርት ጥራትም መረጋገጥ አለበት፣ ግን ደግሞ ይህ መሆን የሚችለው በሒደት ነው፡፡ ይህ መታየት አለበት፡፡ ”
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በዚህ ጉዳይ ዙርያ ምላሽና ማብራሪያ ይዞ ይቀርባል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
#ሴጅ_ማሰልጠኛ_ኢንስቲትዩት
የሁለት ወር የልጆች የክረምት ስልጠና (25% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም)
👉ስልጠናው ዕድሜያቸው ከ 5-18 ዓመት ላሉ ልጆች የሚሰጥ ነው።
👉 ልጆች ፕሮጀክቶች እየሰሩ የሚሰለጥኑበት
👉ስልጠናው ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
የስልጠናዎቹ ዓይነት:
👉 Computer Programming and Website Development
👉 AI and Robotics
👉 Graphic Design, Video Editing and Animation
👉 Art (Film Acting, Writing and Modeling)
👉 Painting, Drawing and Sculpture
👉 Language and Basic Computer
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram
Tiktok
Linkedin
የሁለት ወር የልጆች የክረምት ስልጠና (25% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም)
👉ስልጠናው ዕድሜያቸው ከ 5-18 ዓመት ላሉ ልጆች የሚሰጥ ነው።
👉 ልጆች ፕሮጀክቶች እየሰሩ የሚሰለጥኑበት
👉ስልጠናው ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
የስልጠናዎቹ ዓይነት:
👉 Computer Programming and Website Development
👉 AI and Robotics
👉 Graphic Design, Video Editing and Animation
👉 Art (Film Acting, Writing and Modeling)
👉 Painting, Drawing and Sculpture
👉 Language and Basic Computer
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram
Tiktok
TIKVAH-ETHIOPIA
" በኢ-መደበኛ መንገድ ከሚሰሩት ውጪ 860 የተመዘገቡ የፕላስቲክ አምራች ድርጅቶች አሉ ይህም ጥቅል ካፒታላቸው 58.8 ቢሊዮን ብር ይገመታል " - ፕላስቲክ እና ጎማ አምራቾች ማህበር ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኘ ከ2,000 እስከ 5,000 ብር የሚያስቀጣው " የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ " በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወሳል።…
" ይህንን በተመለከተ ምንም ነገር የለም ፌስታልን እንዲተኩ እንደአማራጭ ይሆናሉ ተብለው የሚነገሩ መሬት ላይ ይወርዳሉ ብለን የማንገምታቸው ነገሮችም አሉ " -የፕላስቲክ እና ጎማ አምራቾች ማህበር
የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ ከመጽደቁ ቀደም ብሎ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተው ነበር።
ሚኒስትሩ ከፕላስቲክ ስናገኝ የነበረውን አገልግሎት በምን አማራጭ ምርቶች ለመተካት ታስቧል ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ።
" በኬሚካል ምርምር ማዕከሎቻችን ያሉ ተመራማሪዎች ፕላስቲክን የሚተኩ አካባቢ ተስማሚ የሆኑ ምርቶችን አግኝተው ሰርተፍኬት ወስደዋል።
ይህንን ምርት ወደ ኢንዱስትሪዎች እያስተዋወቅን ስለሆነ በቀጣይ በስፋት እያመረቱ ህብረተሰቡ የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ መጪው ትውልድ ያልተበከለ አካባቢ እንዲረከብ ማድረግ አስፈላጊ ነው " ማለታቸው ይታወቃል።
ተገኘ የተባለው ፕላስቲክን የሚተካ ምርት በሚመለከት ወደ ኢንዱስትሪዎች የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ፕላስቲክ እና ጎማ አምራቾች ማህበርን ጠይቋል።
የማህበሩ አባል አቶ በረከት ገ/ህይወት " ይህንን በተመለከተ ምንም ነገር የለም ፌስታልን እንዲተኩ እንደአማራጭ ይሆናሉ ተብለው የሚነገሩ መሬት ላይ ይወርዳሉ ብለን የማንገምታቸው ነገሮችም አሉ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ወደ መሬት ይወርዳሉ ብለን አንገምትም ሲሉ ከዘረዘሯቸው ውስጥ አንደኛው " የወረቀት ማሸጊያዎች " ናቸው።
" የወረቀት ማሸጊያዎች ከሚያስወጡት የውጭ ምንዛሬ አንጻር ፣ለሁሉም አይነት ማሸጊያዎች ጥቅም ላይ የሚውሉ ባለመሆናቸው፣ ለእርጥበት እና ለተለያዩ ነገሮች ተጋላጭ በመሆናቸው እንዲሁም እነዚህን ምርቶች በበቂ ሁኔታ የሚያመርት የወረቀት ኢንዱስትሪ በሃገር ውስጥ ባለመኖሩ ይህንን ክፍተት ይሙሉ ቢባል አስቸጋሪ ይሆናል " ብለዋል።
በተጨማሪም " እነዚህ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ገብተው ክፍተቱን ለመሙላትም በጣም በርካታ አመት ያስፈልጋቸዋል" ሲሉ አክለዋል።
አቶ በረከት ገ/ህይወት በዝርዝር ምን አሉ?
" የፌስታል ፋብሪካዎች በቀን ከመቶ ሺ በላይ ያመርታሉ ወረቀት ከባህሪው አንጻር ይህን ያህል በቀን ተመርቶ ፍላጎትን ማሟላት አይችልም ከተጣለም በኋላም መልሶ መጠቀም የማይቻል በመሆኑ የማያቋርጥ የውጭ ምንዛሬ ይጠይቃል።
ወረቀት ሃገር ውስጥ ይመረት ቢባል እንኳን ኢትዮጵያ ያላት የእንጨት ሃብት በቂ አይደለም አንድ ኪሎ ግራም ወረቀት ለማምረት የሚፈልገው አቅም አንድ ኪሎ ግራም ፌስታል ለማምረት ከሚወጣው ጉልበት ጋር ሲነጻጸር አራት እና አምስት እጥፍ ነው።
ገበያ ላይም ሰቀርብ ዋጋው ውድ በመሆኑ ትክክለኛ ምትክ ምርት ነው አንለውም።
በሁለተኛነት እንደ እማራጭ የቀረበው የጨረቅ ወይም Non woven ማሸጊያዎች ናቸው እነዚህም እንደጨርቅ የተሸመኑ የፕላስቲክ ምርቶች ናቸው ውድ ናቸው በሃገራችንም ይህንን የሚያመርት ባለመኖሩ የዋጋ ክፍተት መፍጠሩ አይቀርም።
ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አለኝ የሚለው ነገር ለማን እንደሆነ ያወቅነው ነገር የለም አለም ከተባለ ለእኛ ለአምራቾች ሊቀርብልን ይገባል " ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል አምራቾች በተወሰነ ማስተካከያ ሪፕርፕዝ (Repurpose) በማድረግ በኮቪድ ወቅት የመጠጥ፣ የውሃ እና የአልኮን ፋብሪካዎች ሳኒታይዘር እንዲያመርቱ የተደረገበት አጋጣሚ እንደነበር በመግለጽ የፕላስቲክ ኢንዱስትሪዎችን ተመመሳሳይ ሂደት እንዲከተሉ ይደረጋል ማለታቸው ይታወሳል።
በዚህ ሂደት ላይ ምክክር አላቹ ወይ ? ስንል ሃሳባቸውን የጠየቅናቸው አቶ በረከት " ምክክር የለንም ያንን እና ይሄንን ማነጻጸር ተገቢ አይደለም " ብለዋል።
" የአልኮል እና የኬሚካል ኢንዱስትሪዎችን ለወጥ አድርጎ ሳኒታይዘር እንዲያመርቱ ማድረግ የማሽኖቹን መሰረታዊ ባህሪ መቀየር አያስፈልገውም በእኛ መንገድ ግን ማሽኖቹን repurpose ማድረግ የሚቻልበት እድል የለም የአመራረት ሂደቱ ፕላስቲክ እና ወረቀት አብረው የሚሄዱ ስላልሆኑ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የማህበሩ አባል አቶ በረከት በሰጡት ምክረ ሃሳብም "አዋጁ ጸድቋል በረቂቅ ሂደቱ ላይ የነበሩ ያሳታፊነት ስህተቶች መደገም የለባቸውም ከእኛ ጋር በትክክል ምክክር ያስፈልጋል " ያሉ ሲሆን ኢንዱስትሪ በምንም ሁኔታ በስድስት ወር ውስጥ ስራ አቁም ሊባል አይገባም የሌላ ሃገራት ልምድም ይህንን አያሳይም ሲሉ ተናግረዋል።
" በየትኛውም ሃገር ያልተፈጸመ ተግባር ለምን በእኛ ሃገር ይፈጸማል ? " ሲሉም ጠይቀዋል።
" እነዚህ ኢንዱስትሪዎች በተከራይዋቸው ዌር ሃውስ ውስጥ የሚሰሩ ናቸው ሲከራዩም የ6 ወር እና የ1 አመት ክፍያ ነው የሚፈጽሙት በዚህ ምክንያት ቀድመው በከፈሉት ክፍያ ብቻ ኪሳራ ይደርስባቸዋል " " ሲሉ ገልጸዋል።
" ማሽኖቹም ከጥቅም ውጪ ነው የሚሆኑት ለማጓጓዝም ሰፊ ቦታ እና መሽነሪዎች የሚፈልጉ ናቸው በእነዚህ እና ሌሎች ምክንያቶች የሽግግር ጊዜው ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበ አይደለም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ ከመጽደቁ ቀደም ብሎ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተው ነበር።
ሚኒስትሩ ከፕላስቲክ ስናገኝ የነበረውን አገልግሎት በምን አማራጭ ምርቶች ለመተካት ታስቧል ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ።
" በኬሚካል ምርምር ማዕከሎቻችን ያሉ ተመራማሪዎች ፕላስቲክን የሚተኩ አካባቢ ተስማሚ የሆኑ ምርቶችን አግኝተው ሰርተፍኬት ወስደዋል።
ይህንን ምርት ወደ ኢንዱስትሪዎች እያስተዋወቅን ስለሆነ በቀጣይ በስፋት እያመረቱ ህብረተሰቡ የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ መጪው ትውልድ ያልተበከለ አካባቢ እንዲረከብ ማድረግ አስፈላጊ ነው " ማለታቸው ይታወቃል።
ተገኘ የተባለው ፕላስቲክን የሚተካ ምርት በሚመለከት ወደ ኢንዱስትሪዎች የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ፕላስቲክ እና ጎማ አምራቾች ማህበርን ጠይቋል።
የማህበሩ አባል አቶ በረከት ገ/ህይወት " ይህንን በተመለከተ ምንም ነገር የለም ፌስታልን እንዲተኩ እንደአማራጭ ይሆናሉ ተብለው የሚነገሩ መሬት ላይ ይወርዳሉ ብለን የማንገምታቸው ነገሮችም አሉ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ወደ መሬት ይወርዳሉ ብለን አንገምትም ሲሉ ከዘረዘሯቸው ውስጥ አንደኛው " የወረቀት ማሸጊያዎች " ናቸው።
" የወረቀት ማሸጊያዎች ከሚያስወጡት የውጭ ምንዛሬ አንጻር ፣ለሁሉም አይነት ማሸጊያዎች ጥቅም ላይ የሚውሉ ባለመሆናቸው፣ ለእርጥበት እና ለተለያዩ ነገሮች ተጋላጭ በመሆናቸው እንዲሁም እነዚህን ምርቶች በበቂ ሁኔታ የሚያመርት የወረቀት ኢንዱስትሪ በሃገር ውስጥ ባለመኖሩ ይህንን ክፍተት ይሙሉ ቢባል አስቸጋሪ ይሆናል " ብለዋል።
በተጨማሪም " እነዚህ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ገብተው ክፍተቱን ለመሙላትም በጣም በርካታ አመት ያስፈልጋቸዋል" ሲሉ አክለዋል።
አቶ በረከት ገ/ህይወት በዝርዝር ምን አሉ?
" የፌስታል ፋብሪካዎች በቀን ከመቶ ሺ በላይ ያመርታሉ ወረቀት ከባህሪው አንጻር ይህን ያህል በቀን ተመርቶ ፍላጎትን ማሟላት አይችልም ከተጣለም በኋላም መልሶ መጠቀም የማይቻል በመሆኑ የማያቋርጥ የውጭ ምንዛሬ ይጠይቃል።
ወረቀት ሃገር ውስጥ ይመረት ቢባል እንኳን ኢትዮጵያ ያላት የእንጨት ሃብት በቂ አይደለም አንድ ኪሎ ግራም ወረቀት ለማምረት የሚፈልገው አቅም አንድ ኪሎ ግራም ፌስታል ለማምረት ከሚወጣው ጉልበት ጋር ሲነጻጸር አራት እና አምስት እጥፍ ነው።
ገበያ ላይም ሰቀርብ ዋጋው ውድ በመሆኑ ትክክለኛ ምትክ ምርት ነው አንለውም።
በሁለተኛነት እንደ እማራጭ የቀረበው የጨረቅ ወይም Non woven ማሸጊያዎች ናቸው እነዚህም እንደጨርቅ የተሸመኑ የፕላስቲክ ምርቶች ናቸው ውድ ናቸው በሃገራችንም ይህንን የሚያመርት ባለመኖሩ የዋጋ ክፍተት መፍጠሩ አይቀርም።
ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አለኝ የሚለው ነገር ለማን እንደሆነ ያወቅነው ነገር የለም አለም ከተባለ ለእኛ ለአምራቾች ሊቀርብልን ይገባል " ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል አምራቾች በተወሰነ ማስተካከያ ሪፕርፕዝ (Repurpose) በማድረግ በኮቪድ ወቅት የመጠጥ፣ የውሃ እና የአልኮን ፋብሪካዎች ሳኒታይዘር እንዲያመርቱ የተደረገበት አጋጣሚ እንደነበር በመግለጽ የፕላስቲክ ኢንዱስትሪዎችን ተመመሳሳይ ሂደት እንዲከተሉ ይደረጋል ማለታቸው ይታወሳል።
በዚህ ሂደት ላይ ምክክር አላቹ ወይ ? ስንል ሃሳባቸውን የጠየቅናቸው አቶ በረከት " ምክክር የለንም ያንን እና ይሄንን ማነጻጸር ተገቢ አይደለም " ብለዋል።
" የአልኮል እና የኬሚካል ኢንዱስትሪዎችን ለወጥ አድርጎ ሳኒታይዘር እንዲያመርቱ ማድረግ የማሽኖቹን መሰረታዊ ባህሪ መቀየር አያስፈልገውም በእኛ መንገድ ግን ማሽኖቹን repurpose ማድረግ የሚቻልበት እድል የለም የአመራረት ሂደቱ ፕላስቲክ እና ወረቀት አብረው የሚሄዱ ስላልሆኑ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የማህበሩ አባል አቶ በረከት በሰጡት ምክረ ሃሳብም "አዋጁ ጸድቋል በረቂቅ ሂደቱ ላይ የነበሩ ያሳታፊነት ስህተቶች መደገም የለባቸውም ከእኛ ጋር በትክክል ምክክር ያስፈልጋል " ያሉ ሲሆን ኢንዱስትሪ በምንም ሁኔታ በስድስት ወር ውስጥ ስራ አቁም ሊባል አይገባም የሌላ ሃገራት ልምድም ይህንን አያሳይም ሲሉ ተናግረዋል።
" በየትኛውም ሃገር ያልተፈጸመ ተግባር ለምን በእኛ ሃገር ይፈጸማል ? " ሲሉም ጠይቀዋል።
" እነዚህ ኢንዱስትሪዎች በተከራይዋቸው ዌር ሃውስ ውስጥ የሚሰሩ ናቸው ሲከራዩም የ6 ወር እና የ1 አመት ክፍያ ነው የሚፈጽሙት በዚህ ምክንያት ቀድመው በከፈሉት ክፍያ ብቻ ኪሳራ ይደርስባቸዋል " " ሲሉ ገልጸዋል።
" ማሽኖቹም ከጥቅም ውጪ ነው የሚሆኑት ለማጓጓዝም ሰፊ ቦታ እና መሽነሪዎች የሚፈልጉ ናቸው በእነዚህ እና ሌሎች ምክንያቶች የሽግግር ጊዜው ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበ አይደለም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ExitExam : ከሰኔ 02 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል። ከ190 ሺህ በላይ ተፈታኞች በ51 ዩኒቨርሲቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት የመውጫ ፈተናውን እንደወሰዱ ይጠበቃል። ከእነዚህ ውስጥ 88 ሺህ የሚሆኑት ዳግም የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ናቸው። በዛሬ ዕለት በተጨማሪም በክረምት የመምህራን ስልጠና መርሐግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩ ከ5 ሺህ…
#ExitExam
የ2017 ዓ/ም የቅድመ ምረቃ መውጫ ፈተና ውጤት ለዩኒቨርሲቲዎች እየተላከ ይገኛል።
ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና ውጤት ለተቋማት እየላከ እንደሚገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተቋማቱ ያገኘው መረጃ ያሳያል።
ውጤቱ የደረሳቸው የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸው ውጤታቸውን በሬጅስትራር በኩል እንዲያዩ መልዕክት እያስተላለፉ ናቸው።
ካስፈተኗቸው ተማሪዎች መካከልም ምን ያህል ተማሪዎች ፈተናውን እንዳለፉም ይፋ ማድረግ ጀምረዋል።
የመውጫ ፈተናው ውጤት እስካሁን ሁሉም ተማሪ ባለበት ሆኖ እንዲያይ ከዚህ በፊት ውጤት በሚታይበት ድረ-ገጽ https://result.ethernet.edu.et ላይ አልተለቀቀም።
ውጤት በድረ-ገጽ ማየት ሲጀመር ተከታትለን መረጃ እናደርሳለን።
በሌላ በኩል ፥ በርካታ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማሯቸውን ተማሪዎች በሳምንቱ መጨረሻ ያስመርቃሉ።
ከ20 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች የ2017 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ቅዳሜ ሰኔ 14/2017 ዓ.ም የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እሑድ ሰኔ 15/2017 ዓ.ም ያካሒዳሉ።
🎓 አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ራያ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ወልድያ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 አክሱም ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ጂንካ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 መቱ ዩኒቨርሲቲ እና
🎓 የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሳምንቱ መጨረሻ ተማሪዎቻቸውን ከሚያስመርቁ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
የ2017 ዓ/ም የቅድመ ምረቃ መውጫ ፈተና ውጤት ለዩኒቨርሲቲዎች እየተላከ ይገኛል።
ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና ውጤት ለተቋማት እየላከ እንደሚገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተቋማቱ ያገኘው መረጃ ያሳያል።
ውጤቱ የደረሳቸው የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸው ውጤታቸውን በሬጅስትራር በኩል እንዲያዩ መልዕክት እያስተላለፉ ናቸው።
ካስፈተኗቸው ተማሪዎች መካከልም ምን ያህል ተማሪዎች ፈተናውን እንዳለፉም ይፋ ማድረግ ጀምረዋል።
የመውጫ ፈተናው ውጤት እስካሁን ሁሉም ተማሪ ባለበት ሆኖ እንዲያይ ከዚህ በፊት ውጤት በሚታይበት ድረ-ገጽ https://result.ethernet.edu.et ላይ አልተለቀቀም።
ውጤት በድረ-ገጽ ማየት ሲጀመር ተከታትለን መረጃ እናደርሳለን።
በሌላ በኩል ፥ በርካታ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማሯቸውን ተማሪዎች በሳምንቱ መጨረሻ ያስመርቃሉ።
ከ20 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች የ2017 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ቅዳሜ ሰኔ 14/2017 ዓ.ም የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እሑድ ሰኔ 15/2017 ዓ.ም ያካሒዳሉ።
🎓 አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ራያ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ወልድያ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 አክሱም ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ጂንካ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣
🎓 መቱ ዩኒቨርሲቲ እና
🎓 የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሳምንቱ መጨረሻ ተማሪዎቻቸውን ከሚያስመርቁ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በነፃ ተሰናበቱ።
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬን የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነፃ አሰናበታቸው።
13 ዓመት ተፈርዶባቸዉ በማረሚያ ቤት የነበሩት የቀድሞው ከንቲባ በዛሬዉ ዕለት በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነበራቸው ችሎት የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከወሰነባቸው የፍርድ ዉሳኔ በነፃ መሰናበታቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተነግረዋል።
የቀድሞው ከንቲባ በአጠቃላይ ከቀረበባቸዉ 7 የክስ መዝገቦች በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከቀረበባቸው 2 ክሶች በነፃ ተሰናብተው የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ3 ክሶች ነፃ በ2 ክሶች ደግሞ 13 ዓመት እስራት ፈርዶባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ከፍርዱ በኃላ ባለቤታቸው ወ/ሮ ዜናዬ ተሰማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ " ፀጋዬ ቱኬ የፖለቲካ እስረኛ እንጂ ጥፋተኛ እንዳልሆነ፣ ለሁለት ዓመት የሚጠጋ ጊዜ ያለ አግባብ በእስር ቤት እንደተንገላታ ፣ጉዳዩን የያዙ ዳኞች በባለስልጣን ጫና ሲቀያየሩ እንደነበር፣ በአጠቃላይ የፍርድ ዉሳኔዉ ጣልቃገብነት የታየበት እንደነበርና ይግባኝ እንደጀመሩ " ተናግረው ነበር።
የቀድሞው ከንቲባ በዛሬው ዕለት በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነጻ ተሰናብተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የችሎት ሂደቱን ቦታዉ ላይ በመገኘት የተከታተለ ሲሆን የዉሳኔዉን አፈፃፀም የክልሉ ማረሚያ ተቋም የወሰደ ሲሆን ከምሳ ሰዓት በኋላ ከእስር እንደሚለቀቁ ከስፍራዉ ማረጋገጥ ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬን የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነፃ አሰናበታቸው።
13 ዓመት ተፈርዶባቸዉ በማረሚያ ቤት የነበሩት የቀድሞው ከንቲባ በዛሬዉ ዕለት በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነበራቸው ችሎት የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከወሰነባቸው የፍርድ ዉሳኔ በነፃ መሰናበታቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተነግረዋል።
የቀድሞው ከንቲባ በአጠቃላይ ከቀረበባቸዉ 7 የክስ መዝገቦች በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከቀረበባቸው 2 ክሶች በነፃ ተሰናብተው የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ3 ክሶች ነፃ በ2 ክሶች ደግሞ 13 ዓመት እስራት ፈርዶባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ከፍርዱ በኃላ ባለቤታቸው ወ/ሮ ዜናዬ ተሰማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ " ፀጋዬ ቱኬ የፖለቲካ እስረኛ እንጂ ጥፋተኛ እንዳልሆነ፣ ለሁለት ዓመት የሚጠጋ ጊዜ ያለ አግባብ በእስር ቤት እንደተንገላታ ፣ጉዳዩን የያዙ ዳኞች በባለስልጣን ጫና ሲቀያየሩ እንደነበር፣ በአጠቃላይ የፍርድ ዉሳኔዉ ጣልቃገብነት የታየበት እንደነበርና ይግባኝ እንደጀመሩ " ተናግረው ነበር።
የቀድሞው ከንቲባ በዛሬው ዕለት በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነጻ ተሰናብተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የችሎት ሂደቱን ቦታዉ ላይ በመገኘት የተከታተለ ሲሆን የዉሳኔዉን አፈፃፀም የክልሉ ማረሚያ ተቋም የወሰደ ሲሆን ከምሳ ሰዓት በኋላ ከእስር እንደሚለቀቁ ከስፍራዉ ማረጋገጥ ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
SAMSUNG S24 ULTRA !
ዛሬ የቶምቦላ ሎተሪ ለቆረጠ 1 እድለኛ SAMSUNG S24 ULTRA ስልክ ይሸለማል!
ቶምቦላው ባለ 3 እና 2 መኝታቤት አፓርትመንት ፣ ID6 እና BYD SUV መኪና ሽልማቶችን ይዞ መጥቷል
ቶምቦላ ሎተሪን በ ethiolottery.et እና በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ ይግዙ ፡፡
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
SAMSUNG S24 ULTRA !
ዛሬ የቶምቦላ ሎተሪ ለቆረጠ 1 እድለኛ SAMSUNG S24 ULTRA ስልክ ይሸለማል!
ቶምቦላው ባለ 3 እና 2 መኝታቤት አፓርትመንት ፣ ID6 እና BYD SUV መኪና ሽልማቶችን ይዞ መጥቷል
ቶምቦላ ሎተሪን በ ethiolottery.et እና በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ ይግዙ ፡፡
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
"ከግማሽ በመቶ በላይ የሚሆነው የጥላቻ ንግግር የተሰራጨው በታዋቂ ሰዎች/በፐብሊክ ፊገርስ መሆኑን ጥናቱ ያረጋግጣል”- ጥናት
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በማህበራዊ ሚዲያዎች አማካኝነት የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት አሳሳቢ ደረጃ ስለመድረሱ በጥናት ማረጋገጡን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
"በሀገራችን የሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር አሳሳቢ ደርጃ ላይ መድረሱ በጥናት ተረጋግጧል” ሲልም ተናግሯል።
በጥናቱ ግኝት መሠረት፣ “አብዛኛው የጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ የተሰራጨው ባብዛኛው በጽሑፍ እና በተንቀሳቃሽ ምስል፤ በአብዛኛው የተሰራጨውም በፌስቡክ፣ ቲክቲቶክና በቴሌግራም እንደሆነ ጥናቱ ያመለክታል” ብሏል።
ባለስልጣኑ በመግለጫው፣ ተጠቃሚዎቹ የተሳሳተ መረጃ ሲያገኙ ሪፖርት እንደሚያደርጉና ለማን ሪፖርት እንደሚደረግ እንደማያውቁ ተናግሯል።
ይህን ሁሉ ያሉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አማካሪ አቶ ታምራት ደጀኔ፣ “ከግማሽ በመቶ በላይ የሚሆኑ የጥላቻ ንግግር የተሰራጨው በታዋቂ ሰዎች/ፐብሊክ ፊገርስ በሚባሉት መሆኑን ጥናቱ ያረጋግጣል” ብለዋል።
በግኝቱ መሠረት፣ “የጥላቻ ንግግር ያነጣጠረው የፖለቲካ አመለካካት ላይ ነው፡፡ ቀሪዎቹ በብሔርና ሃይማኖት ናቸው፤ (ብሔር 15%፣ ሃይማት 6%”) ብለው፣ “ሀሰተኛ መረጃው የተሰራጨባቸው ዋና ዋና መንገዶች በግኝቱ መሠረት የሐሰት አውድ በመጠቀም፣ በተሳሳቱ መረጃዎች (በእንዝላልነት)፣ አሳሳች በሆኑ ይዘቶች..." መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ለማሰራጨት የተፈለገው፣ “ማሕበራዊ አለመረጋጋት እንዲፈጠር፣ በማህበረሰብ መካከል ግጭት የመቀስቀስ አላማ፤ የመግስት ተቋማትና መንግስት ሥራቸውን ተረግተው እንዳያከናውኑ ለማድረግና የማስተባበል፣ የግለሰብና የቡድኖችን ሥም ለማጠልሸት..” መሆኑን የጥናቱ ዳሰሳ እንደሚያስረዳ ገልጸዋል።
"ዜጎችን ለአመጽና ለጥቃት እንዲነሳሱ መቀስቀም 15% ይዟል፣ የማህበረሰቡን አብሮ የመኖር እሴት በመሸርሸርም ወደ 11% ታርጌት እንደተደረገ መረጃው ያመለክታል" ነው ያሉት።
“እንደ ኢትዮጵያ ቴሌ ኮሚዩኒኬሽን መረጃ በአገራችን ከ44 ሚሊዮን በላይ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ይገኛሉ፡፡ ለብቻው የማሕበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ደግሞ ወደ 4 ሚሊዮን ይጠጋሉ፡፡ ይህ ቀላል ቁጥር አይደለም” ሲሉም ተናግረዋል።
ከአጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አንጻር፣ “የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ቁጥር አነስተኛ ቢሆንም በአንጀንዳ ሴቲንግ ከፍተኛ ሚና አላቸው፣ ኮንተንት እስከመወሰን ራሱ የሚደርስ አቅም እንዳላቻው”ም የጥናቱ ግኝት እንደሚያስረዳ አብራርተዋል።
የጥናቱ መረጃ ምንጭ በአምስት ዋና ዋና ማለትም ሜታ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክና ቲዊተር ማህበራዊ ሚዲያዎችን መሠረት ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
እንዲሁም፣ ከ500 ሺሕ ባላይ ተከታዮች ያላቸው ተጸዕኖ ፈጣሪ፣ ግለሰቦችን መሠረት ያደረገ እንደሆነ እና ወደ 1700 ከሚሆኑ ተጽዕኖ ፈታጣሪ ግለሰቦችም በጉዳዩ ዙሪያ የህዝብ አስተያየት እንደተሰበሰበ ገልጸው፣ “ከ2000 በላይ ይዘቶች በባለሙያዎቻችን ሞኒተር ተደርገዋል” ተብሏል።
የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ለሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት ምክንያት እንደሆነ፣ በዚህም ታዋቂ ሰዎች 56%፣ መገናኛ ብዙኃን 26%፣ ግለሰቦች 17% አስተዋጽኦ እንዳደረጉ ተነግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በማህበራዊ ሚዲያዎች አማካኝነት የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት አሳሳቢ ደረጃ ስለመድረሱ በጥናት ማረጋገጡን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
"በሀገራችን የሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር አሳሳቢ ደርጃ ላይ መድረሱ በጥናት ተረጋግጧል” ሲልም ተናግሯል።
በጥናቱ ግኝት መሠረት፣ “አብዛኛው የጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ የተሰራጨው ባብዛኛው በጽሑፍ እና በተንቀሳቃሽ ምስል፤ በአብዛኛው የተሰራጨውም በፌስቡክ፣ ቲክቲቶክና በቴሌግራም እንደሆነ ጥናቱ ያመለክታል” ብሏል።
ባለስልጣኑ በመግለጫው፣ ተጠቃሚዎቹ የተሳሳተ መረጃ ሲያገኙ ሪፖርት እንደሚያደርጉና ለማን ሪፖርት እንደሚደረግ እንደማያውቁ ተናግሯል።
ይህን ሁሉ ያሉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አማካሪ አቶ ታምራት ደጀኔ፣ “ከግማሽ በመቶ በላይ የሚሆኑ የጥላቻ ንግግር የተሰራጨው በታዋቂ ሰዎች/ፐብሊክ ፊገርስ በሚባሉት መሆኑን ጥናቱ ያረጋግጣል” ብለዋል።
በግኝቱ መሠረት፣ “የጥላቻ ንግግር ያነጣጠረው የፖለቲካ አመለካካት ላይ ነው፡፡ ቀሪዎቹ በብሔርና ሃይማኖት ናቸው፤ (ብሔር 15%፣ ሃይማት 6%”) ብለው፣ “ሀሰተኛ መረጃው የተሰራጨባቸው ዋና ዋና መንገዶች በግኝቱ መሠረት የሐሰት አውድ በመጠቀም፣ በተሳሳቱ መረጃዎች (በእንዝላልነት)፣ አሳሳች በሆኑ ይዘቶች..." መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ለማሰራጨት የተፈለገው፣ “ማሕበራዊ አለመረጋጋት እንዲፈጠር፣ በማህበረሰብ መካከል ግጭት የመቀስቀስ አላማ፤ የመግስት ተቋማትና መንግስት ሥራቸውን ተረግተው እንዳያከናውኑ ለማድረግና የማስተባበል፣ የግለሰብና የቡድኖችን ሥም ለማጠልሸት..” መሆኑን የጥናቱ ዳሰሳ እንደሚያስረዳ ገልጸዋል።
"ዜጎችን ለአመጽና ለጥቃት እንዲነሳሱ መቀስቀም 15% ይዟል፣ የማህበረሰቡን አብሮ የመኖር እሴት በመሸርሸርም ወደ 11% ታርጌት እንደተደረገ መረጃው ያመለክታል" ነው ያሉት።
“እንደ ኢትዮጵያ ቴሌ ኮሚዩኒኬሽን መረጃ በአገራችን ከ44 ሚሊዮን በላይ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ይገኛሉ፡፡ ለብቻው የማሕበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ደግሞ ወደ 4 ሚሊዮን ይጠጋሉ፡፡ ይህ ቀላል ቁጥር አይደለም” ሲሉም ተናግረዋል።
ከአጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አንጻር፣ “የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ቁጥር አነስተኛ ቢሆንም በአንጀንዳ ሴቲንግ ከፍተኛ ሚና አላቸው፣ ኮንተንት እስከመወሰን ራሱ የሚደርስ አቅም እንዳላቻው”ም የጥናቱ ግኝት እንደሚያስረዳ አብራርተዋል።
የጥናቱ መረጃ ምንጭ በአምስት ዋና ዋና ማለትም ሜታ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክና ቲዊተር ማህበራዊ ሚዲያዎችን መሠረት ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
እንዲሁም፣ ከ500 ሺሕ ባላይ ተከታዮች ያላቸው ተጸዕኖ ፈጣሪ፣ ግለሰቦችን መሠረት ያደረገ እንደሆነ እና ወደ 1700 ከሚሆኑ ተጽዕኖ ፈታጣሪ ግለሰቦችም በጉዳዩ ዙሪያ የህዝብ አስተያየት እንደተሰበሰበ ገልጸው፣ “ከ2000 በላይ ይዘቶች በባለሙያዎቻችን ሞኒተር ተደርገዋል” ተብሏል።
የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ለሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት ምክንያት እንደሆነ፣ በዚህም ታዋቂ ሰዎች 56%፣ መገናኛ ብዙኃን 26%፣ ግለሰቦች 17% አስተዋጽኦ እንዳደረጉ ተነግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ከማረሚያ ወጥተዉ ወደ ቤታቸዉ ገብተዋል " - ቤተሰቦች
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ እና አብሯቸዉ ታስረዉ የነበሩት የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ታርኩ ታመነ ከማረሚያ ተለቀዉ ወደ ቤታቸው መግባታቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ላለፉት ሁለት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በእስር ላይ የቆዩትና ከሁለት ወራት በፊትም የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሁለት የክስ 13 ዓመት ፅኑ እስራት ዉሳኔ አስተላልፎባቸዉ የነበሩት የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ይግባኝ ጠይቀዉ ዛሬ በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነፃ መሰናበታቸውን ተከትሎ ከሀዋሳ ከተማ ማረሚያ ቤት ወጥተው ቤተሰቦቻቸውን ተቀላቅለዋል።
ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ከማረሚያ ቤት ወጥተዉ ወደ ቤታቸዉ ሲሄዱ በርከት ሰዎች በሞተር ሳይክሎችና በመኪና አጅቧቸዉ ደስታቸዉን ሲገልፁ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ እና አብሯቸዉ ታስረዉ የነበሩት የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ታርኩ ታመነ ከማረሚያ ተለቀዉ ወደ ቤታቸው መግባታቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ላለፉት ሁለት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በእስር ላይ የቆዩትና ከሁለት ወራት በፊትም የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሁለት የክስ 13 ዓመት ፅኑ እስራት ዉሳኔ አስተላልፎባቸዉ የነበሩት የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ይግባኝ ጠይቀዉ ዛሬ በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በነፃ መሰናበታቸውን ተከትሎ ከሀዋሳ ከተማ ማረሚያ ቤት ወጥተው ቤተሰቦቻቸውን ተቀላቅለዋል።
ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ከማረሚያ ቤት ወጥተዉ ወደ ቤታቸዉ ሲሄዱ በርከት ሰዎች በሞተር ሳይክሎችና በመኪና አጅቧቸዉ ደስታቸዉን ሲገልፁ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
“ ካሜራ ይዛ አንገቷን በመስኮት አውጥታ ነበር ”- የኮንታ ዞን ጸጥታ መምሪያ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንታ ዞን ዛሬ በደረሰ የመኪና አደጋ የዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን የካሜራ ባለሙያ ሕይወት መቀጠፉን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
አንድ ዞኑ ጸጥታ መምሪያ አካል በሰጡን ቃል፣ “ አንዲት ካሜራ ማን ለመግስታዊ የሥራ ጉዳይ ከዞን ወደ ወረዳ እየሄደች በአጋጣሚ ቀረጻ ላይ እያለች መኪና ተገልብጦ ነው የሞተችው ” ብለዋል።
የአደጋው ምክንያት ምን እንደሆነና ከሟቿ ባሻገር ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱ ሲጠየቁ፣ “ የቴክኒክ ችግር ይመስለኛል። የመንገድ፣ የቦታ ችግር አይደለም። የቴክኒክ ችግር ሳይሆን አይቀርም የሚል ስጋት አለ። ሌላ ሰው ብዙ የተጎዳ የለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“ ካሜራ ይዛ አንገቷን በመስኮት አውጥታ ነበር ” ብለው፣ አደጋው ዛሬ ከረፋዱ 4 ሰዓት ገደማ እንደደረሰም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ “ዛሬ ረፋድ እህታችን ወ/ሮ ቃልኪዳን መለሰ የኮንታ ዞን የመንግስት ኮሚኒዩኬሽን የሚዲያ ባለሙያ ለመንግስት ሥራ በሚታደርገው ጉዞ በደረሳት ድንገተኛ የመኪና እደጋ ሕይወቷ አልፏል ” ሲሉ አስታውቀዋል።
“ አደጋው ሲያጋጥም በቅርብ ርቀት ለነበርን ሐዘኑ በጣም ጥልቅ ነው። ፈጣሪ ነፍሷን በአፀደ ገነት ያኑርልን ” ብለው ለሟች ቤተሰብ መጽናናትን ተመኝተዋል። “ በአደጋው የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው የሥራ ባልደርቦቻችንም ፈጣሪ ፈጥንነው እንዲያገግሙ ብርታቱን ይስጣችው ”ሲሉ በፌስቡክ ገጻቸው አስፍረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንታ ዞን ዛሬ በደረሰ የመኪና አደጋ የዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን የካሜራ ባለሙያ ሕይወት መቀጠፉን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
አንድ ዞኑ ጸጥታ መምሪያ አካል በሰጡን ቃል፣ “ አንዲት ካሜራ ማን ለመግስታዊ የሥራ ጉዳይ ከዞን ወደ ወረዳ እየሄደች በአጋጣሚ ቀረጻ ላይ እያለች መኪና ተገልብጦ ነው የሞተችው ” ብለዋል።
የአደጋው ምክንያት ምን እንደሆነና ከሟቿ ባሻገር ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱ ሲጠየቁ፣ “ የቴክኒክ ችግር ይመስለኛል። የመንገድ፣ የቦታ ችግር አይደለም። የቴክኒክ ችግር ሳይሆን አይቀርም የሚል ስጋት አለ። ሌላ ሰው ብዙ የተጎዳ የለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“ ካሜራ ይዛ አንገቷን በመስኮት አውጥታ ነበር ” ብለው፣ አደጋው ዛሬ ከረፋዱ 4 ሰዓት ገደማ እንደደረሰም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ “ዛሬ ረፋድ እህታችን ወ/ሮ ቃልኪዳን መለሰ የኮንታ ዞን የመንግስት ኮሚኒዩኬሽን የሚዲያ ባለሙያ ለመንግስት ሥራ በሚታደርገው ጉዞ በደረሳት ድንገተኛ የመኪና እደጋ ሕይወቷ አልፏል ” ሲሉ አስታውቀዋል።
“ አደጋው ሲያጋጥም በቅርብ ርቀት ለነበርን ሐዘኑ በጣም ጥልቅ ነው። ፈጣሪ ነፍሷን በአፀደ ገነት ያኑርልን ” ብለው ለሟች ቤተሰብ መጽናናትን ተመኝተዋል። “ በአደጋው የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው የሥራ ባልደርቦቻችንም ፈጣሪ ፈጥንነው እንዲያገግሙ ብርታቱን ይስጣችው ”ሲሉ በፌስቡክ ገጻቸው አስፍረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia