Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
" ትምህርት ቤቶች ባቀረቡት የዋጋ ጭማሪ ፕሮፖዛል ላይከወላጆች ጋር መግባባት ላይ መድረስ ካልተቻለ ባለሥልጣኑ ውሳኔ የሚሰጥ ይሆናል " - የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ 1,227 የግል ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን እስከ 65 በመቶ ድረስ የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ እንዲያደርጉ እንደተፈቀደለቸው መዘገቡ ይታወሳል። ጭማሪውን ተከትሎ የአዲስ…
#AddisAbaba

የትምህርት ቤት ክፍያ !

20 በመቶ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር አለመስማማታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቅርቡ ባጸደቀው የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሰራር ስርአት ደንብ ቁጥር 194/2017 መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ላይ ከ ተማሪ ወላጅና አሳዳጊዎች ጋር ካልተስማሙ መንግስታዊ ካልሆኑ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት መካሄዱን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በውይይት መርሃ ግብሩ ፦
- የትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ፣
- የትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ከፍተኛ አመራሮች
- የግል ትምህርት ቤቶች አሰሪዎች ማህበር ፣
- የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እና የተማሪ ወላጅ ኮሚቴ ተወካዮች እንደ ተሳተፉ ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።

ውይይቱ የተካሄደው በጭማሪው ላይ መስማማት ላይ ያልደረሱ ትምህርት ቤቶች ደንቡ በሚያስቀምጠው መሰረት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አስተሳሰብ ለመያዝ እንዲቻል መሆኑን ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ "በደንቡ መሰረት 80 ፐርሰንት ያህል ትምህርት ቤቶች ከወላጆችና አሳዳጊዎች ጋር በመስማማት የአገልግሎት ክፍያ መጨመራቸው የሚበረታታ ተግባር ነው" ብለዋል።

እንደ ትምህርት ቢሮ ሃላፊው ገለጻ 20 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከክፍያ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ከወላጆች እና አሳዳጊዎች መስማማት ላይ አለመድረሳቸውን አመላክቷል።

የትምህርትና ስልጠናና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዘዲን ሙስባህ "በደንቡ ላይ በመግባባት ወደ ስራ መገባቱን በዚህም መሰረት በርካታ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመስማማት መጨመራቸውን ፣ መመሪያውን መሰረት በማድረግም ባለስልጣኑ በተቀሩትና መስማማት ባልቻሉት ላይ  ውሳኔ መስጠቱን" አሳውቀዋል ።

ባለሥልጣኑ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ በዝርዝር ባይገለጽም የወላጆችን የመክፈል አቅም እና የትምህርት ተቋማቱን የግብአት አቅርቦት ታሳቢ አድርጎ ተግባራዊ የሆነ መሆኑን ስለመናገራቸው ትምህርት ቢሮው አሳውቋል።

#AddisAbabaEducationBureau

@tikvahethiopia
404😭57😡40🕊10🤔8😢8😱4



group-telegram.com/tikvahethiopia/98288
Create:
Last Update:

#AddisAbaba

የትምህርት ቤት ክፍያ !

20 በመቶ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር አለመስማማታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቅርቡ ባጸደቀው የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሰራር ስርአት ደንብ ቁጥር 194/2017 መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ላይ ከ ተማሪ ወላጅና አሳዳጊዎች ጋር ካልተስማሙ መንግስታዊ ካልሆኑ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት መካሄዱን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በውይይት መርሃ ግብሩ ፦
- የትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ፣
- የትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ከፍተኛ አመራሮች
- የግል ትምህርት ቤቶች አሰሪዎች ማህበር ፣
- የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እና የተማሪ ወላጅ ኮሚቴ ተወካዮች እንደ ተሳተፉ ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።

ውይይቱ የተካሄደው በጭማሪው ላይ መስማማት ላይ ያልደረሱ ትምህርት ቤቶች ደንቡ በሚያስቀምጠው መሰረት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አስተሳሰብ ለመያዝ እንዲቻል መሆኑን ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ "በደንቡ መሰረት 80 ፐርሰንት ያህል ትምህርት ቤቶች ከወላጆችና አሳዳጊዎች ጋር በመስማማት የአገልግሎት ክፍያ መጨመራቸው የሚበረታታ ተግባር ነው" ብለዋል።

እንደ ትምህርት ቢሮ ሃላፊው ገለጻ 20 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከክፍያ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ከወላጆች እና አሳዳጊዎች መስማማት ላይ አለመድረሳቸውን አመላክቷል።

የትምህርትና ስልጠናና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዘዲን ሙስባህ "በደንቡ ላይ በመግባባት ወደ ስራ መገባቱን በዚህም መሰረት በርካታ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመስማማት መጨመራቸውን ፣ መመሪያውን መሰረት በማድረግም ባለስልጣኑ በተቀሩትና መስማማት ባልቻሉት ላይ  ውሳኔ መስጠቱን" አሳውቀዋል ።

ባለሥልጣኑ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ በዝርዝር ባይገለጽም የወላጆችን የመክፈል አቅም እና የትምህርት ተቋማቱን የግብአት አቅርቦት ታሳቢ አድርጎ ተግባራዊ የሆነ መሆኑን ስለመናገራቸው ትምህርት ቢሮው አሳውቋል።

#AddisAbabaEducationBureau

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/98288

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Channels are not fully encrypted, end-to-end. All communications on a Telegram channel can be seen by anyone on the channel and are also visible to Telegram. Telegram may be asked by a government to hand over the communications from a channel. Telegram has a history of standing up to Russian government requests for data, but how comfortable you are relying on that history to predict future behavior is up to you. Because Telegram has this data, it may also be stolen by hackers or leaked by an internal employee. He said that since his platform does not have the capacity to check all channels, it may restrict some in Russia and Ukraine "for the duration of the conflict," but then reversed course hours later after many users complained that Telegram was an important source of information. These administrators had built substantial positions in these scrips prior to the circulation of recommendations and offloaded their positions subsequent to rise in price of these scrips, making significant profits at the expense of unsuspecting investors, Sebi noted. Following this, Sebi, in an order passed in January 2022, established that the administrators of a Telegram channel having a large subscriber base enticed the subscribers to act upon recommendations that were circulated by those administrators on the channel, leading to significant price and volume impact in various scrips. He floated the idea of restricting the use of Telegram in Ukraine and Russia, a suggestion that was met with fierce opposition from users. Shortly after, Durov backed off the idea.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American