Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኮሬ 🛑 “ አሁንም ግድያው እንደቀጠለ ነው። ዛሬም 3 ሰዎች በታጣቂዎች ተገድለዋል” - ኮሬ ዞን 🔵 “ ምንም መፍትሄ የሌለው ጉዳይ ነው የሆነው። ግድያና መፈናቀሉ ቀጥሏል” - በፌደራል ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የኮሬ ህዝብ ተወካይ ዛሬ (ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ/ም) ሦስት ንጹሐን ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል ከምዕራብ ጉጂ በተነሱ ታጣቂዎች መገዳላቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኮሬ ዞን አስተዳደር ለቲክቫህ…
#ኮሬ

🛑 " ከትላንትና በስቲያም ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ቆስለዋል። የአርሶ አደሩ ስጋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው " - ኮሬ ዞን

🔵 " እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ በማጽዳት መሬቱን መውሰድ ነው የተፈለገው " - የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ዳኖ ቀበሌ ከትላንት በስቲያ ሁለት አርሶ አደሮች በታጣቂዎች ጥቃት እንደቆሰሉ ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ተወካይ አቶ አማረ አክሊሉ፣ ጉዳዩ በመንግስት ልዩ ትኩረት ስላልሰጠው አርሶ አደሮች በከፍተኛ ስጋት ላይ በመሆናቸው የፌዴራሉ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ጥቃቱን እንዲያስቆም ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አማረ በዝርዝር ምን አሉ ?

" በጎርካ ወረዳ ዳኖ ቀበሌ ትላንትም ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ቆስለዋል። የአርሶ አደሩ ስጋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው። አገዳደላቸው ራሱ ዘግናኝ ነው። 

አንድ ሰው ላይ እስከ 30 ጥይት ነው የሚያርከፈክፉት አጥንቱ እስኪታይ።

አሁን የመኸር እርሻ ወቅት በመሆኑ የአረም ሥራ ላይ ባሉ አርሶ አደሮች ነው ጥቃት እየደረሰ ያለው።

በአብዛኛው ጥቃቱ የሚሰነዘረው ጋላና ወረዳ ነው። ጥቃቱን የሚያደርሱት እዛው አካባቢ የመሸጉ ታጣቂዎች ናቸው።

ከምዕራብ ጉጂ ተነስተው ነው ጥቃት የሚፈጽሙት። በአካባቢው ላይ የመሬት ይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱ ናቸው።

በዋነናነት ‘ወደ 18 ቀበሌዎችን አፈናቅለን ቦታ ካልወሰድን’ የሚሉ አካላት ናቸው። በዚሁ ምክንያት ነው በአርሶ አደሮች ግድያና ድብደባ፣ በንብረት ላይ ዘረፋ እየተፈጸመ ያለው።

የፌደራል መንግስት ካልገባ የአካባቢው ችግር እየተወሳሰበ ነው። ጣልቃ ገብቶ ነጻ ካላወጣ በስተቀር ግድያው ከ6 ዓመታት በላይ አስቆጥሮም አልቆመም። የሸኔ ታጣቂ አለ፤ ጉጂ ላይ የተወሸቀ ሌላ ታጣቂም አለ
" ነው ያሉት። 

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኮሬ ህዝብ ተወካይ ሀምዛዬ አወቀ (ዶ/ር) በበኩላቸው ለቲክቫህ ሰጡት ቃል፣ " መንግስት ባለበት አገር ነው ህዝቡ ጥቃት የሚደርስበት። ጥቃት የሚደርስበትም ከኦሮሚያ ክልል ነው " ብለዋል።

" በቁጥሩ ትንሽ ስለሆነ ይሄ ህዝብ ብቻውን መጋፈጥ አይችልም። መንግስት መከታ ካልሆነው በስተቀር የህልውና አደጋ ውስጥ ነው። መንግስት ተገቢውን እርምጃ እየወሰደ አይደለም "  ሲሉ ለቲክቫህ ተናግረዋል።

ለችግሩ መፈጠር መሠረታዊ መንስዔው፤ ታጣቂዎች በግልጽ ከዛ ህዝብ የሚፈልጉት ጉዳይ ምንድን ነው ? ስንል ላቀረብለንላቸው ጥያቄ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" የችግሩ መሠረታዊ ነገር እውነት እንነጋገር ከተባለ የግዛት መስፋፋት ፍላጎት መኖር ነው። ምንም ሌላ ምክንያት የለውም። ‘ሸኔ’ ምናምን እየተባለ ሰበብ እየተደረገ ይቀርባል እንጂ።

እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ በማጽዳት መሬቱን መውሰድ ነው የተፈለገው። በተለይ ከሁለት ቀበሌዎች ላይ ህዝቡ ከዚያ እንዲፈናቀል፤ እንዲጠፋ ተደርጓል።

ከዚያ በኋላ ግን እንደ አቡካዶ፣ ሙዝ የመሳሰሉ ቋሚ ተክሎች ሁሉ ተነቅለው እንዲጠፉ፣ አካባቢው ወደ ባድማነት እንዲቀየር፣ ባዶ መሬት ነው ተብሎ እንዲሰጥ የተደረገበት ሁኔታ አለ። 

በ20ውም ቀበሌያት ወረራ ሲደረግ ቋሚ ተክሎች ሁሉ ነው የሚነቀሉት። ይሄ የሚደረገው ለምንድን ነው? በሚል ብዙ ጊዜ እንጠይቃለን፤ የደረስንበትም ህዝቡን በማጥፋት መሬት ለመውረስ መሆኑን ነው
" ሲሉ አስረድተዋል።

ችግሩን ለምን ማስቆም እንዳልተቻለ ማብራሪያ እዲሰጡ በፅሑፍ መልዕክት ጭምር የጠየቅናቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ፣ " የአመራር ስልጠና ላይ ነኝ " በማለት ዝርዝር ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል ።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😢260😭6966😡26🕊8🥰4👏4😱3



group-telegram.com/tikvahethiopia/91422
Create:
Last Update:

#ኮሬ

🛑 " ከትላንትና በስቲያም ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ቆስለዋል። የአርሶ አደሩ ስጋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው " - ኮሬ ዞን

🔵 " እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ በማጽዳት መሬቱን መውሰድ ነው የተፈለገው " - የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ዳኖ ቀበሌ ከትላንት በስቲያ ሁለት አርሶ አደሮች በታጣቂዎች ጥቃት እንደቆሰሉ ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ተወካይ አቶ አማረ አክሊሉ፣ ጉዳዩ በመንግስት ልዩ ትኩረት ስላልሰጠው አርሶ አደሮች በከፍተኛ ስጋት ላይ በመሆናቸው የፌዴራሉ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ጥቃቱን እንዲያስቆም ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አማረ በዝርዝር ምን አሉ ?

" በጎርካ ወረዳ ዳኖ ቀበሌ ትላንትም ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ቆስለዋል። የአርሶ አደሩ ስጋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው። አገዳደላቸው ራሱ ዘግናኝ ነው። 

አንድ ሰው ላይ እስከ 30 ጥይት ነው የሚያርከፈክፉት አጥንቱ እስኪታይ።

አሁን የመኸር እርሻ ወቅት በመሆኑ የአረም ሥራ ላይ ባሉ አርሶ አደሮች ነው ጥቃት እየደረሰ ያለው።

በአብዛኛው ጥቃቱ የሚሰነዘረው ጋላና ወረዳ ነው። ጥቃቱን የሚያደርሱት እዛው አካባቢ የመሸጉ ታጣቂዎች ናቸው።

ከምዕራብ ጉጂ ተነስተው ነው ጥቃት የሚፈጽሙት። በአካባቢው ላይ የመሬት ይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱ ናቸው።

በዋነናነት ‘ወደ 18 ቀበሌዎችን አፈናቅለን ቦታ ካልወሰድን’ የሚሉ አካላት ናቸው። በዚሁ ምክንያት ነው በአርሶ አደሮች ግድያና ድብደባ፣ በንብረት ላይ ዘረፋ እየተፈጸመ ያለው።

የፌደራል መንግስት ካልገባ የአካባቢው ችግር እየተወሳሰበ ነው። ጣልቃ ገብቶ ነጻ ካላወጣ በስተቀር ግድያው ከ6 ዓመታት በላይ አስቆጥሮም አልቆመም። የሸኔ ታጣቂ አለ፤ ጉጂ ላይ የተወሸቀ ሌላ ታጣቂም አለ
" ነው ያሉት። 

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኮሬ ህዝብ ተወካይ ሀምዛዬ አወቀ (ዶ/ር) በበኩላቸው ለቲክቫህ ሰጡት ቃል፣ " መንግስት ባለበት አገር ነው ህዝቡ ጥቃት የሚደርስበት። ጥቃት የሚደርስበትም ከኦሮሚያ ክልል ነው " ብለዋል።

" በቁጥሩ ትንሽ ስለሆነ ይሄ ህዝብ ብቻውን መጋፈጥ አይችልም። መንግስት መከታ ካልሆነው በስተቀር የህልውና አደጋ ውስጥ ነው። መንግስት ተገቢውን እርምጃ እየወሰደ አይደለም "  ሲሉ ለቲክቫህ ተናግረዋል።

ለችግሩ መፈጠር መሠረታዊ መንስዔው፤ ታጣቂዎች በግልጽ ከዛ ህዝብ የሚፈልጉት ጉዳይ ምንድን ነው ? ስንል ላቀረብለንላቸው ጥያቄ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" የችግሩ መሠረታዊ ነገር እውነት እንነጋገር ከተባለ የግዛት መስፋፋት ፍላጎት መኖር ነው። ምንም ሌላ ምክንያት የለውም። ‘ሸኔ’ ምናምን እየተባለ ሰበብ እየተደረገ ይቀርባል እንጂ።

እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ በማጽዳት መሬቱን መውሰድ ነው የተፈለገው። በተለይ ከሁለት ቀበሌዎች ላይ ህዝቡ ከዚያ እንዲፈናቀል፤ እንዲጠፋ ተደርጓል።

ከዚያ በኋላ ግን እንደ አቡካዶ፣ ሙዝ የመሳሰሉ ቋሚ ተክሎች ሁሉ ተነቅለው እንዲጠፉ፣ አካባቢው ወደ ባድማነት እንዲቀየር፣ ባዶ መሬት ነው ተብሎ እንዲሰጥ የተደረገበት ሁኔታ አለ። 

በ20ውም ቀበሌያት ወረራ ሲደረግ ቋሚ ተክሎች ሁሉ ነው የሚነቀሉት። ይሄ የሚደረገው ለምንድን ነው? በሚል ብዙ ጊዜ እንጠይቃለን፤ የደረስንበትም ህዝቡን በማጥፋት መሬት ለመውረስ መሆኑን ነው
" ሲሉ አስረድተዋል።

ችግሩን ለምን ማስቆም እንዳልተቻለ ማብራሪያ እዲሰጡ በፅሑፍ መልዕክት ጭምር የጠየቅናቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ፣ " የአመራር ስልጠና ላይ ነኝ " በማለት ዝርዝር ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል ።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/91422

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

"This time we received the coordinates of enemy vehicles marked 'V' in Kyiv region," it added. "There is a significant risk of insider threat or hacking of Telegram systems that could expose all of these chats to the Russian government," said Eva Galperin with the Electronic Frontier Foundation, which has called for Telegram to improve its privacy practices. "Like the bombing of the maternity ward in Mariupol," he said, "Even before it hits the news, you see the videos on the Telegram channels." Under the Sebi Act, the regulator has the power to carry out search and seizure of books, registers, documents including electronics and digital devices from any person associated with the securities market. The company maintains that it cannot act against individual or group chats, which are “private amongst their participants,” but it will respond to requests in relation to sticker sets, channels and bots which are publicly available. During the invasion of Ukraine, Pavel Durov has wrestled with this issue a lot more prominently than he has before. Channels like Donbass Insider and Bellum Acta, as reported by Foreign Policy, started pumping out pro-Russian propaganda as the invasion began. So much so that the Ukrainian National Security and Defense Council issued a statement labeling which accounts are Russian-backed. Ukrainian officials, in potential violation of the Geneva Convention, have shared imagery of dead and captured Russian soldiers on the platform.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American